የደ/ኢ/ክ/ ወጣቶች ጉዳይና በጎ ፍቃድ አገልግሎት ኮምሽን

  • Home
  • Ethiopia
  • Jinka
  • የደ/ኢ/ክ/ ወጣቶች ጉዳይና በጎ ፍቃድ አገልግሎት ኮምሽን

የደ/ኢ/ክ/ ወጣቶች ጉዳይና በጎ ፍቃድ አገልግሎት ኮምሽን የተከበራችሁ የፔጃችን ተከታዮች አዲስ በተዋቀረዉ ኮምሽናችን ስም የፌስቡክ ፔጃችን እያስተካከልን ስለሆነ በትዕግስት እንድትጠብቁን እያሳሰብን የሚለቀቀዉን መረጃ ላይክ ሼር በማድረግ ወቅታዊ መረጃ ያግኙ፡፡

Our page is providing the recent information about South Ethiopia Region Youth and Sport Works, Events and different activities for the followers

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የክረምት ወራት የወጣቶች በጎ ፈቃድ አገልግሎት ኮማንድ  ፖስት  የ6ኛ ሳምንት የዕቅድ ክንውን ሪፖርት ገምግሟል።በግምገማው  ወቅት ጠንካራ ውጤቶችን፣ ክፍተቶችንና ቀጣ...
17/08/2026

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የክረምት ወራት የወጣቶች በጎ ፈቃድ አገልግሎት ኮማንድ ፖስት የ6ኛ ሳምንት የዕቅድ ክንውን ሪፖርት ገምግሟል።

በግምገማው ወቅት ጠንካራ ውጤቶችን፣ ክፍተቶችንና ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎችን በግልጽ አስቀምጧል።

በ6ኛው ሳምንት የክልሉ አጠቃላይ አፈጻጸም ሲታይ፣ የተሳታፊዎች አፈጻጸም 70.93%፣ የተጠቃሚዎች 86.49% እና የዳነ ገንዘብ 45.28% ደርሷል።

ይህ የበጎ ፈቃድ አገልግሎቱ ለህብረተሰቡ ዘረፈ ብዙ ጠቀሜታ እየሰጠ መሆኑን የሚያመላክት ቢሆንም፣ የተሳትፎንና የሥራ ውጤትን በተገቢው የገንዘብ ዋጋ መመዝገብ አሁንም ትኩረት እንደሚሻ ያመላክታል።

በእስካሁኑ ሂደት በአረንጓዴ አሻራ ፣በጤና፣በስነ-ልቦና ድጋፍና ምክር፣ በተዋልዶ ጤና፣ የድልድይና የፍሳሽ መውረጃ ሥራዎች፣ የመንገድ ደህንነት፣ የአየር ንብረት ግንዛቤ፣ የሕይወት ክህሎትና የሙያ በጎ ፈቃድ ዘርፎች ጠንካራ አፈጻጸም አሳይተዋል።

ከ84 የውጤት አመላካቾች ውስጥ 13 ከፍተኛ፣ 42 መካከለኛ እና 29 የሚሆኑት ደግሞ ዝቅተኛ አፈጻጸም ውስጥ የሚገኙ መሆኑ በግምገማው ወቅት ተነስተዋል።

በተለይ ከ50% በታች የሆኑ የውጤት አመላካቾች የተለየ ድጋፍና ክትትል የሚፈልጉ መሆናቸው በግምገማ ወቅት ተለይቷል።

በዋናነት የምግብና አልባሳት ድጋፍ ፣ማዕድ ማጋራት ፣የአደባባይና መናፈሻ ማስዋብ፣የጽዳት አገልግሎት ፣የወጣት ማዕከላት እድሳት እና የሰዎች ዝውውር መከላከያ አደረጃጀት ቀጣይ ትኩረት የሚፈልጉ የውጤት አመልካቾች ናቸው።

በተጨማሪም የተገነቡና የታደሱ ቤቶች የXY ኮርዲኔት መረጃ አለመሟላት፣አንዳንድ መዋቅሮች ሪፖርታቸውን በአብይና ቴክኒክ ኮሚቴ ሳይገመግሙ መላካቸው እና የፌዴራል ደረጃ የቤት ግንባታ መረጃ ለክልሉ በበቂ ሁኔታ አለመድረሱ ክፍተቶች ሆነው በግምገማው ወቅት ተነስተዋል።

ቀጣዩ የአፈጻጸም ወቅት ዝቅተኛ ውጤት ያላቸውን መስኮች በተለየ ክትትል ማሻሻል፣ መካከለኛ ውጤቶችን ወደ ከፍተኛ ማሻገር እና ከፍተኛ ውጤቶችን ማስቀጠል ላይ ትኩረት እንደሚደረግም ተብራርተዋል።

በተለይ ምግብና አልባሳት ድጋፍ፣ ማዕድ ማጋራት፣ አደባባይና መናፈሻ ማስዋብ፣ ጽዳት፣ የሰዎች ዝውውር መከላከያ ስራ፣ የትራፊክ ምልክት/ዜብራ፣ የወጣት ማዕከል እድሳትና ግብዓት እና የመማሪያ ግብአቶች ድጋፍ በቀጣይ ልዩ ድጋፍና ክትትል የሚፈልጉ ዋና የትኩረት መስኮች ናቸው።

እንዲሁም በወጣቶች የቴክኖሎጂና ክህሎት ልማት ላይ ትኩረት መጨመር፣ የኢትዮ-ኮደርስና የሙያ አገልግሎቶችን ማጠናከር እና ለወጣቶች የሥራ አቅም ግንባታ ልዩ በጀትና ክትትል ማድረግ እንደሚገባ ተገልፆል።

የ5ኛ ሳምንት የክረምት ወራት የበጎ ፈቃድ ዕቅድ ክንውን በኮማንድ ፖስት ተገመገመ።የበጎ ፈቃድ ተግባር  አፈፃፀም ማጠናከር፣ የታዩ ክፍተቶችን በፍጥነት ማረምና ተጨባጭ ማህበራዊ ተፅዕኖን ማሳ...
10/08/2026

የ5ኛ ሳምንት የክረምት ወራት የበጎ ፈቃድ ዕቅድ ክንውን በኮማንድ ፖስት ተገመገመ።
የበጎ ፈቃድ ተግባር አፈፃፀም ማጠናከር፣ የታዩ ክፍተቶችን በፍጥነት ማረምና ተጨባጭ ማህበራዊ ተፅዕኖን ማሳየት በግመገማው ትኩረት መደረጉም ተገልፆል።

ጂንካ ነሐሴ 4/2018 ዓ/ም የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ወጣቶች ጉዳይና በጎ ፈቃድ ኮሚሽን የ2018/19 ዓ.ም የክረምት ወራት በጎ ፈቃድ አገልግሎት የ5ኛ ሳምንት የዞኖችና ሪጂዮ ፖሊስ ከተሞችን የዕቅድ ክንውን ሪፖርት በኮማንድ ፖስት ገመገመ አድርጓል።

ግምገማው በዞኖችና በሪጂዮ ፖሊስ ከተሞች እየተከናወኑ ያሉ 18 የበጎ ፈቃድ መስኮችን የዕቅድ ክንውን፣ የሪፖርት ጥራት፣ የመረጃ ሙሉነት፣ የተጠቃሚ ተደራሽነትና የተግባር አፈፃፀምን መነሻ በማድረግ ተካሂዷል።

በግምገማው ወቅት በአጠቃላይ በ18ቱም የበጎ ፈቃድ መስኮች የተጀመሩ ተግባራት ወደ ተሻለ የአፈፃፀም ደረጃ መምጣታቸውና በተጨባጭ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑ በጥንካሬ ተገምግሟል።

በተለይም በአረንጓዴ አሻራ፣ በጤና አገልግሎት፣ በፋይዳ ማታወቂያ፣ በመንገድ ትራፍክና ደህንነት፣ በኢትዮ ኮደርሶ፣ በቤት ግንባታና ዕድሳት፥በመሰረተ ልማት እና በትውልድ ግንባታ የተሻለ እንቅስቃሴ መመዝገቡ ተጠቁሟል።

ከዚህ በተጨማሪ መዋቅሮች ሪፖርቶችን ተስተካክሎ በወረደው ፎርማትና በተቀመጠው የጊዜ ሰሌዳ ማቅረብ መቻላቸው በአዎንታዊ ጎን ተነስተዋል።

በሌላ በኩል ግን በአፈፃፀሙ ላይ የታዩ ክፍተቶችም ተለይተዋል። በአንዳንድ ሪፖርቶች ዕቅድና ክንውን በግልጽ አለመለየት፣ በቂ ማስረጃ ያልተደገፈ መረጃ ማቅረብ፣ ሪፖርቶች በአብይና ቴክኒክ ኮሚቴ ሳይገመገሙ መላክ እና የተሳታፊዎችን የወንድና የሴት ቁጥር በተናጠል አለማሳየት እንደ ክፍተት ተጠቅሰዋል።

በአንዳንድ መዋቅሮች የታየው ከ40 በመቶ በታች የሆኑ አፈፃፀሞች ፈጣን የማሻሻያ እርምጃ የሚፈልጉ ሲሆን፣ ከ20 በመቶ በታች የሆኑ አፈፃፀሞች ደግሞ በአስቸኳይ ተለይተው እንዲሻሻሉ አቅጣጫ ተሰጥቷል።

ከዚህ ጋር ተያይዞ በቀጣይ ሳምንት ሁሉም መዋቅሮችና ሪጂዮ ፖሊስ ከተሞች የቤቶችን የXY ኮርዲኔት መረጃ በሙሉ ማቅረብ እንደሚገባቸው በግምገማው ወቅት ተገልጿል።

በአንዳንድ ዞኖች ከቤት ግንባታ ጋር በተያያዘ ከተቀመጠው የአሰራር መመሪያ ውጪ የጭቃ ቤቶችን መገንባት መቆም እንደሚገባ፥ በሁሉም የውጤት አመልካቾች ላይ ተመጣጣኝ ትኩረት እንዲሰጥ እና ሁሉም ሪፖርቶች በአብይና ቴክኒክ ኮሚቴ ከተገመገሙና ከፀደቁ በኋላ ብቻ እንዲላኩ አቅጣጫ ተቀምጧል።

በአጠቃላይ የ5ኛ ሳምንት ግምገማ የበጎ ፈቃድ አገልግሎቱ አፈፃፀም እየተጠናከረ መምጣቱን ቢያሳይም፣ ዝቅተኛ አፈፃፀሞችን በፍጥነት ማሻሻል፣ የሪፖርት ጥራትንና ተዓማኒነትን ማሳደግ፣ የተጠቃሚ ተፅዕኖን በማስረጃ ማሳየትና 18ቱንም የበጎ ፈቃድ መስኮች በተመጣጣኝ ሁኔታ መሸፈን የቀጣዩ ሳምንት ዋና ትኩረቶች እንዲሆኑ አቅጣጫ ተሰጥቷል።

የ2018/19 ዓ.ም የክረምት ወራት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት የእስካሁኑ የዞኖች የዕቅድ ክንውን ሪፖርት በኮሚሽኑ ደረጃ ተገምግሟል።ጂንካ ሐምሌ 27/2018 ዓ/ም የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ወጣቶ...
03/08/2026

የ2018/19 ዓ.ም የክረምት ወራት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት የእስካሁኑ የዞኖች የዕቅድ ክንውን ሪፖርት በኮሚሽኑ ደረጃ ተገምግሟል።

ጂንካ ሐምሌ 27/2018 ዓ/ም የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ወጣቶች ጉዳይና በጎ ፈቃድ አገልግሎት ኮሚሽን የ2018/19 ዓ.ም የክረምት ወራት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት የእስካሁኑን የዞኖች የዕቅድ ክንውን ሪፖርትን በተመለከተ በኮሚሽኑ ደረጃ ገምገማ አድርጓል።

የግምገማው ዓላማ በዞኖች እየተከናወኑ ያሉ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ስራዎች የደረሱበትን አፈጻጸም መለየት፣ የሪፖርት ጥራትን መፈተሽ፣ ጥንካሬዎችን ማበረታታት እና የተስተዋሉ ክፍተቶችን በመለየት በቀጣይ አፈጻጸም ተሻሽሎ እንድቀርቡ ማድረግ ነው።

በግምገማው ወቅት አንዳንድ ዞኖች ከተጨባጭ ክንውን ጋር የማይጣጣም የተጋሸበ ቁጥራዊ መረጃ ማቅረባቸው፣ የተጠቃሚዎች ቁጥርና የዳነ ገንዘብ መጠን የተጋነነ መሆኑ፣ አንዳንድ ዞኖች ለሪፖርቱ የተዘጋጀውን ፎርማት አለመከተል፣ ሪፖርቶችን በተቀመጠው የጊዜ ሰሌዳ አለማቅረብ እንደ ዋና ክፍተት ተነስተዋል።

በሌላ በኩል በግምገማው ወቅት የታዩ ጥንካሬዎች እጅግ አበረታች መሆናቸው ተንጸባርቋል።

ዞኖች በ18 የስምሪት ዘርፎች ትኩረት በመስጠት የማህበረሰባቸውን ፍላጎት የሚመልሱ ተጨባጭ ስራዎችን እያከናወኑ መሆናቸው፣ በመሬት ላይ የሚታዩ ውጤቶች መመዝገባቸው፣ የወጣቶች ተሳትፎ እያደገ መምጣቱ እና የአብይና የቴክኒክ ኮሚቴዎች ለፕሮግራሙ ትኩረት ሰጥተው በቅርብ ክትትል እያደረጉ መሆናቸው እንደ ዋና ጥንካሬዎች ተገምግመዋል።

በመድረኩ የተሰጠው አቅጣጫ በቀጣይ የሚቀርቡ ሪፖርቶች በተጨባጭ መረጃ ላይ ብቻ እንዲመሰረቱ፣ ሁሉም ዞኖች የተቀመጠውን ፎርማት እና የጊዜ ሰሌዳ በጥብቅ እንዲከተሉ፣ ሪፖርቶች ከመላካቸው በፊት በአብይና በቴክኒክ ኮሚቴ በቂ ግምገማ እንዲደረግባቸው እና የመረጃ ጥራት፣ ተዓማኒነትና ወቅታዊነት እንዲረጋገጥ አፅንኦት ተሰጥቷል።

ኮሚሽኑም በቀጣይ ወቅቶች የክትትልና የድጋፍ ስራዎችን በማጠናከር፣ የመረጃ አያያዝና የሪፖርት ዝግጅት አቅምን በማሳደግ የ2018/19 ዓ.ም የክረምት ወራት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ዕቅድ የተቀመጡ ግቦችን በተሻለ ውጤት እንዲያሳካ ከሁሉም አመራሮችና ፈጻሚ አካላት የላቀ ትኩረትና ተጠያቂነት እንደሚጠበቅ አሳስቧል።

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ወጣቶች በአንድ ጀምበር 21 ሚሊዮን 350 ሺህ ችግኞችን ለመትከልና የወሰን ተሻጋሪ በጎ ፈቃድ አገልግሎቶችን ለማስፈጸም ቅድመ ዝግጅት ላይ መሆናቸው ተገለፀ።ጂንካ ሐም...
01/08/2026

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ወጣቶች በአንድ ጀምበር 21 ሚሊዮን 350 ሺህ ችግኞችን ለመትከልና የወሰን ተሻጋሪ በጎ ፈቃድ አገልግሎቶችን ለማስፈጸም ቅድመ ዝግጅት ላይ መሆናቸው ተገለፀ።

ጂንካ ሐምሌ 25/2018 ዓ.ም
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ወጣቶች በአንድ ጀምበር 21 ሚልዮን 350 ሺህ ችግኞችን ለመትከል ያቀደውን መርሃ ግብር ከግብ ለማድረስ የሚያስችል ውይይት በበይነ መረብ አካሄዱ።

በዕቅዱ ቅድመ ዝግጅት ዙሪያ የተደረገው ይህ ውይይት በዞኖችና በሪጂዮ ፖሊስ ከተሞች የበጎ ፈቃድ አገልግሎት የጽ/ቤት ሃላፊዎች ተሳትፎ በዙም (Zoom) መድረክ ተካሂዶ ፍሬያማ መግባባት ላይ ተደርሷል።

ውይይቱን በበላይነት የመሩት የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ወጣቶች ጉዳይና በጎ ፈቃድ አገልግሎት ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ ማርቆስ ማቴዎስ እንደገለጹት፤ ይህ የታቀደው የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ክልላዊ አረንጓዴ አሻራን ከግብ ለማሳካት የሚደረግ ታሪካዊ እንቅስቃሴ ነው ሲሉ አስረድተዋል።

በመሆኑም ለዕቅዱ ስኬታማነት ሁሉም አደረጃጀቶችና ባለድርሻ አካላት በባለቤትነት ስሜትና በትኩረት ሊሰሩ ይገባል ሲሉም ገልፀዋል።

በክልሉ በሁሉም ዞኖችና ሪጂዮ ፖሊስ ከተሞች የተቀናጀ አሰራር በመዘርጋት 21 ሚሊዮን 350 ሺህ ችግኞችን በአንድ ቀን ጀምበር ለመትከል የሚያስችል የሰው ሃይል ንቅናቄ፣ የቁሳቁስና የጉርጓድ ቁፋሮ ዝግጅት ቀድሞ ማለቅ እንደሚገባም ተነስተዋል።

በሌላ በኩል የወሰን ተሻጋሪ በጎ ፈቃድ አገልግሎት: ወጣቶች በማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና አካባቢ ጥበቃ ስራዎች ላይ ያላቸውን ተሳትፎ በማጠናከር ከአንድ አካባቢ አልፈው በጋራ ልማት ላይ የጋራ እጅ እንዲኖራቸው ለማድረግና ሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከት ወሳኝ መሆኑም ተገልፆል።

የውይይቱ ተሳታፊዎች በበኩላቸው በክልሉ ደረጃ የታቀደውን የአንድ ጀምበር የችግኝ ተከላ ዕቅድ ከግቡ ለማድረስ ከወዲሁ የዝግጅት ስራዎችን በማጠናቀቅ፣ ህብረተሰቡንና ወጣቱን በማቀናጀት ዕቅዱን ለማሳካት እንደሚሰሩ ገልፀዋል።

ወሰን ተሻጋሪ ወጣቶች በጎፋ ዞን የአረንጓዴ አሻራን፣ የብሔራዊ አንድነትንና የቱሪዝም ልማትን አጎለበቱሐምሌ 7/2018 ዓ.ምከተለያዩ ሀገሪቱ ክልሎች የተወጣጡ ወሰን ተሻጋሪ ወጣቶች በጎፋ ዞን...
14/07/2026

ወሰን ተሻጋሪ ወጣቶች በጎፋ ዞን የአረንጓዴ አሻራን፣ የብሔራዊ አንድነትንና የቱሪዝም ልማትን አጎለበቱ

ሐምሌ 7/2018 ዓ.ም

ከተለያዩ ሀገሪቱ ክልሎች የተወጣጡ ወሰን ተሻጋሪ ወጣቶች በጎፋ ዞን በቡልቂ ከተማ አስተዳደር በመገኘት የአረንጓዴ አሻራ እና ብሔራዊ አንድነትን በማጠናከር የቱሪዝም ልማት ስራዎችን ምልከታ አድርገዋል።

ከመላው ኢትዮጵያ የተውጣጡ ወሰን ተሻጋሪ የወጣቶች በጎ ፈቃድ አገልግሎት ተሳታፊዎች በጎፋ ዞን ቡልቂ ከተማ በመገኘት የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ በማከናወን፣ የአካባቢውን የቱሪዝም መስህቦች በመጎብኘትና ከማህበረሰቡ ጋር የባህልና የልምድ ልውውጥ በማድረግ በጎነት ከድንበር በላይ የሚያስተሳስር እሴት መሆኑን በተግባር አሳይተዋል።

የመርሃ ግብሩ ዋና ዓላማ የአረንጓዴ ልማትን ማፋጠን፣ በወጣቶች መካከል የብሔራዊ አንድነትን ማጠናከር፣ የባህልና የልምድ ልውውጥን ማስፋፋት እንዲሁም የጎፋ ዞንን ተፈጥሯዊና ታሪካዊ የቱሪዝም ሀብቶች ለሀገር አቀፍ ታዳሚ ማስተዋወቅ መሆኑ ተገልጿል።

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ወጣቶችና በጎ ፍቃድ አገልግሎት ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ ማርቆስ ማትዮስ በበኩላቸው፣ የወጣቶቹ ጉዞ ችግኝ ከመትከል በላይ የኢትዮጵያን የአብሮነት ባህል፣ የሰላም እሴትና የመተሳሰብ መንፈስ በተግባር ለማሳየት የታለመ መሆኑን ገልጸዋል።

በቆይታቸውም ችግኝ ተከላ፣ የአቅመ ደካሞች ድጋፍ፣ የቤት ግንባታና ሌሎች ማህበራዊ ተግባራትን በመፈጸም የበጎነት ባህልን እንደሚያጠናክሩ አስረድተዋል።

የጎፋ ዞን የመንግስት ረዳት ተጠሪ አቶ ይሁን ደምሴ እንደገለጹት፣ ወሰን ተሻጋሪ የወጣቶች በጎ ፈቃድ አገልግሎት ወጣቶችን በበጎ ተግባር ከማሳተፍ ባለፈ የባህል፣ የቋንቋና የልምድ ልውውጥን በማጎልበት ብሔራዊ አንድነትን የሚያጠናክር እና ለሌሎች ወጣቶች አርአያ የሚሆን ንቅናቄ መሆኑን ገልጸዋል።

የጎፋ ዞን ወጣቶችና በጎ አገልግሎት ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ብርሃኑ ደቻሳ በበኩላቸው፣ ከመላው ሀገሪቱ ለበጎ ተግባር የመጡ ወጣቶችን በጎፋ ዞን በደስታ መቀበላቸውን ገልጸው፣ በጋራ መስራትና በጎነትን ማስፋፋት ለሀገር ከፍታ መሠረት መሆኑን ገልጸዋል።

የቡልቂ ከተማ ከንቲባ ኢንጂነር ተመስገን ጣሰው በበኩላቸው፣ ወጣቶቹ የጎፋን ታሪክ፣ ባህልና የቱሪዝም ሀብት በመጎብኘት የአካባቢውን እሴቶች እንዲያውቁ እና የራሳቸውን ልምድ እንዲያካፍሉ የተፈጠረው እድል በሀገራዊ መተሳሰብ ግንባታ ትልቅ ድርሻ እንዳለው ገልጸዋል።

ተሳታፊ ወጣቶችም በጎፋ ዞን ያገኙት ሞቅ ያለ አቀባበል፣ የህዝቡ እንግዳ ተቀባይነትና የባህል ብዝሃነት እጅግ እንዳስደሰታቸው ገልጸው፣ የተከሉት ችግኝ ለአረንጓዴ ልማት ብቻ ሳይሆን የሰላም፣ የወንድማማችነትና የአንድነት ዘላቂ አሻራ መሆኑን ተናግረዋል።

ወጣቶቹ በቆይታቸው የጎፋ ዞን የቱሪዝም መስህቦችን በመጎብኘት የአካባቢውን ታሪክ፣ ባህልና ተፈጥሯዊ ሀብቶች ከመተዋወቅ ባሻገር የጎፋን የቱሪዝም አቅም ለመላው ሀገር ለማስተዋወቅ ጉልህ አስተዋጽኦ አበርክተዋል።

በጎፋ ዞን የተከናወነው ይህ ወሰን ተሻጋሪ የወጣቶች በጎ ፈቃድ አገልግሎት፣ አረንጓዴ ልማትን፣ ብሔራዊ አንድነትን፣ የባህል ልውውጥንና የቱሪዝም ልማትን በአንድ ማዕቀፍ ያገናኘ ተምሳሌታዊ ተግባር ሆኖ ተገልጿል።

የክልሉ የክረምት ወራት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ቴክኒክ ኮሚቴ የእስካሁን ተግባራት አፈፃፀምን በበይነ መረብ ገምግሟል ሐምሌ 03/2018 ዓ.ም የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የክረምት ወራት የበጎ ፈ...
10/07/2026

የክልሉ የክረምት ወራት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ቴክኒክ ኮሚቴ የእስካሁን ተግባራት አፈፃፀምን በበይነ መረብ ገምግሟል

ሐምሌ 03/2018 ዓ.ም

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የክረምት ወራት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ቴክኒክ ኮሚቴ የቅድመ ዝግጅት ስራዎች ማጠቃለያና የተግባር ምዕራፍ የእስካሁን አፈፃፀምን በበይነ መረብ ገምግሟል።

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የ 2018 የክረምት ወራት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ማስጀመሪያ ክልል አቀፍ ንቅናቄ በጋሞ ዞን ምዕራብ አባያ ወረዳ ተካሂዶ ወደ ስራ መገባቱ ይታወቃል።

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊና የቴክኒክ ኮሚቴዉ ሰብሳቢ አቶ ንጋቱ ዳንሳ የክረምት ወራት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት በሀገር ደረጃ ባህል እየሆነ መምጣቱን ጠቅሰዋል።

"በጎነት ለኢትዮጵያ ከፍታ" በሚል መሪ ቃል የ 2018 የክረምት ወራት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ክልል አቀፍ ማስጀመሪያ በከፍተኛ ድምቀት ተካሂዶ ወደ ስራ መገባቱን አስታዉሰዋል።

ባለፉት ስምንት አመታት በክረምት ወራት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት በተሰራው ስራ በርካታ ዜጎችን ተጠቃሚ ያደረጉ ዉጤታማ ስራዎች መሠራታቸዉን አቶ ንጋቱ ጠቁመዋል።

በክልሉ ሰኔ 22 የተጀመረውን የክረምት ወራት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት እስከ መስከረም/2019 የመጨረሻ ሳምንት ድረስ በከፍተኛ ትኩረት ማከናወን እንደሚገባም አሳስበዋል።

በትምህርት፣ ጤና፣ የቤት ግንባታ፣ ወሰን ተሻጋሪ የወጣቶች የበጎ ፈቃድ አገልግሎትና ሌሎች ተግባራትን የፓርቲ ዲስፕሊን ባከበረና የተቀመጡ አቅጣጫዎችን ባስጠበቀ መልኩ መተግበር ይገባል ብለዋል።

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት የዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ዘርፍ ኃላፊና የቴክኒክ ኮሚቴው ም/ሰብሳቢ አቶ ሳጌ ሻምባ በተያዘው ዓመት በቂ ዝግጅት ተደርጎ ወደ ስራ መገባቱን ጠቅሰዋል።

በሂደቱ የሚስተዋሉ ችግሮችን በተደራጀና በተናበበ መንገድ በመፍታት በክረምቱ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት የተቀመጡ ዕቅዶችን ጥራትና ተደራሽነት ጠብቆ ማሳካት እንደሚገባ አስገንዝበዋል።

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ኮሚሽን ኮሚሽነርና የቴክኒክ ኮሚቴዉ ፀሐፊ ማርቆስ ማቴዎስ ክልላዊ የማብሰሪያ መርሃ-ግብሩን ተከትሎ ወደ ተግባር ምዕራፍ መገባቱን አመልክተዋል።

እስካሁን በተሰሩ ስራዎች 255 ዩኒት የደም ልገሳን ጨምሮ በችግኝ ተከላ፣ የቤት ግንባታ፣ የከተማ ዉበትና ፅዳት እንዲሁም በሌሎች 18 የበጎ ፈቃድ ዘርፎች በርካታ ተግባራት መከናወናቸውን ገልፀዋል።

በየዓመቱ በክረምት ወራት የሚከናወነው የበጎ ፈቃድ አገልግሎት፤ ወጣቶችንና ልዩ ልዩ የኅብረተሰብ ክፍሎችን በማስተባበር በርካታ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮችን በመቅረፍ ላይ እንደሚገኝ በዉይይቱ ተነስቷል።

በመዋቅሮች መካከል የሚስተዋለውን የአፈፃፀም ልዩነት በፍጥነት በማስተካከል በቀጣይ ጊዜያት ተግባሩን ዉጤታማ አድርጎ መምራት እንደሚገባ አፅኖት ተሰጥቷል።

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በዘንድሮው የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ከ 3 ነጥብ 5 ሚሊዮን በላይ ዜጎችን ተሳታፊ የሚያደርጉ ተግባራት እንደሚከናወኑ ተመላክቷል።

በዉይይቱ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የክረምት ወራት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ቴክኒክ ኮሚቴ አባላት እና የዞኖችና ሪጂዮ ፖሊሲ ከተሞች የቴክኒክ ኮሚቴ አባላት ተሳታፊ ሆነዋል።

የፌዴራል ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ለደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ወጣቶች ጉዳይና በጎ ፈቃድ አገልግሎት ኮሚሽን የላፕቶፕ ድጋፍ አደረገ።አርባምንጭ ሰኔ 16/2018 ድጋፉ የኮሚሽኑን የዕለት ...
23/06/2026

የፌዴራል ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ለደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ወጣቶች ጉዳይና በጎ ፈቃድ አገልግሎት ኮሚሽን የላፕቶፕ ድጋፍ አደረገ።

አርባምንጭ ሰኔ 16/2018 ድጋፉ የኮሚሽኑን የዕለት ተዕለት የአሰራር ሂደት በቴክኖሎጂ ለማዘመን እና ውጤታማነትን ለማሳደግ ወሳኝ ሚና እንዳለው የሴቶችና ማህበራዊ ሚኒስቴር ተወካይ አቶ ሀብታሙ ከበደ በርክብክቡ ወቅት ተናግሯል።

አቶ ሀብታሙ አክለውም እንደገለፁት ከሆነ ድጋፉ የዘርፉን መረጃዎች በዲጂታል መንገድ ለመምራት እና ሪፖርቲንግ ስርአቱን ለማዘመን ወሳኝ ሚና ይኖረዋል ሲሉም ገልፀዋል።

ድጋፉ ለኮሚሽኑ የዘመኑ የቴክኖሎጂ መሳሪያዎች ፍላጎት መፍትሄ የሚሰጥ መሆኑንም ተናግረዋል።

የክልሉን የወጣቶች ዘርፍ ስራዎችን በዘመናዊ አሰራር ለማገዝ የሚደረገው ድጋፍ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም የሚኒስቴር መ/ቤቱ ተወካይ አቶ ሀብታሙ ከበደ አረጋግጧል።

የክልሉ ወጣቶች ጉዳይና በጎ ፈቃድ አገልግሎት ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ ማርቆስ ማቴዎስ ድጋፉ ለስራ ቅልጥፍናና ለወቅታዊ ሪፖርቶች ተአማኒነት ጉልህ አስተዋጽኦ እንዳለው ገልጸዋል።

አያይዘውም፣ የቴክኖሎጂ ግብዓቶቹ የኮሚሽኑን የመረጃ አያያዝ እና የአገልግሎት አሰጣጥ ሂደቱን በማዘመን ረገድ የላቀ ፋይዳ እንዳላው አቶ ማርቆስ ማቴዎስ ገልፀው ድጋፉ ለተግባራዊ ስራችን እጅግ ወሳኝ መሆኑን አስረድተዋል።

ኮሚሽነሩ አቶ ማርቆስ ማቴዎስ፣ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ላደረገው ድጋፍ ልባዊ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

“በጎነት የህሊና ዕርካታ የሚሰጥ የኢትዮጵያውያን የቆየ እሴት ነው” ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ ሰኔ 16/2018 ዓ.ም “በጎነት ለኢትዮጵያ ከፍታ” በሚል መሪ ቃል የ2018 ዓ.ም የ...
23/06/2026

“በጎነት የህሊና ዕርካታ የሚሰጥ የኢትዮጵያውያን የቆየ እሴት ነው” ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ

ሰኔ 16/2018 ዓ.ም

“በጎነት ለኢትዮጵያ ከፍታ” በሚል መሪ ቃል የ2018 ዓ.ም የበጋ ወራት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ማጠቃለያና የክረምት ወራት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ማስጀመሪያ ክልል አቀፍ የንቅናቄ መድረክ በጋሞ ዞን ምዕራብ አባያ ወረዳ ቆላ ሙልአቶ ቀበሌ ተካሂዷል።

በመድረኩ ላይ የተገኙት የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ እንደገለጹት፣ በጎነት የህሊና ዕርካታ የሚሰጥ እና ለዘመናት በኢትዮጵያውያን ዘንድ የቆየ እሴት ነው ብለዋል።

ባለፉት ስምንት ዓመታት ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ በመደመር እሳቤ በመመራት ተበታትኖ የነበረውን የበጎነት ባህል በማሰባሰብ በሀገር አቀፍ ደረጃ ውጤታማ ሥራ መሰራታቸውን ርዕሰ መስተዳድሩ ገልጸዋል።

የበጎነት ሥራ ወቅታዊ ዘመቻ ብቻ ሳይሆን ዓመቱን ሙሉ ሊቀጥል የሚገባ ባህል መሆኑን የጠቀሱት ርዕሰ መስተዳድሩ የጠቅላይ ሚኒስትሩን ፈለግ በመከተል በበጋም ሆነ በክረምት ወቅት በመሥራት የተሻለ ውጤት ማስመዝገብ እንደሚገባ ገልጸዋል።

በዘንድሮው የክረምት ወራት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ከቤት ግንባታና ጥገና፣ ደም ልገሳ፣ አካባቢ ጥበቃ እና ሌሎች ማህበራዊ ተግባራት ባሻገር ከ5 ሺህ በላይ ቤቶችን በብሎኬት በጥራት ለመገንባት የአፈር ጡብ በማምረት በሁሉም ከተሞችና የገጠር አካባቢዎች የተደራጀ ሥራ እንደሚከናወን ገልጸዋል።

በተለይም በክልሉ ለመጀመሪያ ጊዜ የአፈር ጡብ ቴክኖሎጂን በመጠቀም የሚገነቡ ቤቶች በአንድ ወር ውስጥ ተጠናቀው ለተጠቃሚዎች እንደሚተላለፉ አስታውቀዋል።

የክልሉ ብልጽግና ፓርቲ ጽሕፈት ቤት ኃላፊና የክልሉ በጎ ፈቃድ አገልግሎት አብይ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ገብረመስቀል ጫላ በበኩላቸው፣ የ2018 ዓ.ም የክረምት ወራት በጎ ፈቃድ አገልግሎት እሳቤ ሰው ተኮር ከሆነ አስተሳሰብ የመነጨ መሆኑን ገልጸዋል።

በጎ ፈቃድ አገልግሎት ውድ የሆኑትን ጊዜ፣ ገንዘብና ዕውቀት ያለ ምንም ክፍያ ለሌሎች ማካፈል መሆኑን ጠቅሰው፣ እነዚህን ሀብቶች ለሚያስፈልጋቸው ወገኖች ማድረስ የበጎነት እውነተኛ መገለጫ መሆኑን ገልጸዋል።

በጎ ፈቃድ ሥራ የዛሬን ችግር መፍታት ብቻ ሳይሆን ለሚመጣው ትውልድ ሀገርን የማሻገርና የመዋጀት ትውልድ ተሻጋሪ ተግባር መሆኑን የጠቀሱት አቶ ገብረመስቀል የተጠቃሚዎችን የመኖሪያ ቤት ችግር መፍታት ብቻ ሳይሆን እነሱም ወደፊት ሌሎችን እንዲረዱ መልካም ስብዕና ማላበስ የፕሮግራሙ ዋነኛ ግብ መሆኑን ገልጸዋል።
የክልሉ ወጣቶች ጉዳይና በጎ ፈቃድ አገልግሎት ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ ማርቆስ ማቴዎስ የ2018 ዓ.ም የበጎ ፈቃድ አገልግሎት አፈጻጸም ሪፖርት ያቀረቡ ሲሆን፣ በዓመቱ በተከናወኑ የተለያዩ የበጎ ሥራ ተግባራት በርካታ ዜጎችን ተጠቃሚ ማድረጋቸውን ገልጸዋል።

በትምህርት፣ በጤና፣ በአካባቢ ጥበቃ፣ በደም ልገሳ፣ በቤት ግንባታና ጥገና እንዲሁም በሌሎች ማህበራዊ ዘርፎች የተመዘገቡ ውጤቶች የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ለማህበረሰቡ ያለውን ከፍተኛ ፋይዳ እንደሚያሳዩ አመልክተዋል።

የጋሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ዶክተር ደምስ አድማሱ በበኩላቸው በጎ ፈቃድ አገልግሎት የተቸገሩ ዜጎችን ለመደገፍ እና የከተማና የገጠር አካባቢዎችን ለማልማት ወሳኝ አጋጣሚ መሆኑን ገልጸዋል።

በተጨማሪም በዘንድሮው የበጎነት መርሃ ግብር የተጀመረው የገጠር ኮሪደር ልማት አካል የሆኑ መኖሪያ ቤቶች ተገንብተው ለማስረከብ ዝግጁ መሆናቸውን ገልጸዋል።

በመርሃ ግብሩ የክልሉ አመራሮች፣ የዞንና የወረዳ ኃላፊዎች፣ ወጣቶች እና ሌሎች የህብረተሰብ ክፍሎች በሰፊው ተሳትፈው የ2018 ዓ.ም የክረምት ወራት በጎ ፈቃድ አገልግሎትን በይፋ አስጀምረዋል።

በየኔዓለም ሳሙኤል

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የ2018 የክረምት ወራት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ክልል አቀፍ ማስጀመሪያ መድረክ እየተካሄደ ይገኛልምዕራብ ዓባያ፡ ሰኔ 16/2018 ዓ.ም የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ ...
23/06/2026

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የ2018 የክረምት ወራት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ክልል አቀፍ ማስጀመሪያ መድረክ እየተካሄደ ይገኛል

ምዕራብ ዓባያ፡ ሰኔ 16/2018 ዓ.ም የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ በተገኙበት "በጎነት ለኢትዮጵያ ከፍታ" በሚል መሪ ቃል የ2018 የክረምት ወራት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ክልል አቀፍ ማስጀመሪያ መድረክ በዕምራብ አባያ ወረዳ ቆላ ሞልአቶ ቀበሌ እየተካሄደ ይገኛል፡፡

‎የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ፣ የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች የዞንና የወረዳ አመራሮች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ወደ ቀበሌው ሲደርሱ ደማቅ አቀባበል ተደርጎላቸዋል።

የበጎ ፈቃድ ንቅናቄው የአረጋውያን ቤት እድሳት፣ የደም ልገሳ፣ የመረዳዳት፣ የአብሮነትና የአንድነት እሴቶችን ይበልጥ ለማጠናከር ያለመ መሆኑ ተገልጿል።

‎ክልሉ ከ1.1 ሚልዮን ብር በላይ የሚገመት የተለያዩ ቁሳቁሶችን ለድጉና ፋንጎ ወረዳ ወጣቶች ስብዕና ማዕከል ድጋፍ አደረገ። የደቡብ ኢትዮጵያዊ ክልል ወጣቶች ጉዳይና በጎ ፍቃድ አገልግሎት ኮ...
19/06/2026

‎ክልሉ ከ1.1 ሚልዮን ብር በላይ የሚገመት የተለያዩ ቁሳቁሶችን ለድጉና ፋንጎ ወረዳ ወጣቶች ስብዕና ማዕከል ድጋፍ አደረገ።

የደቡብ ኢትዮጵያዊ ክልል ወጣቶች ጉዳይና በጎ ፍቃድ አገልግሎት ኮሚሽን ከ1.1 ሚልዮን ብር በላይ የሚገመት የተለያዩ ቁሳቁሶችን ለድጉና ፋንጎ ወረዳ ወጣቶች ስብዕና ማዕከል ድጋፍ አድርጓል።

‎የደቡብ ኢትዮጵያዊ ክልል ወጣቶች ጉዳይና በጎ ፍቃድ አገልግሎት ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ ማርቆስ ማቴዎስ የተደረገው ድጋፍ ወጣቶች አልባሌ ቦታ ከመዋል ይልቅ በማዕከሉ በሚገኙ የተለያዩ መዝናኛዎችን በመጠቀም እየተዝናኑ ጊዚያቸውን እንዲያሳልፉና ዕውቀት እንዲያገኙ የሚያግዝ ነው ብለዋል።

‎በወረዳው ከፍተኛ ገንዘብ ተመድቦ የወጣቶች ስብዕና ማዕከል ተገንብቶ ማስመረቁን በመገለጽ፥ ይህም መንግስት ለወጣቶች ምን ያህል ትኩረት እንደሚሰጥ ማሳያ ነው ብለዋል።

‎በምረቃው ዕለታ ተገኝተው በገባው ቃል መሠረት ከ1.1 ሚሊዮን ብር በላይ የመገመት የተለያዩ ቁሳቁሶችን የመጀመሪያ ዙር ድጋፍ ማድረጉንም አስታውቀዋል።

‎ማዕከሉ ወጣቶች የሚዝናኑበት ሳይሆን የሚመሩበት እንዲሆን ለማድረግ ድጋፉ ተጠናክሮ ይቀጥላል ያሉት ኮሚሽነሩ፥ ማዕከሉ ለወጣቶች የተሻለ አገልግሎት እንዲሰጥ ቀጣይ የሙያ ስልጠናና የቁሳቁስ ድጋፍ እንደሚደረግም ገልፀዋል።

‎በክልሉ የሚገኙ የወጣቶች ስብዕና ማዕከላት ለወጣቶች ምቹ እንዲሆኑ ጥገና የማድረግ እና የተለያዩ ቁሳቁሶችን ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝም ጠቅሰዋል።

‎የወጣቶች ስብዕና ማዕከላት የራሳቸውን መሆናቸውን ወጣቶች በመገንዘብ የማስዋብና የመጠበቅ ስራ መሰራት እንደሚጠብቅባቸውም አሳስበዋል።

‎ቀጣይ ድጋፍ የሚሹ ስራዎች መኖሩን የጠቆሙት ኮሚሽነሩ፥ ከዞንና ከወረዳው አስተዳደሩ ጋር በመሆን ቀሪ ስራዎችን የማሟላት ስራ እንደሚሰራም ተናግረዋል።

‎የወላይታ ዞን ወጣቶች ጉዳይና በጎ ፍቃድ አገልግሎት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ታምራት ከበደ ክልሉ ለድጉና ፋንጎ ወጣቶች ስብዕና ማዕከል ላበረከተው የተለያዩ ቁሳቁሶች በማድረጉ ምስጋና አቅርበዋል።

‎የተደረገው ድጋፍ ወጣቶች አልባሌ ቦታዎች እንዳይውሉ እና የበለጠ ተወዳዳሪና ብቁ እንዲሆኑ የሚያስችል ነው ብለዋል።

‎ማዕከሉ ለወጣቶች በዘላቂነት አገልግሎት እንዲሰጥ አስፈላጊውን ድጋፍና ቁጥጥር እንደሚደረግም ገልፀዋል።

‎የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዘካሪያስ ዎንታሞ በበኩላቸው ክልሉ ያደረገው ዘመናዊና አዳዲስ ዕቃዎችን በተገቢው ለወጣቶች አገልግሎት እንዲውል የማድረግ ስራ ይሰራልም በማለት ለተደረገው ድጋፍም ምስጋና አቅርበዋል።

‎ማዕከሉ ለታለመለት አላማ እንዲውልና የወጣቶችን አቅሞ መገንቢያ እንዲሆን ልዩ ትኩረት ይሰጣል ብለዋል።

Address

South Ethiopia Region Jinka
Jinka

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የደ/ኢ/ክ/ ወጣቶች ጉዳይና በጎ ፍቃድ አገልግሎት ኮምሽን posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to የደ/ኢ/ክ/ ወጣቶች ጉዳይና በጎ ፍቃድ አገልግሎት ኮምሽን:

Shortcuts

Share