የኦሮሞ ብ/አስ/መሬት መምሪያ Qajeelcha Lafa B/S/Oromoo

  • Home
  • Ethiopia
  • Kemise
  • የኦሮሞ ብ/አስ/መሬት መምሪያ Qajeelcha Lafa B/S/Oromoo

የኦሮሞ ብ/አስ/መሬት መምሪያ Qajeelcha Lafa B/S/Oromoo ፍትሐዊ የመሬት አስተዳደርና አጠቃቀም ስርዓት ለሁሉም!!!

የኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር መሬት መምሪያ ለክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት የሚውል የትምህርት መርጃ ቁሳቁስ ድጋፍ አደረገከሚሴ — ነሀሴ 15/2018 የኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር መሬት መምሪያ...
21/08/2026

የኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር መሬት መምሪያ ለክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት የሚውል የትምህርት መርጃ ቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ

ከሚሴ — ነሀሴ 15/2018 የኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር መሬት መምሪያ ህዝብ ግንኙነት

የኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር መሬት መምሪያ በክረምት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት መርሐ-ግብር ዝቅተኛ ገቢ ላላቸው የማኅበረሰብ ክፍሎች ልጆች የሚውል የደብተርና የእስክሪፕቶ ድጋፍ ለዞኑ ትምህርት መምሪያ አስረክቧል።

ይህ ድጋፍ የተዘጋጀው መጪውን የትምህርት ዘመን ታሳቢ በማድረግ ሲሆን፣ ዓላማውም አቅመ-ደካማና ዝቅተኛ ገቢ ያላቸው ወላጆች ልጆቻቸውን ወደ ትምህርት ቤት ለመላክ የሚያደርጉትን ጥረት በከፊልም ቢሆን ለማገዝ መሆኑ ተገልጿል።

15/08/2026
የኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር መሬት መምሪያ የ2018 በጀት ዓመት የዕቅድ አፈፃፀም ግምገማ እና የ2019 ዕቅድ ትውውቅ መድረክ የቅድመ ዝግጅት ስራ አከናወነከሚሴ — ነሀሴ 08/2018የኦሮሞ ...
14/08/2026

የኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር መሬት መምሪያ የ2018 በጀት ዓመት የዕቅድ አፈፃፀም ግምገማ እና የ2019 ዕቅድ ትውውቅ መድረክ የቅድመ ዝግጅት ስራ አከናወነ

ከሚሴ — ነሀሴ 08/2018
የኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር መሬት መምሪያ ህዝብ ግንኙነት

የኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር መሬት መምሪያ የ2018 በጀት ዓመት የዕቅድ አፈፃፀም ግምገማ እና የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ትውውቅ መድረክን ለማካሄድ የሚያስችለውን የቅድመ ዝግጅት ስራ ዛሬ ማከናወኑን አስታውቋል።

መምሪያው እንዳመለከተው ይህ የቅድመ ዝግጅት ስራ በበጀት ዓመቱ የተከናወኑ ዋና ዋና ተግባራትን በዝርዝር ለመገምገም እና በቀጣዩ በጀት ዓመት የሚተገበሩ ዕቅዶችን ይፋ ለማድረግ ለሚዘጋጀው ሰፊ መድረክ መነሻ የሚሆን ነው።

በመድረኩ የ2018 በጀት ዓመት የሥራ አፈፃፀም ጥንካሬዎችና ድክመቶች በጥልቀት የሚገመገሙ ሲሆን፣ የተገኙ መልካም ተሞክሮዎችን በማስቀጠልና የታዩ ክፍተቶችን በማረም ረገድ በትኩረት ለመስራት የሚያስችል አቅጣጫ ይቀመጣል ተብሎ ይጠበቃል።

ይህ የቅድመ ዝግጅት መድረክ መካሄዱ ዋናው የግምገማ እና የእቅድ ትውውቅ መድረክ በተሳካ ሁኔታ እንዲጠናቀቅና በቀጣይም የተቀናጀ አሠራርን ለመዘርጋት ያለመ ነው መሆኑን የመምሪያው ኃላፊ የሆኑት አቶ ዘሪሁን በቀለ ገልጸዋል።

13/08/2026
13/08/2026

ዘመናዊ የካዳስተር ስርዓት እንገነባለን!!!

የኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር መሬት መምሪያ ለክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት የሚውል የደብተርና እስክሪፕቶ ድጋፍ አሰባሰበ።ከሚሴ — ነሀሴ 06/2018 የኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር መሬት መምሪያ...
12/08/2026

የኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር መሬት መምሪያ ለክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት የሚውል የደብተርና እስክሪፕቶ ድጋፍ አሰባሰበ።

ከሚሴ — ነሀሴ 06/2018 የኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር መሬት መምሪያ ህዝብ ግንኙነት

የኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር መሬት መምሪያ በክረምት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት መርሐ-ግብር ዝቅተኛ ገቢ ላላቸው የማኅበረሰብ ክፍሎች ልጆች የሚውል የደብተርና የእስክሪፕቶ ድጋፍ ማሰባሰቡን አስታውቋል። ይህ የድጋፍ ማሰባሰብ ሥራ የተዘጋጀው መጪውን የትምህርት ዘመን ታሳቢ በማድረግ ሲሆን፣ ዓላማውም በኢኮኖሚ እጥረት ምክንያት ለልጆቻቸው የትምህርት መርጃ ቁሳቁስ ማሟላት ለሚቸገሩ ወላጆችና ተማሪዎች እገዛ ማድረግ እንደሆነ ተገልጿል።

የመምሪያው የሥራ ኃላፊዎችና ሠራተኞች በበጎ ፈቃድ አገልግሎት ተሳትፎ ያደረጉ ሲሆን፣ የተሰበሰቡት የትምህርት ቁሳቁሶች ድጋፍ ለሚያስፈልጋቸው ተማሪዎች በአግባቡ እንዲደርሱ ይደረጋል ተብሏል።

በቀጣይም የተሰበሰቡትን ቁሳቁሶች ለይቶ ተጠቃሚ ለሆኑ ተማሪዎች የማከፋፈል ሥራ የሚሠራ ሲሆን፣ ሌሎች ተቋማትና ባለድርሻ አካላትም በተመሳሳይ ሁኔታ ዝቅተኛ ገቢ ያላቸውን የኅብረተሰብ ክፍሎች በመደገፍ የበኩላቸውን አስተዋጽኦ እንዲያበረክቱ ጥሪ ቀርቧል።

የመሬት መረጃ አያያዝን ዲጂታል ለማድረግ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጠ።ነሀሴ 06/2018የኦሮሞ ብ/ሰብ አሰተዳደር መሬት መምሪያ ህዝብ ግንኙነት የኦሮሞ ብሄረሰብ አስ/ መሬት መምሪያ የመ...
12/08/2026

የመሬት መረጃ አያያዝን ዲጂታል ለማድረግ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጠ።

ነሀሴ 06/2018
የኦሮሞ ብ/ሰብ አሰተዳደር መሬት መምሪያ ህዝብ ግንኙነት

የኦሮሞ ብሄረሰብ አስ/ መሬት መምሪያ የመሬት ይዞታ ምዝገባና መረጃ የካዳስተር ስርአትን ግንባታ ተግባራዊ ለማድረግ በባቲ ከተማ ለአመራርና ባለሙያዎች የግንዛቤ ፈጠራ ተሰጥቷል።

በመድረኩ ላይ የኦሮሞ ብሔ/ዞን መሬት መምሪያ ሀላፊ አቶ ዘሪሁን በቀለ፣ የባቲ ከተማ ከንቲባ አቶ አብዱ አህመድ፣ የከተማ አመራሮችና የቀበሌ ስራአስኪያጆች እንዲሁም ባለሙያዎች ተገኝተዋል።

የኦሮሞ ብ/ሰብ አስተዳደር መሬት መምሪያ ሀላፊ አቶ ዘሪሁን በቀለ በንግግራቸው እንደገለፁት የመሬት ካዳስተር ስርአት መገንባት አላማው እያንዳንዱን ቁራሽ መሬት ቆጥሮና መዝግቦ ለማወቅ ነው ብለዋል።

ስለዚህ እያንዳንዱ በከተማ አስተዳደሩ ውስጥ ያሉ ቁራሽ መሬቶችን ብዛት መሰረት በማድረግ በየቀበሌው ያሉ የመንግስትና የግል ይዞታዎችን ተመዝግበው መያዝ እንዳለበት ገልፀዋል።

የመድረኩን የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የባቲ ከተማ ከንቲባ አቶ አብዱ አህመድ በበኩላቸው ይህ ስልጠና ለከተማችን ዘመናዊ የመሬት ልማት ካዳስተር ምዝገባ ስርአት ወቅታዊና አስፈላጊ ነው ብለዋል።

ካዳስተር ማለት መብትን፣ ክልከላንና ኃላፊነትን እንዲሁም የይዞታውን ካርታ አጣምሮ የያዘ ወቅታዊ የመሬት ይዞታ መረጃ ስርዓት ነው።

የኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር መሬት መምሪያ ለጨፋ ሮቢት ከተማ አስተዳደር በካዳስተር ቅድመ ዝግጅት ዙሪያ ስልጠና ሰጠጨፋ ሮቢት — ነሀሴ 01/2018 የኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር መሬት መምሪያ...
07/08/2026

የኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር መሬት መምሪያ ለጨፋ ሮቢት ከተማ አስተዳደር በካዳስተር ቅድመ ዝግጅት ዙሪያ ስልጠና ሰጠ

ጨፋ ሮቢት — ነሀሴ 01/2018
የኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር መሬት መምሪያ ህዝብ ግንኙነት

የኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር መሬት መምሪያ ለጨፋ ሮቢት ከተማ አስተዳደር አመራሮች፣ የዘርፉ ባለሙያዎች እና ለሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት በዘመናዊ የከተማ መሬት መረጃ አያያዝ (ካዳስተር) ቅድመ ዝግጅት ዙሪያ ያተኮረ ስልጠና መስጠቱ ታውቋል።

የስልጠናው ዋና ዓላማ በከተማዋ ደረጃውን የጠበቀ እና ዘመናዊ የሕጋዊ ካዳስተር ሥርዓት ለመዘርጋት የሚያስችሉ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎችን በብቃት ለመምራትና ለመተግበር የሚያስችል አቅም መገንባት እንደሆነ ተገልጿል።

በስልጠናው መድረክ ላይ የመሬት መምሪያው የሥራ ኃላፊዎችና ባለሙያዎች እንደገለጹት፤ ዘመናዊ የካዳስተር ሥርዓት መዘርጋት በከተሞች የሚስተዋለውን የተወሳሰበ የመሬት አስተዳደር ችግር ለመፍታት፣ የአገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ እንዲሁም የይዞታ ባለቤትነት ዋስትናን ለማረጋገጥ ወሳኝ ሚና አለው።

የካዳስተር ሥርዓትን በተሟላ ሁኔታ ወደ ሥራ ለማስገባት ደግሞ አስቀድሞ የግንዛቤ ፈጠራ ስራዎችን መስራት ፣መሠረታዊ የካርታ ዝግጅትን ማጠናቀቅ፣ የቅየሳ መነሻዎችን ማስተካከልና ይዞታዎችን በልዩ የይዞታ መለያ ኮድ ማደራጀትን የመሳሰሉ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎችን በጥራት ማከናወን እንደሚገባ ተመላክቷል።

በተጨማሪም የካዳስተር ሥርዓት መዘርጋት በከተማ መሬት አጠቃቀም ላይ የሚስተዋሉ ሕገ-ወጥ አሰራሮችንና የኪራይ ሰብሳቢነት ምንጮችን ለማድረቅ፣ የከተማዋን የገቢ አቅም ለማሳደግ እንዲሁም በይዞታ ይገባኛል ምክንያት በዜጎች መካከል የሚፈጠሩ አላስፈላጊ ክርክሮችን ለመቀነስ ከፍተኛ እገዛ እንደሚያደርግ በስልጠናው ወቅት ማብራሪያ ተሰጥቷል።

በመጨረሻም፣ የስልጠናው ተሳታፊዎች በቀጣይ በሚከናወኑ የካዳስተር ዝግጅት ሥራዎችና የባለድርሻ አካላት ቅንጅታዊ አሰራር ላይ ውይይት በማድረግ ለቀጣይ ሥራዎች አቅጣጫ በማስቀመጥ ስልጠናው መጠናቀቁ ታውቋል።

05/08/2026

ከተማ መሬትና ቤት ይዞታ ስመ-ንብረት ዝውውር የሚፈጸምበት አግባብ :_
✅✅✅✅✅✅✅✅✅✅✅✅✅✅✅✅✅
በስመ ንብረት ዝውውር ወቅት መሟላት ያለባቸው መረጃዎች የከተማ ቦታን በሊዝ ስለመያዝ በወጣው አዋጅ ቁጥር 721/2004 አንቀፅ 33 ንዑስ አንቀፅ 2 አንፃር ሲታይ፦
ሀ/ የከተማ ቤትና ይዞታ ስመ-ንብረት ዝውውር ስለመፈጸም የሚከተሉት ማስረጃዎች/ሰነዶች ሲሟሉ የስመ ንብረት ዝውውር የሚፈጸም ይሆናል፤
✍️ህጋዊ የይዞታ ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት/ካርታ፣
✍️ጸድቆ የተሰጠ የግንባታ ፕላን፣ የስራ ዝርዝር ግምት ወይም የጸደቀ የነባር ግንባታ ፕላን፣
✍️ጸድቆ በተሰጠው የግንባታ ፕላን መሰረት ስለመገንባቱ እና ግንባታው ያለበት ደረጃ የተረጋገጠበት ማስረጃ/50% እና በላይ/፤
✍️ውዝፍ የሊዝ ኪራይ ዕዳ የሌለበት ስለመሆኑ የተሰጠ የማረጋገጫ ደብዳቤ ወይም ቀሪ የሊዝ ክፍያ ዕዳውን ገዥው ለመክፈል በፊርማ ያረጋገጠበት የስምምነት ደብዳቤ ፣
✍️በንብረቱ ላይ የባንክ እዳ/የፍ/ቤት ዕግድ የሌለበት ስለመሆኑ ማረጋገጫ ሲቀርብ፣
✍️ የቤትና ይዞታ ስም ዝውውር ጥያቄው የቀረበው በህግ ባለመብት/በውርስ/በፍርድ አፈጻጸም ወይም በውክልና ከሆነ ይህንኑ የሚገልጽ ማስረጃ፤
✍️ በግለሰቦች ግዥና ሽያጭ ወይም ስጦታ ስምምነት ከሆነ በዉልና ማስረጃ በአካል ቀርቦ በእማኞች የተፈረመ የስምምነት የውል ማስረጃ ሲቀርብ፣
ለ/ በሽያጭ/በስጦታ የሚተላለፍ ቤትና ይዞታ ስም-ዝውውር መሟላት ያለባቸው መስፈርቶች፣
✍️ግንባታው በዋስትና ያልተያዘ እንዲሁም እዳ የሌለበት መሆኑ ሲረጋገጥ ወይም እዳው በሚመለከተው አካል በደብዳቤ መነሳቱ ሲረጋገጥ፣
✍️ የቤትና ይዞታ ሽያጭ ወይም የስጦታ ውሉ በምስክሮች ሲረጋገጥና በፍትህ ወይም በመሪ ማዘጋጃ ቤት ፊት ቀርቦ ሲጸድቅ፣
✍️ ግንባታው ጸድቆ በተሰጠው ዲዛይን መሰረት 50 በመቶና በላይ የተሰራ መሆኑ በባለሙያ ተረጋግጦ ሲቀርብ፣
✍️ በይዞታው ላይ ውዝፍ የቦታ ኪራይ የሌለበት ስለመሆኑ ወይም ውዝፍ የቦታ ኪራይ ክፍያ አጠናቆ የከፈለ ስለመሆኑ የቀረበ ክፍያ ደረሰኝ ማረጃ ሲቀርብ፣
✍️ የአገልግሎትና የገቢዎች ክፍያ በቤቱ ግምት መሰረት ስለመከፈሉ ሲረጋገጥ፣
ዝውውሩ የሚፈፀመው በሊዝ በተገኘ ይዞታና ግንባታ ላይ ከሆነ
✍️ የሊዝ ይዞታ ባለቤትነት ኦሪጅናል ካርታና ውል ሲቀርብ፣
✍️ በሊዝ ውል መሰረት ክፍያው የተጠናቀቀና ሌሎች ግዴታዎቹን የተወጣ መሆኑ ሲረጋገጥ ወይም የሊዝ እዳው ያልተጠናቀቀ ከሆነ ስም የሚዞርለት ወገን እዳውን ለመክፈል እና ነባሩን የሊዝ ውል ግዴታዎች የተቀበለ ስለመሆኑ ከከተማው በጽሁፍና በፊርማ አረጋግጦ ሲያቀርብ፣
✍️ በሊዝ የተገዛን የመሬት ይዞታ ለሌላ ሰው ለማስተላለፍ በቅድሚያ በገባው የሊዝ ውል መሰረት በተቀመጠው የጊዜ ገደብ የሚፈለገውን የግንባታ ደረጃ ያሟላ መሆኑ ወይም የግንባታ ፈቃድ የጊዜ ገደብ ያላለፈ ወይም የግንባታ ማራዘሚያ የተፈቀደለት መሆኑ ሲረጋጥ፣
✍️ የከተማ ቤትና ይዞታ ሽያጭ ወይም የስጦታ ውሉ በምስክሮች ሲረጋጥና በዉልና ማስረጃ ቀርቦ ሲጸድቅ ይሆናል፡፡
ሐ/ በውርስ የተገኘ ይዞታና ቤት የባለቤትነት ስመ-ንብረት ዝውውር አፈፃፀም፣
(ሀ) በውርስ የተላለፈ ነባር ይዞታ ዝውውር ለመፈፀም መሟላት ያለባቸው፡-
✍️ የሚዛወረው የመሬት ይዞታ ወይም ቤት ህጋ የባለቤትነት ማስረጃ/ካርታ ሲኖረው፣
✍️ ወራሾች የውርስ ባለመብትነትን የሚያረጋግጥ የፍርድ ቤት ውሳኔ ማስረጃ ሲያቀርቡ፣
✍️ ወራሾች በውርስ ያገኙትን ይዞታ ወይም ቤት በየግላቸው የባለቤትነት ማስረጃ ለመያዝ ሲፈልጉ ለእያንዳንዳቸው ድርሻ መጠን በፍ/ቤት የፀደቀ ማስረጃ ሲያቀርቡ ወይም የሁሉም ወራሾች የጋራ ስምምነት በውል አፅዳቂ አካል ጸድቆ ሲቀርብ፣
✍️ የእያንዳንዱ ወራሽ የድርሻ መጠን በፍርድ ቤት ያልተረጋገጠ ከሆነ የስም ዝውውሩ በሁሉም ወራሾች ስም በጋራ የሚፈፀም ይሆናል፡፡
የፍርድ ቤቱ የውርሱ ውሳኔ የይዞታ ክፍፍልን የሚያስከትል ሆኖ ሲገኝ የሚፈፀመው የወቅቱን አነስተኛ የይዞታ መጠን መስፈርት የሚያሟላ ከሆነ ብቻ ነው፡፡ ይህ ካልሆነም በተነፃፃሪ የመሬት ይዞታ ድርሻ ህግ ወይም በጋራ ሰነድ/ካርታ መሰረት ይስተናገዳል፡፡
ይዞታው በውሉ መሰረት ግንባታ ለመጀመር የተሰጠውን የጊዜ ገደብ ያለፈበት እና ግንባታው ያልተጀመረ ከሆነ በውርስ ሊተላለፍ አይችልም፡፡
👉በሊዝ የተያዘ ይዞታ ለህጋዊ ወራሽ የሚተላለፈውና ዝውውር የሚፈፀመው፡-
✍️ አውራሹ በገባው የሊዝ ውል ግዴታ መሰረት አመታዊውን የሊዝ ክፍያ የፈፀመና ሌሎች የሊዝ ግዴታችን በተገቢው መንገድ የተወጣ ሲሆን፣
✍️ ወራሽ አውራሽ የገባቸውን የውል ስምምነቶች(የሊዝ መብት፣ክልከላና ኃላፊነት) ሙሉ በሙሉ የተቀበለ መሆኑን በፊርማው ሲያረጋግጥና ውዝፍ ክፍያ ካለ ከፍሎ ደረሰኝ ሲያቀርብ ይሆናል፡፡
✍️ በሊዝ ውሉ መሰረት አውራሹ በህይወት እያለ ለግንበታ መጀመሪያ የተሰጠው የጊዜ ገደብ ካለፈና ግንባታ ካልጀመረ ውሉ ተቋርጦ ቦታው ለከተማ መሪ ማዘጋጃ ቤት ተመላሽ ይሆናል፡፡
አውራሽ በይዞታው ላይ ግንባታ ያልጀመረው ከአቅም በላይ በሆነ ምክንያት መሆኑ ከተረጋጠ አውራሽ በህይወት ቢኖር ኖሮ በመመሪያው መሰረት ሊፈቀድለት የሚችለው የግንባታ መጀመሪያ የማራዘሚያ ጊዜ ለወራሽ ሊፈቀድለት ይችላል፡፡
መ/ በባንክ ሃራጅ የሚሸጥ እና የሚወረስ ቤት የባለቤትነት ስም ዝውውር
✍️ በባንክ የተሸጠ ቤት የባለቤትነት ስም ዝውውር ለመፈፀም በሐራጅ ጨረታው አሸናፊ የሆነው ሰው ያሸነፈበትን ዋጋና ለዝውውሩ በውል የገባቸው ግዴታዎች ተገልፀው ከባንኩ የተፃፈ ህጋዊ ደብዳቤና ውል ሲቀርብ፣
✍️በባንክ ዋስትና ተይዞ የነበረው ይዞታ የባለቤትነት ማረጃ/ካርታ በማህደሩ ውስጥ ካለው ሰነድ ጋር ተገናዝቦ ትክክለኛነቱ ሲረጋገጥ፣
✍️ይዞታው በሌላ ባንክ ብድርና ዋስትና ያልተያዘ ወይም እገዳ የሌለበት መሆኑ ሲረጋገጥ፣
✍️ በሁለተኛና ሶስተኛ ደረጃ ዋስትና የተመዘገበ ዋስትና ያለው ባንክ መኖሩ ከተረጋገጠ ባንኩ ስለ ይዞታው መሸጥ ሲፈቅድ፣
✍️ በባንክ ሃራጅ ሽያጭ እንዲዞር የተጠየቀው ቤትና ይዞታ የተሟላ ሰነድ የሌለው/ሰነድ አልባ ከሆነ በቅድሚያ በሥራ ላይ ባለው የሰነድ አልባ መመሪያ መሰረት ሰነድ ተሰጥቶት ሲቀርብ፣
✍️ ባንኩ ንብረቱን ባለበት ሁኔታ የሚረከብ ከሆነ የቤቱና ይዞታው ግምት እንደማንኛውም ቋሚ ንብረት ግምት ተሰልቶ ተገቢውን የአገልግሎትና የገቢ ክፍያ ሲፈጸም፣
✍️ ቤቱና ይዞታው ባንኩ በሚያወጣው ጨረታ የሚሸጥ ከሆነ ባንኩ ያቀረበው የጨረታ መነሻ ዋጋ በከተማው በኩል ተገቢ መሆኑ ተረጋግጦ በጨረታ ሲሸጥ እና የስም ማዛወሪያ ክፍያዎችን ስለመፈጸሙ የክፍያ ደረሰኝ ማስረጃ ሲያቀርብ የሥመ-ንብረት ዝውውሩ የሚፈጸም ይሆናል::

ጠበቃ አደም ሰይድ ከማል

Address

Wollo Oromo
Kemise
LAND@8569

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የኦሮሞ ብ/አስ/መሬት መምሪያ Qajeelcha Lafa B/S/Oromoo posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share