14/08/2026
🌾🤝 በጎነት ለአብሮነት! በጂንካ ከተማ በኩሬ የበቆሎ ሽልቃቆ ተከናወነ
ነሐሴ 8/2018 ዓ.ም | ጂንካ
በጂንካ ከተማ በኩሬ የበቆሎ ሽልቃቆ በበጎ ተግባር መልክ ተከናወነ። የጂንካ ከተማ ወጣቶችና የሴቶች አደረጃጀቶች ከኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ጋር በመተባበር በተግባሩ ተሳትፈዋል።
ከፌዴራል ሰላም ሚኒስቴር ተወክለው የመጡት አቶ ፍለታሞ ፈከና፣ ወጣቶች በእንዲህ ያሉ በጎ ተግባራት በመሳተፍ አብሮነትንና ሰላምን ማጠናከር እንዳለባቸው ገልጸዋል።
የስብዕና ግንባታ ልማት ቡድን መሪ አቶ አረጋ ዳጉማ በበኩላቸው፣ ወጣቶች ለማህበረሰቡ የሚጠቅሙ በጎ ተግባራትን በተከታታይ ማከናወን እንዳለባቸው አስገንዝበዋል።
የጂንካ ከተማ ወጣቶች ማህበር ፕሬዝዳንት ወጣት አንተነህ ተሾመ፣ ወጣቶች በበጎ ተግባር በመሳተፍ ለማህበረሰቡ ችግር መፍትሄ ከመሆን ባለፈ የአብሮነት ባህልን ማጠናከር እንዳለባቸው ገልጸዋል።
የወጣቶች ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንትም ኤፍሬም ጉልላት የወጣቶች አደረጃጀቶች በተቀናጀ መልኩ ሲሰሩ በከተማው የልማትና የበጎ ተግባር ሥራዎች የሚታይ ውጤት እንደሚመጣ ገልጸዋል።
የወጣቶች ማህበር ጸሐፊ ወጣት አንተነህ አለማየሁ በበኩላቸው፣ “የበጎ ተግባር ዋና ዓላማው ለሌላው መድረስና አብሮነትን በተግባር ማሳየት ነው” በማለት፣ ወጣቶችና ሴቶች በጋራ ሲሰሩ ትንሽ የሚመስል ተግባር እንኳን ትልቅ ውጤት እንደሚያመጣ አስገንዝበዋል።
የከተማዉ የብልጽግና ፓርቲ ወጣቶች ሥራ አስፈጻሚዎችም ባደረግንዉ ማስተባበር የተከናወነው ይህ ተግባር፣ የመረዳዳት፣ የትብብርና የአብሮነት ነዉ በማለት ተገልፆል ።
🌱 በጎነት ለአብሮነት፤ አብሮነት ለልማት!