20/08/2026
የኣሪ ዞን ፖሊስ መምሪያ የተጠናቀቀዉን በጀት አመት የሥራ ዕቅድ አፈጻጸም በመገምገም በ2019 በጀት ዓመት የውጤት ተኮር ስራ ዕቅድ ላይ የዉይይት መድረክ አካሄዴ።
ነሐሴ14/ ቀን 2018 ዓ/ም በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን የኣሪ ዞን ፖሊስ መምሪያ የ2018 ዓ.ም የሥራ ዕቅድ አፈጻጸም ግምገማና በ2019 በጀት ዓመት የውጤት ተኮር ስራ ዕቅድ ላይ ተወያይቷል።
በዉይይት መድረኩ ላይ የተገኙት የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ ክቡር አቶ አብራሃም አታ ባደረጉት የመክፈቻ ንግግር ላይባለፈዉ በጀት አመት የዞኑ ፖሊስ የዜጎችን ሠላምና ደህንነት አስተማማኝ በማድረግ ህብረተሰቡ ከወንጀል ስጋት ተላቆ በነፃነት ተንቀሳቅሶ መስራት እንዲችል ምቹ ሁነታ በመፍጠር መላዉ ህዝባችን የልማት ተጠቃሚነት እንዲረጋገጥ ፖሊስ የተጣለበትን ኃላፊነት ተወጥታል ብለዋል ።
የህግ የበላይነት ሰፍኖ የህዝብ ሠላምና ደህንነት የተረጋገጠበትን ከወንጀል ነጻ የሆነ ህብረተሰብ ለመፍጠር እና ወንጀልን አስቀድመው ለመከላከል ህብረተሰቡን በማስተባበር በቅንጂት በመስራት ፣አጋዥ ኃሎችን በማጠናከር ፣ የማህበረሰብ አቀፍ የወንጀል መከላከል ፖሊስ ተቋማትን ማስፋፋት በተጠናከረ መልኩ በቀጣይ በጀት አመት መሰራት እንዳለበት ገልጸዋል።
በመቀጠልም የ2018 ዓ.ም ዕቅድ ክንውን ሪፖርት እና የ2019 ዓ.ም በጀት ዓመት መነሻ ዕቅድ የኣሪ ዞን ፖሊስ መምሪያ ልማት ዕቅድ ዲቪዥን ኃላፊ ኮማንደር ጥላሁን ተስፋዬ አቅርበዋል።
መድረኩን የመሩት የዞኑ ፖሊስ አዛዥ ምክትል ኮማንደር መሰለ ገብሬ እንደገለጹት ፖሊስ ባለፈዉ በጀት አመት ዉስጥ ጠንካራ አፈፃፀም ያስመዘገበበት ብሆንም በቀጣይ በጀት አመት ዉስጥ ጉድለቶችን በመለየት የተሻለ አፈፃፀም ማስመዝገብ ያስፈልጋል ብለዋል።
አክለዉም ፖሊስ ከማህበረሰቡ ጋር በጋራ በመሥራት ወንጀልን አስቀድሞ ለመከላከል፣ የሰላምና ጸጥታ ደህንነትን አስተማማኝ ለማድረግ እንዲሁም የሕብረተሰቡን ተሳትፎ ከፍ ለማድረግ ከባለድርሻ አካላትና የአጋዥ ኃይሎችን በማደራጀት የማህበረሰብ አቀፍ ወንጀል መከላከል ትምህሪቶችን በማጠናከር እንደምሰራ ጠቁመዋል።
በመጨረሻም በ2018 በጀት ዓመት የተስተዋሉ ጉድለቶችንና ስኬቶችን በመለየት በቀጣይ የ2019ዓ/ም ዕቅድ ላይ የትኩረት አካል በማድረግ መስራት እንደሚገባም የዉይይቱ ተሳታፊዎች አስገንዝበዋል።
በመድረኩም የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸምና የ2019 ዓ.ም መነሻ ዕቅድ ላይ በመወያየት ቀጣይ የመፍትሔ አቅጣጫ በዞኑ ዋና አስተዳደር፣በዞኑ ሠላምና ፀጥታ መምሪያ ኃላፍና በዞኑ ፖሊስ አዛዥ ተቀምጦ ዉይይቱ ተጠናቋል።
የኣሪ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ክቡር አቶ አብራሃም አታ ፣የኣሪ ዞን ምክር ቤት ህግና ፍትህ መልካም አስተዳደር ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ወ/ሮ ሊደት መኮንን ፣የኣሪ ዞን ሠላምና ፀጥታ መምሪያ ኃላፊ አቶ ማታዶ በርብ ፣የዞን ፖሊስ መምሪያ ማናጅመንት አባላት ፣የከተማና የወረዳ ፖሊስ አዛዦችና ማናጅመንት አካላት በመድረኩ ተሳትፈዋል ሲል የኣሪ ዞን ፖሊስ መምሪያ በገፁ ዘግቧል።