South Omo Zone Trade & Market Development Department

South Omo Zone Trade & Market Development Department Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from South Omo Zone Trade & Market Development Department, Government Organization, SNNPR South Omo zone, Jinka Town, Jinka.

29/06/2020

መረጃውን ከዳሰነች ወረዳው የመንግስት ኮሙዮኒኬሽ ጉዳዮች ጽ/ቤት ለሚዲያችን የላኩት መልእክት ፡፡
============================
መነሻውን ሻሸመኔ አድርጎ ወደ ጎረቤት ሀገር ኬንያ ሊሻገር ሲል የነበረ 10 ኩንታል ካናቢስ የተሰኘው አደንዛዥ ዕፅ በዳሰነች ወረዳ በሎኮሮ ንዑስ ፖሊስ ጣቢያ በቀን 14/10/2012 ዓ.ም በፀጥታ መዋቅሩ በቁጥጥር ስር ዋለ፡፡ ኦሞራቴ ሰኔ 15 ቀን 2012 ዓ.ም ኮድ AA 93661 በሆነ አይሱዚ መኪና ሲንቀሳቀስ የነበረው 10 ኩንታል ካናቢስ የተሰኘው አደንዛዥ ዕፅ በቁጥጥር ስር መዋሉን የገለፁት የዳሰነች ወረዳ ፖሊስ ጽ/ቤት አዛዥ ረ/ኢ/ር ጴጥሮስ የቶክ ሲሆኑ መነሻውን ሻሸመኔ በማድረግ የተለያዩ የሀገሪቱን ክፍሎች አቋርጦ መዳረሻውን ኬንያ ለማድረግ በመንቀሳቀስ ላይ ባለበት ወቅት በሎኮሮ ንዑስ ፖሊስ ጣቢያ በፀጥታ መዋቅሩ ፍተሻ 10 ኩንታል ዕፅ በቁጥጥር ስር መዋሉን የተገለፀ ሲሆን
ተሸከርካሪውና አሽከርካሪውን ጨምሮ በጉዳዩ የተጠረጠሩ 3/ሶስት/ ተጠርጣሪዎች በህግ በቁጥጥር ስር ውለው የምርመራ ስራ መጀመሩ ተግልጻል፡፡ የወረዳው ፖሊስ ጽ/ቤቱ አዛዥ ረ/ኢ/ር ጴጥሮስ የቶክ እንደገለፁቱ በንዑስ ፖሊስ ጣቢያ ለነበሩ ለፀጥታ መዋቅሩ እጅ መንሻ 28,000.000/ሃያ ስምንት ሺህ/ ብር የቀረበ ቢሆንም የፀጥታ ሀይሉ በህዝብና መንግስት የተጣለበትን ሀገርን የመጠበቅ ቃል ኪዳንን በማክበር ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስራ ማዋል በመቻላቸው በወረዳው ህዝብና መንግስት ስም ምስጋና ያቀረቡ ሲሆን ፖሊስ በህዝብና መንግስት የተሰጠውን የሀገር ሰላምንና ደህንነት የማስጠበቅ ተግባሩን ከዚህ በበለጠ እንዲያጠናክር ጥሪ ያስተላለፉ ሲሆን ህዝቡ ከፀጥታ መዋቅሩ ጎን በመሆን ሀገርንና ህዝብን ሊጎዱ የሚችሉ ማንኛንም ዓይነት እንቅስቃሴዎችን በሚመለከት ወቅት በአከባቢው ለሚገኝ የፀጥታ መዋቅር ጥቆማ በመስጠት ከፀጥታ መዋቅሩ ጎን እንዲሆኑ ጥሪ ቀርባል፡፡

05/06/2020

#በቅርቡ በሀገሪቱ የተከሰተውን የሲሚንቶ ዋጋ መናር ተከትሎ ጥናት ላይ የተመሰረተ የአቅርቦትና የስርጭት ማስተካከያ ማድረጉን የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ገለጸ
=============================================
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 28 ፣ 2012 (ንኢሚ) በቅርቡ በሀገሪቱ የተከሰተውን የሲሚንቶ ዋጋ መናር ተከትሎ አሰራሩን በማጥናት ስርጭቱንና ዋጋውን በማረጋጋት ወደ ነበረበት ለመመለስ በመንግስት በኩል አቅጣጫ ተቀምጦ እንቅስቃሴዎች የተጀመሩ መሆኑን በንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር የኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክተር አቶ ወንደሙ ፍላቴ ገለጹ፡፡

ዳይሬክተሩ አክለውም ላለፉት ቀናት ተቋርጦ የነበረውን የሲሚንቶ ምርት አስመልክቶ በተደረገው ጥናት ምርቱን ለአምስት የመንግስት የልማት ድርጅቶች እና በተለዩ አስራ ሁለት ፋብሪካዎች ተመርጠው አገልግሎት ሲሰጡ ለነበሩ አከፋፋዮች በኮታ በማከፋፈል ማስቀጠል አስፈላጊ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

በዚህም መሰረት በየዕለቱ 340,238 ኩንታል የሲሚንቶ ምርት ከነዚህ አስራ ሁለት ፋብሪካዎች የሚነሳ ሆኖ ምርቱን በመንግስት ልማት ድርጅቶችና በግል አከፋፋዮች በእኩል መጠን በማከፋፈል በሚሰጣቸው የኮታ ድልድል መሰረት ስርጭቱ መቀጠል እንዳለበት፣ የምርት መሸጫ ዋጋን በተመለከተ ተጨማሪ ዕሴት ታክስን ጨምሮ አከፋፋይ ድርጅቶች በመንግስት በተወሰነላቸው የትርፍ ህዳግ ብቻ ማከፋፈል እንዳለባቸው፣ ዕለታዊ የስርጭትና የሽያጭ አፈጻጸም ሪፖርት በሰነድ ተደግፎ ለሚኒስቴር መ/ቤቱ መላክ እንዳለበት ተገልጿል፡፡

የመሸጫ ዋጋና የትርፍ ህዳግን በሚመለከትም የስሚንቶ ምርት ዋጋ በሁሉም ፋብሪካዎች የተለያየ ስለሆነ አምራቾች ከታህሳስ 30/2012 ዓ.ም በፊት በነበረው ዋጋ መሸጥ እንዳለባቸውና ቸርቻሪዎች ደግሞ ከገዙበት ዋጋ ላይ በአንድ ኩንታል 20 ብር ትርፍ ጨምረው መሸጥ እንዳለባቸው የተለገለጸ ሲሆን በዘላቂነት የአሰራር መመሪያ እየተዘጋጀ ስለሆነ በፍጥነት ጸድቆ ተግባራዊ የሚደረግ መሆኑንም ተብራርቷል፡፡ በመንግስት ከተወሰነው ዋጋ በላይ በሚሸጡ በማናቸውም ድርጅቶች ላይ የማያዳግም እርምጃ የሚወሰድ መሆኑንም ዳይሬክተሩ ገልጸዋል፡፡

ዘገባው፡- የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ነው፡፡

በደቡብ አሞ ዞን ሐመር ወረዳ ቱርሚ, ዲመካና አርቦሬ ከተሞች የተበላሹና ግዘ ያለፈባቸውን ምርቶች የመሰብሰብ ና የማስወገድ ስራ በከፍል
05/06/2020

በደቡብ አሞ ዞን ሐመር ወረዳ ቱርሚ, ዲመካና አርቦሬ ከተሞች የተበላሹና ግዘ ያለፈባቸውን ምርቶች የመሰብሰብ ና የማስወገድ ስራ በከፍል

የደቡብ ኦሞ ዞን የአክስፖርት ምርቶች ንግድ ግብረ-ሐይል የቁም እንስሳት ኤክስፖርት ንግድ አፈፃፀምን 19/09/2012 ገምግሟል፡፡ በዚህም መሠረት፡-በኤስፖርት ቀራዎች አማካኝነት ለውጭ ሀገራ...
27/05/2020

የደቡብ ኦሞ ዞን የአክስፖርት ምርቶች ንግድ ግብረ-ሐይል የቁም እንስሳት ኤክስፖርት ንግድ አፈፃፀምን 19/09/2012 ገምግሟል፡፡ በዚህም መሠረት፡-
በኤስፖርት ቀራዎች አማካኝነት ለውጭ ሀገራት በ3 ወራት (ከሚያዝያ-ሰኔ) በቁጥር 60,000 ፍየል ና በግ ለማቅረብ ታቅዶ ወደ ተግባር ተገብቷል፡፡ በዚህ መሠረት በ11ግለሰብ ነጋዴዎች ለኤክስፖርት ቄራዎች ከሚያዝያ ወር ጀምሮ፡-
ፍየል በቁጥር10,610 የቀረበ ሲሆን በአጠቃላይ 2012 ዓ.ም 93,996 ማቅረብ ተችሏል፡፡
በግ በቁጥር 819 የቀረበ ሲሆን በአጠቃላይ" 2012 ዓ.ም 18, 404 ማቅረብ ተችሏል፡፡
በመሆኑም ግብረ-ሐይሉ በተግባር ሂደት ውስጥ ያጋጠሙ ችግሮችን ና በቀጣይ ትኩረት የሚሹ ጉዳዮች የለዩ ሲሆን ችግሮቹን ለመፍታት ባለድርሻ አካላት በቅንጅት እንድሰሩ ኣቅጣጫ አስቀምጧል፡፡

NIDO Full Cream Milk ይመለከታል፣ NIDO Full Cream MilkPowder የከለር ልዩነት ማሳየቱን ከሸማች በቀረበ ጥቆማ መሠረት ምርመራ እንዲደረግ ለክልል ተስማሚነት ምዘና በ...
18/05/2020

NIDO Full Cream Milk ይመለከታል፣
NIDO Full Cream MilkPowder የከለር ልዩነት ማሳየቱን ከሸማች በቀረበ ጥቆማ መሠረት ምርመራ እንዲደረግ ለክልል ተስማሚነት ምዘና በላክነው ናሙና መሠረት ምርቱ የጥራት ችግር ያለበት መሆኑን የደ/ብ/ብ/ህ ክ/መ/ተስማሚነት ምዘና በቁጥር 2/7/13/660/52 በቀን 5/8/2012 ዓ.ም በተጻፈ ደብዳቤ ሸኝነት የምርመራ ውጤቱን ልከውልናል፡፡
በዚሁ መሠረት በ Batch No 9225034521+NLZ0069 1309:53 EG የታሸገ NIDOFull Cream MilkPowderን ከመጠቀም ህብረተሰቡ እንድቆጠብ እናሳስባለን፡፡

07/05/2020

በዝገባና የንግድስራ ፈቃድ አዋጅ ቁጥር 1150/2011 መሠረት፡-
የንግድ ሥራ ፈቃድ የተሰጠው ነጋዴ መብት
ማንኛውም የንግድ ሥራ ፈቃድ የተሰጠው ነጋዴ የሚከተሉት መብቶች ይኖሩታል፤
1. ይህን አዋጅ፣ አዋጁን ለማስፈጸም የወጡ ደንብና መመሪያ እንዲሁም በሌሎች ሕጎች የተቀመጡ ንግድ ነክ ድንጋጌዎችን በማክበር በተሰጠው የንግድ ፈቃድ መስክ ወሰን የንግድ ሥራዎች የማካሄድ፤
2. ለተመሳሳይ የንግድ ሥራ ለሚከፍተው ቅርንጫፍ ተጨማሪ የንግድ ሥራ ፈቃድ እንዲያወጣ ያለመገደድ፤
3. ስለ ንግድ ምዝገባና ፈቃድ አገልግሎት መረጃ የማግኘት፤
4 .በዚህ አዋጅ መሰረት የንግድ ምዝገባን፣ የንግድ ስምን እና የንግድ ፈቃድን የመለወጥና የማሻሻል፤
5 .በአዋጁ፣ አዋጁን ለማስፈጸም በወጡ ደንብ እና በመመሪያው የተፈቀዱ ሌሎች ተመሳሳይ ተግባራትን ማከናወን፡፡
የንግድ ሥራ ፈቃድ የተሰጠው ነጋዴ ግዴታዎች
የንግድ ሥራ ፈቃድ የተሰጠው ነጋዴ የሚከተሉት ግዴታዎች ይኖሩታል፤
1. የንግድ ፈቃድ የተሰጠባቸውን የተለያዩ የንግድ ሥራዎችን በአንድ ሥፍራ ወይም ግቢ ውስጥ አጣምሮ መሥራት በተጠቃሚው ሕዝብ ጤንነትና ደህንነት ወይም ንብረት ላይ ጉዳት የሚያደርስ ከሆነ እነዚህን ሥራዎች በተለያዩ ሥፍራዎች ወይም ግቢዎች በተናጠል የማካሄድ፤
2. የንግድ ዕቃዎቹንና የአገልግሎቶቹን የዋጋ ዝርዝር በንግድ ቤቱ በግልጽ ሥፍራ በሚታይ ቦታ ማመልከት ወይም በንግድ ዕቃዎች ላይ የመለጠፍ፤
3. የንግድ ሥራው ጠባይ የሚጠይቃቸውን ግዴታዎች የማክበር፣ ደረጃዎችን የማሟላት እና የመሥራት፤
4. የንግድ ሥራ ፍቃዱን በንግድ ቤቱ ውስጥ በግልጽ በሚታይ ቦታ የማስቀመጥ፣ ወይም የንግድ ቤቱ ቅርንጫፍ ከሆነ የመዝጋቢው አካል ማህተም የተደረገበት የንግድ ሥራ ፍቃድ ፎቶ ኮፒ በንግድ ቤቱ ውስጥ በግልጽ በሚታይ ቦታ ማስቀመጥ፤
5. የንግድ ፈቃዱን ለሌላ ለማንኛውም ሰው እንዲገለገልበት ወይም በመያዣነት እንዲይዘው ወይም እንዲያከራየው አሳልፎ ያለመስጠት፤
6. በአስተዳደራዊ ወይም በፍርድ ቤት ውሳኔ የንግድ ድርጅቱ እንዲፈርስ ወይም የግለሰብ ነጋዴ ንግዱን እንዳያካሂድ ሲወሰንበት የተሰጠውን የንግድ ሥራ ፈቃድ በሥራ ላይ ያለማዋል፤
7. የአድራሻ ለውጥ ሲያደርግ ለውጡን በአንድ ወር ጊዜ ውሰጥ ለመዝጋቢው መሥሪያ ቤት የማሳወቅ፤
8. አክስዮን ማህበር እና ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር ከሆነ በየበጀት ዓመቱ በኦዲተር ሂሳቡን የማስመርመር እና ሪፖርት የማቅረብ፤
9. ስለንግዱ በሚመለከታቸው አካላት የሚጠየቀውን ማንኛውንም መረጃ የመስጠት፤
10. በተመሳሳይ ደረጃ ግብይት ያለመፈፀም፤
11. አግባብ ባለው ባለስልጣን የተወሰዱ አስተዳደራዊ እርምጃዎችን እና በሕግ የተደነገጉ ሌሎች ግዴታዎችን የማክበር፡፡

በጠፍ ሰብል ላይ የተስተዋለውን እጥረትና የዋጋ ጭማር ለማረጋጋት የዞኑ አርብቶአደር ዪኒዬን የጠፍ ምርት ለየሸማቾች በተመጣጣኝ ዋጋ በአማራጭነት ማቅረብ ጀምሯል። አድራሻ:_ከጅንካ ቀይ መስቀል...
31/03/2020

በጠፍ ሰብል ላይ የተስተዋለውን እጥረትና የዋጋ ጭማር ለማረጋጋት የዞኑ አርብቶአደር ዪኒዬን የጠፍ ምርት ለየሸማቾች በተመጣጣኝ ዋጋ በአማራጭነት ማቅረብ ጀምሯል።
አድራሻ:_ከጅንካ ቀይ መስቀል/ጽ/ቤት ጀርባ በአ/አ/ዪ ጽ/ቤት

Address

SNNPR South Omo Zone, Jinka Town
Jinka

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when South Omo Zone Trade & Market Development Department posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share