08/08/2025
በመንገድ ትስስር ለምግብ ዋስትና ( RCAFSP) ፕሮጀክት ከወቅተት-ጊቻ-አፍነት ዋጫ ድረስ 9.03 ኪ.ሜ የመንገድ ግንባታ ሥራ ሪክክብ ተደርጐ በይፋ ተጀመረ::
ነሐሴ 1/ 2017 ዓ/ም
ገሊላ
በአሪ ዞን ሰሜን አሪ ወረዳ ከወቅተት-ጊቻ- አፍነት ዋጫ ድረስ ሶስት ቀበሌያትን የሚያገናኝ 9.03 ኪ/ሜ የመንገድ ግንባታ ስራ በክልሉ ም/ቢሮ ኃላፊ እና የት/ዘርፍ ኃላፊ ዶ/ር ብርሃኑ ጉቦ ፣ በአሪ ዞን የብ/ፓርቲ አደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ አቶ አስፋው ዶሪ ፣ የአሪ ዞን ት/መ/ል/ መምሪያ ኃላፊ አቶ ገዛኸኝ ጨነቀ እንድሁም የሰ/አሪ ወረዳ አሰዳደሪና ሌሎችም የወረዳው ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት የመንገድ ሰራዉ ማስጀመሪያ ፕሮግራም በጋማ ቀበሌ በደማቅ ሁኔታ ተካሂዷል :: መንገዱን በ53 ሚሊዮን ብር ጨረታ አሸንፈው ወደ ስራ የገቡት IFBORU CONSTRUCTION ተቋራጭ በ6 ወራት ጊዜ ውስጥ ሰራዉን አጠናቀው ለማስረከብ ውል ገብተው የተረከቡ ቢሆንም በሚቀጥሉት አራት ወራት ዉስጥ በጥራት ስርተን እናጠናቅቃለን ስሉ የፕሮጀክት ማነጀሩ እንጂኔር ማንዴላ ተናግረዋል :: በዓለም ባንክ ድጋፍ ፣ በክልሉ ፣ በዞኑ እና በወረዳው የጋራ ትብብር የሚሰራው የመንገድ ስራ ፕሮጀክት በወረዳችን ባለፉት ወራት በጥገና ኘሮግራም ከገሊላ -አርፋሮ - ሌሎ ድረስ 18.3 ኪ/ሜ ከያዘው ዉስጥ እስከ 7 ኪ/ሜ ድረስ ያለዉን ሰርቶ ጨርሶ ቀሪ 11. 3 ኪ/ሜ ቀጣይ የሚሰራ ሲሆን አሁን ደግሞ የወቅተት - ጊቻ - አ/ዋጫ መንገድ በ 2017 ዓ/ም በግንባታ ከተያዙ ዕቅዶች ውስጥ የመጀመሪያው በመሆን ወደ ስራ ተገብቷል :: ቀጣይም በ2018 በወረዳችን ውስጥ ያሉ ቀሪ ቀበሌያትን የሚያገኙ መንገዶች ልሰሩ በዕቅድ ተይዘዋል :: የሰሜን አሪ ወረዳ ትራንስፖርት እና መንገድ ልማት ጽ/ቤት