Kibet Town Government Communication Affairs Office

Kibet Town Government Communication Affairs Office ⏩እንኳን ወደ የተለያዩ ትኩስና ተአማኒነት ያላቸው ከተማዊ፣ ሀገራዊና ዓለምአቀፋዊ መረጃዎችን የሚያገኙበት ፔጃችን በሰላም መጡ⏪

የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መልዕክትየኢትዮጵያ ሕዝብ አስደናቂም ተአምረኛም ሕዝብ ነው። ከፈጣሪ በቀር ሕዝባችንን አሟልቶ ሊያውቅና ሊገመግም የሚችል ማን ነው? የዳበረ ባህል፣ ...
01/06/2026

የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መልዕክት

የኢትዮጵያ ሕዝብ አስደናቂም ተአምረኛም ሕዝብ ነው። ከፈጣሪ በቀር ሕዝባችንን አሟልቶ ሊያውቅና ሊገመግም የሚችል ማን ነው? የዳበረ ባህል፣ ሀገር ወዳድና የወል መሻቱን መጠበቅ የሚችል ሕዝብ መሆኑን በዘንድሮው ምርጫ ዳግም ለዓለም አሳይቷል። በዛሬው ታሪካዊ ዕለት፡-
• የሌሊቱ ብርድና ጨለማ ያላስፈራቸው፣
• የቀትሩ ፀሐይና ድንገተኛ ዝናብ ያልበገራቸው
• ሠርግ፣ ኀዘን፣ ወሊድና ሌሎች ማኅበራዊ ሁነቶች ያላገዳቸው፣
• ረጃጅም ሰልፎች ያላታከታቸው፣
• የአካል ጉዳት ድምጽ ለመስጠት ያልገደባቸው፣
• ሕመም እና እርጅና የሀገር ተስፋን ከማየት ያላገዳቸው፣
• የነገ ሀገር ተረካቢ ጨቅላ ልጃቸውን ማዘል ያላደከማቸው፣
• ከምንም በላይ የጠላት ጩኸትና ማስፈራሪያ ያላስቆማቸው ዜጎች፤
በብዙ ውጣ ውረዶች መካከል (against all odds) ያሳያችሁት ጽናት ለዴሞክራሲና ለሀገር ሕልውና የተከፈለ ነውና ከልብ የመነጨ ምስጋና ይገባቸዋል፡፡

ይሄንን ሕዝብ ማገልገል መታደል ነውና ተመራጮች ያከበራችሁን አክብራችሁ ለዴሞክራሲ ሥርዓት ዋጋ የከፈለውን ይሄንን ሕዝብ በንጽሕና ለማገልገል ያብቃችሁ።

01/06/2026
01/06/2026
የዘንድሮው ሀገራዊ የምርጫ ሂደት ዜጎች የሚፈልጉትን ፓርቲ ፍፁም ሰላማዊና ነፃ በሆነ አግባብ መምረጥ ያስቻለ መሆኑን በቅበት ምርጫ ክልል ድምፅ የሰጡ የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲ አመራርና አባላ...
01/06/2026

የዘንድሮው ሀገራዊ የምርጫ ሂደት ዜጎች የሚፈልጉትን ፓርቲ ፍፁም ሰላማዊና ነፃ በሆነ አግባብ መምረጥ ያስቻለ መሆኑን በቅበት ምርጫ ክልል ድምፅ የሰጡ የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲ አመራርና አባላት ገለፁ!

ግንቦት 24/2018

በምርጫ ክልሉ ወራቤ ከተማ ከተማ ልማት አካባቢ ተገኝተው ድምጽ የሰጡት የኢፌዴሪ ስራና ክህሎት ሚኒስቴር ሚንስትር ጊስት ሙፈሪሃት የኢፌድሪ ስራና ክህሎት ሚኒስቴር ሚንስትር ጊስት ሙፈሪሃት ካሚል
ምርጫ ማለት የአንድ ሀገር የዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታ መሳሪያና የህዝቦች መሻት ማፅኚያ መንገድ መሆኑን ተናግረዋል።

በዛሬው እለት በሀገራችን የተካሄደው ምርጫም ህዝቡ የፈለገውን መምረጥ እንደሚችል የታየበትና ምርጫ ሂደቱም ሰላማዊ፣ ፍትሃዊና ዲሞክራሲያዊ እንደነበረ ጊስት ሙፈሪሃት ገልፀዋል።

ሀገራችን ከውስጥም ከውጭም እያጋጠሟት ያሉ ችግሮችን እየተጋፈጠች ባለችበት በአሁኑ ወቅት ምርጫውን በዚህ ልክ ማሳካት ተጫማሪ ድሏን ለማፅናት ያላትን ፅናት የሚያረጋግጥ ነው ያሉት ሚኒስትሯ ከምርጫው በኋላም የምርጫው ተዋናዮች የምርጫ ህጉን በማክበር ውጤቱን በፀጋ መቀበል ያስፈልጋል ብለዋል።

ምርጫ የአንድን ሀገር የፓሊሲ አማራጭ፣ ፍትህ፣ ልማትንና የዜጎች ፍላጎት ማረጋገጫ መሳሪያ መሆኑን የገለፁት የነእፓ ምክትል ሊቀመንበር አቶ ዘኑር አብዱልዋሀብ የምርጫ ድምፅ አሰጣጥ ሂደቱ የምርጫ ቦርድ ደንብና መመሪያን የተከተለና መራጮች ድምፃቸውን ሰላማዊና ነፃ በሆነ መንገድ ለፈለጉት ፓርቲ ሲሰጡ የታዘቡበት ምርጫ መሆኑን ተናግረዋል።

የኢዜማ ፓርቲ ተወካይ የሆኑት አቶ መሀመድ ባርሰባ የምርጫ ሂደቱን አስመልክተው በሰጡን አስተያየት ሀገረመንግስት የሚነባበት፣ ዜጎች ለሚፈልጉትና ዮነኛል ለሚሉት ፓርቲ ፍላጎታቸውን የሚገልፁበት መንገድ መሆኑን አስረድተዋል።

የዘንድሮው የሀገራችን የምርጫ ሂደትም አካታች፣ ሀገራችን ለምታካሄደው የዲሞክራሲ-ስርዓተ ግንባታ የልምምድ ጥረት መሳያና ሁሉም ዜጋ ፍላጎቱን በነፃነት ያንፀባረቀበት ክስተት መሆኑን አብራርተዋል።

የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎችና የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲ አባላትና ደጋፊዎች እንዳሉት የዘንድሮው ምርጫ በዚህ ልክ ነፃ፣ ዲሞክራሲያዊና ፍትሃዊ መሆኑ የሀገራችን የዲሞክራሲ ባህል ምን ያክል እየጎለበተ መምጣቱን የሚያሳይ መሆኑን ተናግረዋል። ስ/ዞ/መ/ኮ

የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ድምጽ አሰጣጥ ሒደት ሰልፍ ይዘው የቆዩ መራጮች እስኪመርጡ ይቀጥላል - ቦርዱአዲስ አበባ፣ ግንቦት 24፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የድምፅ መስጠት ሒደቱ ከ12 ሰዓት በፊት...
01/06/2026

የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ድምጽ አሰጣጥ ሒደት ሰልፍ ይዘው የቆዩ መራጮች እስኪመርጡ ይቀጥላል - ቦርዱ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 24፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የድምፅ መስጠት ሒደቱ ከ12 ሰዓት በፊት ሰልፍ ይዘው የቆዩ መራጮች እስኪመርጡ ይቀጥላል አለ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ፡፡

በዛሬው ዕለት ከጠዋት 12 ሰዓት ጀምሮ እየተካሄደ በሚገኘው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሕዝቡ በነቂስ በመውጣት ድምጹን እየሰጠ ይገኛል፡፡

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዛሬ ሰኞ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ከማለዳ 12 ሰዓት ጀምሮ የ7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ድምፅ የማስፈጸም ሒደት ላይ መሆኑ ይታወቃል።

ቦርዱ ድምፅ የመስጠት ሒደቱ እስከ 12 ሰዓት ሠልፍ ላይ የነበረው ድምፅ ሰጪ ድምፅ ሰጥቶ እስኪጠናቀቅ ድረስ ድምፅ የመስጠት ሒደቱ እንደሚቀጥል አስታውቋል።

ዐዋጅ 1162/2011 አንቀጽ 49 (4) መሠረት ቦርዱ በልዩ ሁኔታ የድምፅ መስጫ ሰዓት ሊያራዝም እንደሚችል ይደነግጋል።

የኢፌድሪ ስራና ክህሎት ሚኒስቴር ሚንስትር ጊስት ሙፈሪሃት ካሚል በስልጤ ዞን ቅበት ምርጫ ክልል ሉመያ ቁጥር አንድ/ከተማ ልማት አካባቢ ምርጫ ጣቢያ ድምፃቸውን ሰጥተዋል።ምርጫ ማለት የዲሞክራ...
01/06/2026

የኢፌድሪ ስራና ክህሎት ሚኒስቴር ሚንስትር ጊስት ሙፈሪሃት ካሚል በስልጤ ዞን ቅበት ምርጫ ክልል ሉመያ ቁጥር አንድ/ከተማ ልማት አካባቢ ምርጫ ጣቢያ ድምፃቸውን ሰጥተዋል።

ምርጫ ማለት የዲሞክራሲ ስርዓት መገንቢያ መሳሪያና የህዝቦች መሻት ማፅኚያ መንገድ ነው በማለት በዛሬው እለትም የተደረገው ምርጫ ህዝቡ የፈለገውን መምረጥ እንደሚችል ማረጋገጫ መሆኑን ጊስት ሙፈሪሃት ተናግረዋል።

24/09/22018 ስልጤ ዞን መን ኮሚ

ዓለም አቀፍ ታዛቢዎች የድምፅ አሰጣጥ ሂደቱን እየተመለከቱ ነው አዲስ አበባ፣ ግንቦት 24፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት (ኢጋድ) የምርጫ ታዛቢ ቡድን አ...
01/06/2026

ዓለም አቀፍ ታዛቢዎች የድምፅ አሰጣጥ ሂደቱን እየተመለከቱ ነው

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 24፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት (ኢጋድ) የምርጫ ታዛቢ ቡድን አባላት በድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር እየተካሄደ የሚገኘውን የድምፅ አሰጣጥ ሂደት እየተመለከቱ ነው።

በምርጫ ክልል የተለያዩ ጣቢያዎች ማሕበረሰቡ ከማለዳው ጀምሮ ድምጹን እየሰጠ ይገኛል።

በቲያ ኑሬ

#ኢትዮጵያ #ኢትዮጵያእየመረጠችነው #በምርጫብቻ #ፋናዲጂታል

በስልጤ ዞን ቅበት ከተማ አስተዳደር የ7ኛው ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ የድምጽ አሰጣጥ ስነ-ስርዓት በምስል!-----------------------‎‎ግንቦት 24/2018 ቅበት ከተማ መንግሥት ኮሙኒ...
01/06/2026

በስልጤ ዞን ቅበት ከተማ አስተዳደር የ7ኛው ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ የድምጽ አሰጣጥ ስነ-ስርዓት በምስል!
-----------------------
‎‎ግንቦት 24/2018 ቅበት ከተማ መንግሥት ኮሙኒኬሽን
‎-----------------------

01/06/2026

Address

Silte Zone Kibet Ketema Astedader
Kibet

Opening Hours

Monday 09:00 - 17:00
Tuesday 10:00 - 17:00
Wednesday 09:00 - 17:00
Thursday 09:00 - 17:00
Friday 09:00 - 17:00
Saturday 09:00 - 17:00
Sunday 09:00 - 17:00

Telephone

+251954201649

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Kibet Town Government Communication Affairs Office posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share