የኮሬ ዞን ፖሊስ መምሪያ - Koore Zone Police Department

  • Home
  • Ethiopia
  • Kele
  • የኮሬ ዞን ፖሊስ መምሪያ - Koore Zone Police Department

የኮሬ ዞን ፖሊስ መምሪያ - Koore Zone Police  Department ያለህዝብ ተሳትፎ ሠላምን በዘላቂነት ማረጋገጥ አይቻልም

የኮሬ ዞን ፖሊስ መምሪያ ትራፊክ አደጋ መከላከልና ቁጥጥር ዲቭዥን ከኬሌ ከተማ አሰተዳደር ትራፊክ ሥራ ሂደት ጋር ዉይይት ማድረጉን አስታወቀ።ኬሌ:-ነሐሴ 22/2018 ዓ/ም  ኮሬ ዞን  ፖሊስ...
28/08/2026

የኮሬ ዞን ፖሊስ መምሪያ ትራፊክ አደጋ መከላከልና ቁጥጥር ዲቭዥን ከኬሌ ከተማ አሰተዳደር ትራፊክ ሥራ ሂደት ጋር ዉይይት ማድረጉን አስታወቀ።

ኬሌ:-ነሐሴ 22/2018 ዓ/ም ኮሬ ዞን ፖሊስ መምሪያ

የኮሬ ዞን ፖሊስ መምሪያ ትራፊክ አደጋ መከላከልና ቁጥጥር ዲቭዥን ከኬሌ ከተማ አሰተዳደር ትራፊክ ሥራ ሂደት ጋር አንድ ዕቅድና አንድ ሪፖርት ሥርዓቶች እና ተግባር አፈፃፀም ዙርያ ዉይይት ማድረጉን አስታዉቋል።

የኮሬ ዞን ፖሊስ መምሪያ ትራፊክ አደጋ መከላከልና ቁጥጥር ዲቭዥን ኃላፊ ኮማንደር አበበ ጣሰዉ በዉይይቱ የ2018 ዓ/ም ተግባር አፈፃፀም ገምግመው በ2019 ዓ,ም ዝርዝር ተግባር ዕቅድ ላይ በሰፊው አወያይተዋል።

ዲቪዥን ኃላፊው ኮማንደር አበበ ጣሰው ለአሽከርካሪዎች የግንዛቤ ትምህርቶችን በየጊዜ አጠናክሮ መስጠትና በኃይማኖት ተቋማት በዕድር በተለያዩ ቦታዎች አደረጃጀቶችን ማጠናከር።

የቴክኒክ ብልሽት ያለባቸውን ተሽከርካሪዎችን በጥብቅ መቆጣጠር፤የታሪፍ ቁጥጥር ላይ በትኩረት መሥራት፤የሥነ-ምግባር ችግር ያለባቸው አሽከርካሪዎችን ማረም፤እና የቁጥጥር ሥራዎችን ከአድሎአዊ አሰራር የፀዳ በማድረግ የተሳለጠ አገልግሎት ለማህበረሰባችን በመስጠት ክብር የሆነውን የሰዉ ህይወት ከሞት ከአደጋ ለመታደግና የንብረት ውድመቶች እንዳይከሰት የመከላከል ሥራዎችን መስራት ከእኛ የሚጠበቅ ነዉ በማለት አስረድተዋል።

አክለውም የሚከሰቱ አደጋዎችን በመከላከል ከመንገድና ትራንስፖርት ልማት ጽ/ቤት ጋር በቅርበት በቅንጅት መሥራት ከመናኸሪያ ከመኪና ወንበር በላይ ትርፍ ጭነው የሚወጡትን መቆጣጠርና በከተማ ዉስጥ ከፍጥነት ወሰን በላይ የሚያሽከረክሩትን የሚረብሽ ድምፅ የሚጠቀሙትን አሽከርካሪዎችን መቆጣጠር ማረም ይጠበቅብናል በማለት ገልጸዋል።

በመጨረሻም ተሳታፊዎች በተነሱ ሀሳቦች ላይ በሰፊው ተወያይተው ቀጣይ ተግባር ላይ በተቀመጠው አቅጣጫ መሠረት በትኩረት ለመሥራት አቅጣጫዎችን በማስቀመጥ
የነበረዉን ዉይይት አጠናቀዋል።

የኮሬ ዞን ፖሊስ መምሪያ ህዝብ ግንኙነት

ኮሬ ዞን ፖሊስ መምሪያ እና ኬሌ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽ/ቤት የአመራሮችንና የአባላትን ደንብ ልብስ አለባበስ ወትሮ ዝግጁነት ላይ ያተኮረ ቁጥጥር በመከታተል ማካሄዱን ቀጥሏል።ኮሬ ዞን ፖሊ...
27/08/2026

ኮሬ ዞን ፖሊስ መምሪያ እና ኬሌ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽ/ቤት የአመራሮችንና የአባላትን ደንብ ልብስ አለባበስ ወትሮ ዝግጁነት ላይ ያተኮረ ቁጥጥር በመከታተል ማካሄዱን ቀጥሏል።

ኮሬ ዞን ፖሊስ መምሪያ ፦ነሐሴ 21/2018 ዓ.ም

ኮሬ ዞን ፖሊስ መምሪያ የአመራሩንና አባላትን ደንብ ልብስ አለባበስ ወትሮ ዝግጁነት ላይ ያተኮረ ቁጥጥር ማካሄዱን አስታወቀ።

አመራሮች እንደገለጹት የተስተካከለ አለባበስና ቁመና ለተሻለ ተግባር ዝግጁነት የራሱ ሚና አለው በማለት አስረድተዋል።

የመምሪያው ከፍተኛ አመራሮች እንደገለጹት የፖሊስን ተቋማዊ ገጽታ ለመገንባትና ህዝብን በብቃት ለማገልገል ከተቋሙ ዲሲፕሊን መገለጫ አንደኛ የሆነው የደንብ ልብስ አለባበስና የወትሮ ዝግጁነት ወሳኝ ሚና አለው ብለዋል።

ስለሆነም በየሳምንት ዘውትር ሰኞ እና ሐሙስ ጠዋት ወደ ሥራ ከመገባቱ በፊት በአመራሩና በአባላቱ ላይ የሚደረገው የደንብ ልብስ አለባበስ ቁጥጥር ሳይቋረጥ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ገልፀው ሁሉም የፖሊስ አመራሮች እና አባላት በትኩረት ተግባራዊ እንድያደርግ አሳስበዋል።

የክትትል ሥርዓቱ የፖሊስን ክብር ለመጠበቅና ለህብረተሰቡ የሚሰጠውን አገልግሎት ይበልጥ ውጤታማ ለማድረግ ያለመ መሆኑም አስረድተዋል ።

የኮሬ ዞን ፖሊስ መምሪያ ህዝብ ግንኙነት

ኮሬ ዞን ፖሊስ መምሪያ እና ኬሌ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽ/ቤት  አመራር እንድሁም አባላቶች በጋራ በመሆን  የቡድን ማስ ስፖርት መርሃ-ግብር  ከ9:30 ሰዓት ጀምሮ በአንድነት አከናዉነዋሉ ...
27/08/2026

ኮሬ ዞን ፖሊስ መምሪያ እና ኬሌ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽ/ቤት አመራር እንድሁም አባላቶች በጋራ በመሆን የቡድን ማስ ስፖርት መርሃ-ግብር ከ9:30 ሰዓት ጀምሮ በአንድነት አከናዉነዋሉ ።

ኬሌ፦ነሐሴ 20/2018 ዓ.ም ኮሬ ዞን ፖሊስ መምሪያ ህዝብ ግንኙነት ዲቪዥን

በኮሬ ዞን ወቅታዊ የዉስጥ እና ዉጫዊ ፀጥታ ሁኔታ ላይ ከዞን፤ከወረዳ እና  ከተማ አስተዳደር ፀጥታ መዋቅር እና ከባለ ድርሻ አካላት ጋር ውይይት መደረጉ ተገለፀ ።‎ ከሌ፦ነሐሴ 20/2018 ...
26/08/2026

በኮሬ ዞን ወቅታዊ የዉስጥ እና ዉጫዊ ፀጥታ ሁኔታ ላይ ከዞን፤ከወረዳ እና ከተማ አስተዳደር ፀጥታ መዋቅር እና ከባለ ድርሻ አካላት ጋር ውይይት መደረጉ ተገለፀ ።

ከሌ፦ነሐሴ 20/2018 ዓ/ም ኮሬ ዞን ፖሊስ መምሪያ


‎ የኮሬ ዞን ሠላምና ፀጥታ መምሪያ፤ፖሊስ መምሪያ እና ሚሊሻ ጽ/ቤት በጋራ በወቅታዊ ፀጥታ ዙርያ ከታችኛው መዋቀር ጋር የ2018 ዓ/ም ተግባር አፈፃፀም ግምገማ እና በ2019 ዓ/ም ዕቅድ ዝርዝር ተግባራት ላይ ዉይይት ማድረጉ ገልጿል።

የኮሬ ዞን ሠላም ፀጥታ መምሪያ ኃላፊ አቶ መላኩ መርሻ የ2018 ዓ/ም የዉስጥና የዉጭ ፀጥታ እና ዝርዝር ተግባር አፈፃፀም ክንዋኔዎችን በጥልቀት ገምግመዉ በ2019 ዓ/ም ዕቅድ ዝርዝር ተግባራት ላይ ከዞን ፀጥታ መዋቀር እና ከታችኛው መዋቀር ጋር በሰፊ ዉይይት ማድረጋቸውን አስረድተዋል።

በመድረክ በዉይይቱ ላይ የሠላምና ፀጥታው ኃላፊው ያነሱት በዞናችን የህዝብ ሰላምና ደህንነት ማስጠበቅ ትልቅ ኃላፊነት የፀጥታ መዋቅር እና የባለ ድርሻ አካላት በመሆኑ የፀጥታ ጉዳይ በትኩረት ልሠራ እንደሚገባ አሳስበው በ2018 ዓ/ም በጉድለት የተነሱትን በማደራጀት የ2019 ዓ/ም የዕቅድ አካል በማድረግ ሁሉም መዋቀር መሥራት እንዳለበት አሳስበዋል፡፡

አክለዉም የዉስጥ እና የዉጭ አጎራባች የፀጥታ ሁኔታዎችን በትኩረት በመገምገም የሚልሻ አባላት እና ህዝባዊ ሠራዊቶችን በማደራጀትና በማቀናጀት በቅርበት በመከታተል አጠናክሮ በመስራት ሠላም ማስፈን የሁሉም ድርሻ ልሆን እንደምገባ አስቀምጠዋል።

የኮሬ ዞን ፖሊስ መምሪያ አዛዥ ኮማንደር ስዳሞ ማዳሞ
እና የኮሬ ዞን ሚሊሻ ጽ/ቤ ኃላፊ አቶ ኤልያስ ይልማ የፀጥታ ተቋም ጊዜና ወቅትን በተገናዘበ መልኩ በመደራጀት የማህበረሰብ ሠላምንና ደህንነትን አሁናዊ ካለዉ ሥጋቶች ማላቀቅ እና ወደ ልማት እንድሰማራ በተደራጀ አቅም መሰራት እንዳለበት አስረድተዋል።

ከተሳታፊዎች እና ከባለድርሻ አካላት የተነሱ ሃሳቦችም በዉስጥ እና በዉጭ የፀጥታ ተግባራት ላይ በጋራ በቅንጅት ተረባርበን በመሠለፍ መሠራት ባለባቸዉ ጉዳዮች ላይ በትኩረት በመስራት ችግሮችንም መፍታትና በቀጣይ የህዝብን ሠላም የማረጋገጥ ሥራ የጋራ ዕቅድ በማድረግ የፀጥታ መዋቅሮቻችን በትኩረት መሥራት አለበት በማለት
በተነሱ ሀሳቦች ላይ በሰፍዉ ተወያይተዋል።

በማጠቃለያው የዞኑ ሠላምና ፀጥታ ኃላፊው ሁሉም የፀጥታ መዋቀር በጋራ በመሆን ከዞን ማዕከል እስከ ታችኛው ወረዳ ቀበሌ ድረስ የአደረጃጀት ሥርዓቶችን በማጠናከርና ተከታትሎ አመራሮች ከዉይይቱ ጀምረው በክላስተር በተመደቡበት መዋቀር በመውረድና በመግባት ድጋፍ ማድረግ እንዳለባቸው በማለት የነበረዉን ዉይይት አጠቃለዋል።

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን የ2018 ዓ/ም  የዕቅድ አፈፃፀምና የአመራሩና የአባላት ግምገማ መድረክ መካሔድ ጀመረ።ወላይታ ሶዶ ነሐሴ 19/2018 ዓ/ም(ደኢፖኮ)በመድረኩ መክፈቻ ላ...
25/08/2026

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን የ2018 ዓ/ም የዕቅድ አፈፃፀምና የአመራሩና የአባላት ግምገማ መድረክ መካሔድ ጀመረ።

ወላይታ ሶዶ ነሐሴ 19/2018 ዓ/ም(ደኢፖኮ)

በመድረኩ መክፈቻ ላይ ንግግር ያደረጉት ኮሚሽነር ፍስሃ ጋረደው ያለፈው በጀት አመት እቅድ አፈጻጸማችን ለተቋማችን ምን አተረፈ ምንስ መስራት ሲገባን አልሰራንም የሚለው በሚቀርብ ሪፖርት የምናደምጥ ሲሆን አመራሩና አባላቱስ በአፈጻጸም ምን ይመስላሉ የሚለው የሚገመግም መድረክ መሆኑን አስታውቀዋል ።

መድረኩ ኮሚሽኑ የሚያሻግሩ ሀሳቦች እንደሚነሱበት እምነቴ ነው ብለዋል።

በዚህ መድረክ ከክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን አመራር እስከ ፈጻሚ ድረስ የሚሳተፉ ሲሆን ለተከታታይ ቀናትም የሚቀጥል መሆኑ ከወጣው መረሀ-ግብር ታውቋል።

ዘገባ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ነዉ

የኮሬ ዞን ፖሊስ መምሪያ አዛዥ ኮማንደር ስዳሞ ማዳሞ ለመላው ለእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለ1ሺህ 501 ኛው መውለድ በዓል በሠላም አደረሳችሁ አደረሰን በማለት መልካም ምኞታቸውን ገል...
25/08/2026

የኮሬ ዞን ፖሊስ መምሪያ አዛዥ ኮማንደር ስዳሞ ማዳሞ ለመላው ለእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለ1ሺህ 501 ኛው መውለድ በዓል በሠላም አደረሳችሁ አደረሰን በማለት መልካም ምኞታቸውን ገልፀዋል።

ኬሌ:- ነሐሴ 19/2018 ዓ/ም ኮሬ ዞን ፖሊስ መምሪያ

የኮሬ ዞን ፖሊስ መምሪያ አዛዥ ኮማንደር ስዳሞ ማዳሞ ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለ1ሺህ 501 ኛው መውለድ በዓል በሠላም አደረሳችሁ አደረሰን በማለት መልካም ምኞታቸውን ገልፀዋል።

ኮማንደር ስዳሞ ማዳሞ በዓሉን ስናከብር በመቻቻል፤በፍቅር በመደጋገፍና እርስ በርስ በመጠያየቅ በዞናችን በዓሉ በሠላም ተከብሮ እንዲያልፍ ሁሉም የኃይማኖት ተከታዮችና የማህበረሰብ አካል የበኩሉን አስተዋጽኦ እንዲያደርጉ በመልዕክታቸው አስተላልፈዋል።

ኮሬ ዞን ፖሊስ መምሪያ ህዝብ ግንኙነት ዲቪዥን

ምክትል ኮማንደር ኤርምያስ ኤሳው ኮሬ ዞን የሳርማሌ ወረዳ ፖሊስ ጽ/ቤት አዛዥ ሆነው ተሹመዋል።
25/08/2026

ምክትል ኮማንደር ኤርምያስ ኤሳው ኮሬ ዞን የሳርማሌ ወረዳ ፖሊስ ጽ/ቤት አዛዥ ሆነው ተሹመዋል።

የኮሬ ዞን ፖሊስ መምሪያ ሰኞ ጠዋት ፖለን ቆጠራ እና ቁጥጥር  በፎቶነሐሴ 18/2018 ዓ/ም  ኮሬ ዞን ፖሊስ መምሪያ
24/08/2026

የኮሬ ዞን ፖሊስ መምሪያ ሰኞ ጠዋት ፖለን ቆጠራ እና ቁጥጥር በፎቶ

ነሐሴ 18/2018 ዓ/ም ኮሬ ዞን ፖሊስ መምሪያ

በኮሬ ዞን ፖሊስ መምሪያ ልማት ዕቅድ ዲቪዥን የተዘጋጀ ሥልጠና ለኬሌ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽ/ቤት በዕቅድ አዘገጃጀት እና በሪፖርት አቀራረብ ዙሪያ ሥልጠና መስጠቱ ተገለፀ። ኬሌ ፦ ነሐሴ ...
20/08/2026

በኮሬ ዞን ፖሊስ መምሪያ ልማት ዕቅድ ዲቪዥን የተዘጋጀ ሥልጠና ለኬሌ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽ/ቤት በዕቅድ አዘገጃጀት እና በሪፖርት አቀራረብ ዙሪያ ሥልጠና መስጠቱ ተገለፀ።

ኬሌ ፦ ነሐሴ 14 / 2018 ዓ/ም ኮሬ ዞን ፖሊስ መምሪያ

በኮሬ ዞን ፖሊስ መምሪያ ልማት ዕቅድ ዲቪዥን የተዘጋጀ ሥልጠና ለኬሌ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽ/ቤት ማናጅሜንት ፣ሥራ ሂደት አስተባባሪዎች ፣ቡድን መሪዎችና ለቀበሌ ሴክተር ኦኘሰሮች በዕቅድ አዘገጃጀት እና በሪፖርት አቀራረብ ዙሪያ ሥልጠና መስጠቱ ተገለፀ።

መክፈቻ ያደረጉት የኬሌ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽ/ቤት አዛዥ ረዳት ኢንስፔክተር አስረስ ሙልጌታ በዝህ መልክ ሥልጠናው ተዘጋጅቶ መቅረቡ ለተሻለ ተቋማዊ ለዉጥ ለማምጣትና ዉጤት ለማስመዝገብ ከፍተኛ የሆነ የራሱ አስተዋጽኦ አለዉ ብለዋል።

ሥልጠናውን አዘጋጅተው የሰጡት ረዳት ኢንስፔክተር ታመነ ተክሉ ዕቅድ አዘገጃጀትና የሪፖርት አቀራረብ በአንድ ዕቅድና በአንድ ሪፖርትር ስርዓት መሆን እንዳለበትና የሪፖርት አስፈላጊነትና ጠቀሜታውን አብራርተው ለአመራሮች ስልጠናውን ሰጥተዋል።

በሥልጠናው ከተነሱት መር ሀሳቦች ዉስጥ ፦በተቋም ዉስጥ ከምንም በላይ የሚቀድመው ዕቅድ ነዉ ፣ ዕቅድ የተቋሙን ራዕይንና ዓላማውን የምንረዳበት መንገድ ነዉ ፣ ዕቅድ ሀብትንና ጊዜን ከብክነት ለመጠበቅ ይጠቅማል ፣ ዕቅድ ምን እሰራለሁ : መቼ : በምን ጊዜ : እንዴት ወዘተ አስቀምጠን የምንጓዝበት መሳሪያ ነዉ ፣ የምናቅዳቸው ዕቅዶች ተፈጸምነት ልያገኙ የምችሉና ሚዛናዊ መሆን አለባቸው ፤ዕቅድ ቅድምያ መሥራት ያለብንን ለይተን የምናውቅበት ግቦችን ተልመን የምንጓዝበት መንገድ ነው፤ዕቅድ ልሻሻል ልቀነስ የምችል ነዉ፤ሪፖርት ስቀርብ ያልተንዛዛ ፤ወቅታዊነትና ተዓማኒነት ያለው ከእያንዳንዱ ሥራ ሂደት መቅረብ እንዳለበት እና ሌሎችንም ዝርዝር ሀሳቦችንም በሰፊው በሥልጠናዉ ላይ አስገንዝበዋል።

አክለው የሥልጠናው ዋና ዓላማው በ2018 ዓ/ም በጉድለት የታዩትን በ2019 ዓ/ም ዕቅድ ተግባር አፈፃፀም ላይ በትኩረት በመስራት የተሻለ ዉጤት ለማስመዝገብ እንደሆነም አንስተዋል።

ተሳታፊዎች የተሰጠዉን ሥልጠና ለቀጣይ ተግባር ወሳኝ ሚና ያለዉ እንደሆነ በተገቢው ጊዜና ወቅት እንደሆነም አስተያየት ተሰጥተዋል ።

በመጨረሻም በሥልጠናው በተነሱ ጥያቀዎች ላይ በፖሊስ ጽ/ትቤ ኃላፊው እና ሥልጠናዉን ባዘጋጀዉ ማብራሪያ እና ምላሽ ተሰጥቶ ተጠናቋል።

ኮሬ ዞን ፖሊስ መምሪያ ህዝብ ግንኙነት ዲቪዥን

ኮሬ ዞን ፖሊስ መምሪያ የአመራርና አባላት ደንብ ልብስ አለባበስ እና ወትሮ ዝግጁነት ላይ ያተኮረ ቁጥጥር ወደ ሥራ ከመሰማራታቸው በፍት አድርገዋል።ኮሬ ዞን ፖሊስ መምሪያ ፦ነሐሴ 14/2018...
20/08/2026

ኮሬ ዞን ፖሊስ መምሪያ የአመራርና አባላት ደንብ ልብስ አለባበስ እና ወትሮ ዝግጁነት ላይ ያተኮረ ቁጥጥር ወደ ሥራ ከመሰማራታቸው በፍት አድርገዋል።

ኮሬ ዞን ፖሊስ መምሪያ ፦ነሐሴ 14/2018 ዓ.ም

Address

Amaro Kele
Kele

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የኮሬ ዞን ፖሊስ መምሪያ - Koore Zone Police Department posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share