Kibet Town Government Communication Affairs Office

Kibet Town Government Communication Affairs Office ⏩እንኳን ወደ የተለያዩ ትኩስና ተአማኒነት ያላቸው ከተማዊ፣ ሀገራዊና ዓለምአቀፋዊ መረጃዎችን የሚያገኙበት ፔጃችን በሰላም መጡ⏪

03/09/2026
በስልጢ ወረዳ ከ18 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተገነባው የሶላር ሲስተም የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ተመረቀ!‎‎​በስልጤ ዞን ስልጢ ወረዳ በአሳኖ ዱግደሬራ ቀበሌ በ«ዳይሬክት ኤድ» (Direct Ai...
03/09/2026

በስልጢ ወረዳ ከ18 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተገነባው የሶላር ሲስተም የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ተመረቀ!

‎​በስልጤ ዞን ስልጢ ወረዳ በአሳኖ ዱግደሬራ ቀበሌ በ«ዳይሬክት ኤድ» (Direct Aid) የበጎ አድራጎት ድርጅት በ18.5 ሚሊዮን ወጪ የተገነባውና ከ4 ሺህ በላይ ነዋሪዎችን የንጹህ መጠጥ ውሃ ተጠቃሚ የሚያደርገው የሶላር ሲስተም የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆኗል።

‎​በምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ ተገኝተው የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ውሃና ማዕድን ቢሮ ምክትል ኃላፊ ወ/ሮ አለይካ ሽኩር፤ በአሳኖ ዱግደሬራ ቀበሌ እውን የሆነው ይህ የውሃ ፕሮጀክት የህብረተሰቡን የረጅም ጊዜ ጥያቄ በዘላቂነት የፈታ መሆኑን ተናግረዋል።

‎የዞኑ የመጠጥ ውሃ ሽፋን ከክልልም ሆነ ከመዋቅር አንጻር አሁንም ዝቅተኛ ደረጃ ላይ እንደሚገኝ ያነሱት ወ/ሮ አለይካ፣ ግብረ-ሰናይ ድርጅቶች በዞኑ እንዲንቀሳቀሱ የሚደረገው ይህንኑ የውሃ አቅርቦት ችግር ታሳቢ በማድረግ እንደሆነ አብራርተዋል።

‎​እንደ ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል 47 ከመቶ የሚሆነው ማህበረሰብ አሁንም የንጹህ መጠጥ ውሃ ሽፋን እንዳላገኘ የጠቆሙት ምክትል ቢሮ ኃላፊዋ፤ መንግስት ከመንግስታዊ ካልሆኑ አጋር ድርጅቶችና ከህብረተሰቡ ጋር በመቀናጀት የመጠጥ ውሃ ተደራሽነትን ለማስፋፋት በትኩረት እንደሚሰራ ገልጸዋል።

‎አክለውም ህዝቡ ከብዙ ጥረትና ልፋት በኋላ እውን የሆነውን ይህን የልማት አውታር በባለቤትነት ስሜት እንዲጠብቅና እንዲንከባከብ መልእክት አስተላልፈዋል።

‎​የስልጤ ዞን መንግስት ዋና ተጠሪና የብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ወ/ሮ ነኢማ ሙኒር በበኩላቸው፤ ውሃ የህይወት፣ የጤና እና የልማት መሰረት በመሆኑ የመጠጥ ውሃ ሽፋንን ባጠረ ጊዜ ለማሻሻል ከልማት አጋሮች ጋር የተቀናጀ አሰራር መዘርጋት ወሳኝ መሆኑን አሳስበዋል።

‎​ወ/ሮ ነኢማ አክለውም፤ በዞኑ ባለፉት ሁለት ዓመታት ለዘርፉ በተሰጠው ልዩ ትኩረት 22 የውሃ ፕሮጀክቶችን በማስመረቅ ለህዝብ ክፍት ማድረግ መቻሉን አውስተው፤ በ2018 ዓ.ም ብቻ 14 ፕሮጀክቶች ተጠናቀው ለአገልግሎት መበቃታቸውን ገልጸዋል።

‎በአሁኑ ወቅት 48% የደረሰውን የዞኑን የመጠጥ ውሃ ሽፋን በ2019 ዓ.ም መጨረሻ ወደ 58% ለማድረስ ታቅዶ እየተሰራ እንደሚገኝም ጠቁመዋል።

‎​ዛሬ የተመረቀውና ከ18.5 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተደረገበት የአሳኖ ፕሮጀክት፤ 30 ሺህ ሊትር የመያዝ አቅም ያለው ማጠራቀሚያ፣ 5 የውሃ ቦኖዎች እና 3.5 ኪሎ ሜትር የቱቦ ዝርጋታ ያለው እንደሆነ ተገልጿል።

‎​የስልጢ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሸምሴ ረዲ በበኩላቸው፤ ፕሮጀክቱ የአሳኖ ዱግደሬራ ቀበሌ ህዝብ ለረጅም ዓመታት ሲያነሳው የነበረውን የመጠጥ ውሃና የመልካም አስተዳደር ጥያቄ በዘላቂነት እንደመከተው ገልጸዋል።

‎የፕሮጀክቱ ልዩ ባህሪ በፀሐይ ኃይል (Solar Energy) የሚሰራ በመሆኑ ከነዳጅና ከመብራት ወጪ ነፃ የሆነና ዘመናዊ አሰራርን የተከተለ መሆኑን አስረድተዋል።

‎​አያይዘውም በወረዳው በ2018 ዓመት ብቻ ከ66 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ በማድረግ የተለያዩ የውሃ ልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የጠቆሙት ዋና አስተዳዳሪው፤ በዚህም ከ14,240 በላይ ነዋሪዎችን ተጠቃሚ በማድረግ የወረዳውን የመጠጥ ውሃ ሽፋን ወደ 37.7% ማሳደግ መቻሉን አብራርተዋል።

የ«ዳይሬክት ኤድ» የኢትዮጵያ ስራ አስፈጻሚ ሚስተር ጠሃ ማህሙድ ለፕሮጀክቱ እውን ማህን ማህበረሰቡና አማራሩ ላድረገላው ሁለንተናው ድጋፍ አመስግነዋል።

ዛሬ በአሳኖ ዱግደሬራ የተመረቀ በዞኑ አራተኛው ፕሮጀት እንደሆነ ገልጸው በቀጣይም የማህበረሰቡን ችግር የሚፈቱ ፕሮጀክቶችን እውን ለማድረግ እንደሚሰሩ ገልጸዋል።

‎​በምረቃ መርሃ-ግብሩ ላይ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ውሃና ማዕድን ቢሮ ምክትል ኃላፊ ወ/ሮ አለይካ ሽኩር፣የስልጤ ዞን መንግስት ዋና ተጠሪና የብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ወ/ሮ ነኢማ ሙኒር፣ የ«ዳይሬክት ኤድ» የኢትዮጵያ ስራ አስፈጻሚ ሚስተር ጠሃ ማህሙድ፣
‎የስልጤ ዞን መንግስት ረዳት ተጠሪና የፖለቲካና ሪዖት አለም ዘርፍ ሀላፊ አቶ ሁሴን ሱነሞ፣ የስልጤ ዞን ውሃ መምሪያ ሀላፊ አቶ ጨፋ ከድር የዞንና የወረዳ ከፍተኛ አመራሮች እንዲሁም የአካባቢው ነዋሪዎች የተገኙ ሲሆን፤ አመራሮቹ ለልማት አጋር ድርጅቱ «ዳይሬክት ኤድ» ላደረገው ሁለገብ ድጋፍ ከፍተኛ ምስጋና አቅርበዋል።

በስልጤ ዞን የቅበት ከተማ አስተዳደር ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ከከተማ ወጣቶችና ስፖርት ጽህፈት ቤት ጋር በመተባበር በከተማው የአስፓልት መንገድ ጠርዝ ቀለም የመቀባት ተግባር ማከናወናቸው...
03/09/2026

በስልጤ ዞን የቅበት ከተማ አስተዳደር ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ከከተማ ወጣቶችና ስፖርት ጽህፈት ቤት ጋር በመተባበር በከተማው የአስፓልት መንገድ ጠርዝ ቀለም የመቀባት ተግባር ማከናወናቸው ተገለፀ
--------------------
ነሓሴ 28/2018: ቅበት ከተማ መንግስት ኮሚኒኬሽን
--------------------

በከተማ ደረጃ የጳጉሜን ቀናት በተለያዩ ስያሜዎችና ዝግጅቶች ለማክበር ውይይት ተካሄደ--------------------ነሓሴ 28/2018: ቅበት ከተማ መንግስት ኮሚኒኬሽን -------------...
03/09/2026

በከተማ ደረጃ የጳጉሜን ቀናት በተለያዩ ስያሜዎችና ዝግጅቶች ለማክበር ውይይት ተካሄደ
--------------------
ነሓሴ 28/2018: ቅበት ከተማ መንግስት ኮሚኒኬሽን
--------------------
በቅበት ከተማ አስተዳደር የዘንድሮው የ2018 በጀት አመት መጨረሻ የሆኑት 5ቱ የጳጉሜ ቀናቶች በተለያዩ ስያሜዎችና ዝግጅቶች ለማክበር በእቅዱ ዙሪያ ዉይይት ተካሂዷል።

ለመድረኩ የተዘጋጀው የማስፈፀሚያ ሰነድ በከተማው ብልጽግና ፓርቲ ጽህፈት ቤት የመንግሥት ረዳት ተጠሪ በሆኑት አቶ ሸይቾ ሙስጠፋ በኩል ቀርቦ ሰፊ ውይይት ተደርጎበታል።

መድረኩ በቅበት ከተማ አስተዳደር የመንግሥት ዋና ተጠሪ አቶ መሀመድ ኑራቶ የተመራ ነው።

በመድረክ ኢትዮጵያ የራሷ የዘመን አቆጣጠር እና 13 ወር ያላት ብቸኛዋ ሀገር እንደመሆኗ ልዩ የሆነችዋን የጳጉሜ ወር በተሻለ አስተሳሰብና አመለካከት በማክበር ለቀጣይ አዲስ አመት የተሻለ ስራ ለመስራት በአዲስ ተስፋ የምንዘጋጅበት ወቅት ሊሆን ይገባል ተብሏል።

በመድረኩ የከተማው ምክር ቤት ዋና አፈ -ጉባኤ ወ/ሮ ዛሃራ ስርሞሎ እና የተቋም የስራ ሀላፊዎች ተገኝተዋል።

ምርጫችሁ ስላደረጋችሁን ከልብ እናመሰግናለን !!

‎ወቅታዊ ፣ ተዓማኒ ፣ ትኩስና ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት የተለያዩ የሚዲያ አማራጮችን ይከታተላሉ፣ ይወዳጁ👇👇

‎በፌስቡክ ፦ https://www.facebook.com/kibetketema

በቴሌግራም ፦ https://t.me/+E3gxQkJVy2kwNDc0

በቲክቶክ ፦ tiktok.com/

በዩቲዩብ ፦ https://www.youtube.com/

በትዊተር ፦ https://twitter.com/KibetGov1?t=p6xyHXeqVI6X8WU0gZp97A&s=01

በኢንስታግራም ፦ https://www.instagram.com/kibet_comm980?igsh=Z2E1bWVraTdiOXM0

ከስልጤ ዞን ፖሊስ መምሪያ የተወጣጡ የኢንስፔክሽን ቡድን በቅበት ከተማ አስተደደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት በመገኘት በተቋሙ በ2018 በጀት አመት የተከናወኑ ዝርዝር ተግባራት ላይ ድጋፍና ክትትል ...
02/09/2026

ከስልጤ ዞን ፖሊስ መምሪያ የተወጣጡ የኢንስፔክሽን ቡድን በቅበት ከተማ አስተደደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት በመገኘት በተቋሙ በ2018 በጀት አመት የተከናወኑ ዝርዝር ተግባራት ላይ ድጋፍና ክትትል አደረጉ
--------------------
ነሓሴ 27/2018: ቅበት ከተማ መንግስት ኮሚኒኬሽን
--------------------
ከስልጤ ዞን ፖሊስ መምሪያ የተወጣጡ የኢንስፔክሽን ቡድኖች በቅበት ከተማ አስተደደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት በመገኘት በተቋሙ በ2018 በጀት አመት የተከናወኑ ዝርዝር የእቅድ አፈጻጸም ተግባራት ላይ ድጋፍና ክትትል አድርገዋል።

የኢንስፔክሽን ቡድኑ በበጀት የተከናወኑ ዝርዝር ተግባራት የተቋሙን ተልዕኮ ያሳኩ እንደሆኑ የማህበረሰቡን ሰላም በመጠበቅ ረገድ አመርቂ ስራዎች መሰራታቸውን ተናግረዋል።

የፖሊስ ተቋም ዋና ግቡ ሰላማዊ ማህበረሰብ መፍጠር እንደሆነና ወንጀልን በመከላከልና ማህበረሰቡ በሰላም ወጥቶ እንዲገባ በበጀት አመቱ ውጤታማ ስራዎች እንደተሰራ በመግለጽ ቀጣይም ለተግባሮች ልዩ ትኩረት በመስጠት የማህበረሰቡን ሰላም በዘላቂነት መጠበቅ ይገባል ብለዋል።

በጥንካሬ የተሰሩ ስራዎችን አጠናክሮ በማስቀጠል የታዩ ጉድለቶችን ትኩረት ፈጥኖ በመቅረፍ ጠንካራ ተቋም መገንባት እንደሚገባ ተናግረዋል።

ተቋሙ ያከናወናቸውን ዝርዝር ተግባራት አደራጅቶ በፋይል በማደራጀት እንዲሁም የተጓደሉ ስራዎችን በማሟላት ውጤታማ ስራዎችን ሊሰራ እንደሚገባ ጠቁመዋል።

ወንጀልን ለመከላከል በየቀበሌያት የፖሊስ ማዕከላት የተገነቡና እውቅና የተሠጣቸው ስራ መጀመራቸውን አጠናክረው እንዲቀጥሉ እንዲሁም የፖሊስ ማዕከል በሌለባቸው ቀበሌዎች ቀጣይ 2019 ዓ/ም ታቅዶ መሠራት አለበትም ብለዋል።

የመረጃ ልውውጥን ማጠናከር፣ የፓትሮል ቅኝት ማጠናከር እንዲሁም የስጋት ቀጠናዎችን በዘላቂነት መፍታት የማህበረሰቡን ሰላም ለማረጋገጥ ወሳኝ ጉዳይ መሆኑን ገልጸዋል።

የትራፊክ አደጋን ለመከላከል እድሜያቸው ያልደረሰ አሽከርካሪዎችን ግንዛቤ መፍጠር እና ትርፍ የሚጭኑ ተሽከርካዎችን እርምጃ እየወሰዱ መሄድ ይገባል ብለዋል።

የቅበት ከተማ አስተደደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት አዛዥ ረ/ኢ አደም ሸረፈ እንዳሉ የድጋፍና ክትትል ኢንስፔክሽኑ በተቋሙ በአመቱ የተከናወኑ ተግባራት በዝርዝር ያዩበት መንገድ አበረታች እንደነበርና የተነሱ ነጥቦችን ወስዶ ለመፍታት ርብርብ ይደረጋል ብለዋል።

በበጀት አመቱ ፖሊስ ጽ/ቤቱ የተሰጠውን ተልዕኮ ለማሳካት በሁሉም ዘርፎች ይበልጥ የሚያሰይ ስራ መሰራቱን ተናግረዋል ሲል የቅበት ከተማ አስተደደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ህዝብ ግንኙነት ዘግቧል።

ነሐሴ 30 የሚመረቀውን የከንቲባ ቢሮ ግንባታ አስመልክቶ ከሀገር ሸማግሌና ከሀይማኖት አባቶች ጋር ውይይት ተካሄደ_____________ነሐሴ 27/2018: ቅበት ከተማ መንግስት ኮሚኒኬሽን።__...
02/09/2026

ነሐሴ 30 የሚመረቀውን የከንቲባ ቢሮ ግንባታ አስመልክቶ ከሀገር ሸማግሌና ከሀይማኖት አባቶች ጋር ውይይት ተካሄደ
_____________
ነሐሴ 27/2018: ቅበት ከተማ መንግስት ኮሚኒኬሽን።
_____________
የቅበት ከተማ አስተዳደር ነሐሴ 30 የሚመረቀውን የከንቲባ ቢሮ ግንባታ በማስመልከት በከተማ ደረጃ የሚከናወኑ ልዩ ልዩ የቅድመ ዝግጅት ተግባራት ዙሪያ ከሀገር ሸማግሌና ከሀይማኖት አባቶች ጋር ውይይት ተካሂዷል።

መድረኩ በቅበት ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ መለሰ ዘይኔ የተመራ ነው።

የሀገር ሸማግሌና የሀይማኖት አባቶች በማሳተፍ የተካሄደው መድረክ የምረቃ ሂደቱ ውጤታማ ሆኖ መጠናቀቅ እንዲችል ያለመ ሲሆን የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን በቅርበት እየገመገሙ የምረቃ ሂደቱን በሚመጥን ልክ መካሄድ እንዳለበትም ተመላክቷል።

በተለይ እንግዶች ለምረቃ ሰነ ሰርዓቱ ሲመጡ ቱባውን የስልጤ ህዝብ እንግዳ አቀባበል ባህልና እሴት በሚያጎሉ እንዲሁም አብሮነትን በሚያጠናክሩ መርሃ ግብሮች አቀባበል መደረግ እንዳለበት የተገለጸው

ምርጫችሁ ስላደረጋችሁን ከልብ እናመሰግናለን !!

‎ወቅታዊ ፣ ተዓማኒ ፣ ትኩስና ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት የተለያዩ የሚዲያ አማራጮችን ይከታተላሉ፣ ይወዳጁ👇👇

‎በፌስቡክ ፦ https://www.facebook.com/kibetketema

በቴሌግራም ፦ https://t.me/+E3gxQkJVy2kwNDc0

በቲክቶክ ፦ tiktok.com/

በዩቲዩብ ፦ https://www.youtube.com/

በትዊተር ፦ https://twitter.com/KibetGov1?t=p6xyHXeqVI6X8WU0gZp97A&s=01

በኢንስታግራም ፦ https://www.instagram.com/kibet_comm980?igsh=Z2E1bWVraTdiOXM0

በሁሉም ዘርፍ ተግባራዊ በመደረግ ላይ የሚገኘው የክረምት በጎ ፈቃድ ስራ ተጠናክሮ ቀጥሏል----------------------ነሐሴ 27/2018: ቅበት ከተማ መንግስት ኮሚዩኒኬሽን -------...
02/09/2026

በሁሉም ዘርፍ ተግባራዊ በመደረግ ላይ የሚገኘው የክረምት በጎ ፈቃድ ስራ ተጠናክሮ ቀጥሏል
----------------------
ነሐሴ 27/2018: ቅበት ከተማ መንግስት ኮሚዩኒኬሽን
------------------------
በስልጤ ዞን የቅበት ከተማ አስተዳደር ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ከከተማ ወጣቶችና ስፖርት ጽህፈት ቤት ጋር በመተባበር በከተማው የእግረኛ ማቋራጫ ዜብራ ቅብ ተግባር ማከናወኑን አስታውቋል።

የቅበት ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ መለሰ ዘይኔ፣ የከተማው ብልጽግና ፓርቲ ጽህፈት ቤት ዋና የመንግስት ተጠሪ አቶ መሀመድ ኑራቶ እና የጽህፈት ቤቱ ባለሙያዎች እንዲሁም ከበጎ ፍቃደኛ ወጣቶች ጋር በመሆን የእግረኛ ማቋረጫ ዜብራ መንገድ የቀለም ቅብ እድሳት ማከናወናቸው ተመላክቷል።

የእግረኞች መንገድ ማቋረጫ ዜብራ በየወቅቱ ማደስ በትራፊክ አደጋ ምክንያት በሰው ሂይወትና በንብረት ላይ የሚደርሱ አደጋዎችን ለመቀነስ እንደሚያግዝ ነው የተገለጸው።

በዚህም እግረኞች መንገድ ሲያቋርጡ የዜብራ መንገድን ተጠቅመው በማቋረጥ ከትራፊክ አደጋ ራሳቸውን መከላከል እንዳለባቸው እና አሽከርካሪዎችም ለእግረኞች ቅድሚያ በመስጠት የድርሻቸውን ሊወጡ እንደሚገባ መልዕክት ተላልፏል።

በዕለቱ ዜብራ ቅብ የከተማው ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ጽህፈት ቤት ሀላፊ አቶ አብዲ ባድላላ፣ የከተማው ወጣቶችና ስፖርት ጽህፈት ቤት ሀላፊ አቶ ሁሴን አማን እንዲሁም የወጣቶች ክንፍ ሀላፊ አቶ ፋሪስ ከድር እና በጎ ፍቃደኛ ወጣቶች ተሳትፈዋል።

ምርጫችሁ ስላደረጋችሁን ከልብ እናመሰግናለን !!

‎ወቅታዊ ፣ ተዓማኒ ፣ ትኩስና ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት የተለያዩ የሚዲያ አማራጮችን ይከታተላሉ፣ ይወዳጁ👇👇

‎በፌስቡክ ፦ https://www.facebook.com/kibetketema

በቴሌግራም ፦ https://t.me/+E3gxQkJVy2kwNDc0

በቲክቶክ ፦ tiktok.com/

በዩቲዩብ ፦ https://www.youtube.com/

በትዊተር ፦ https://twitter.com/KibetGov1?t=p6xyHXeqVI6X8WU0gZp97A&s=01

በኢንስታግራም ፦ https://www.instagram.com/kibet_comm980?igsh=Z2E1bWVraTdiOXM0

የቅበት ኮንስትራክሽንና ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ ተመራቂ ተማሪዎች የምስጋናና የዕውቅና ፕሮግራም አካሄዱበስልጤ ዞን የቅበት ኮንስትራክሽንና ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ በተለያዩ የሙያ መስኮች ያሰለጠናቸው...
01/09/2026

የቅበት ኮንስትራክሽንና ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ ተመራቂ ተማሪዎች የምስጋናና የዕውቅና ፕሮግራም አካሄዱ

በስልጤ ዞን የቅበት ኮንስትራክሽንና ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ በተለያዩ የሙያ መስኮች ያሰለጠናቸውን ተማሪዎች የምረቃ፣ የምስጋናና የዕውቅና ስነ-ስርዓት በደመቀ ሁኔታ አካሂዷል።

የኮሌጁ ዋና ዲን አቶ አብዱረዛቅ በሽር ባስተላለፉት መልዕክት፤ ተመራቂዎች ያገኙትን ዕውቀት ተጠቅመው ሥራ ከመጠበቅ ይልቅ ራሳቸው የሥራ ዕድል ፈጣሪ መሆን እንዳለባቸውና በየአካባቢያቸው ጥሩ አምባሳደር ሆነው እንዲያገለግሉ ጥሪ አቅርበዋል።

የኮሌጁ ምክትል ዲን አቶ ነስረዲን አብደላህ በበኩላቸው ሰልጣኞቹን ብቁ ለማድረግ የኮሌጁ ማህበረሰብ ላደረገው ጥረት ምስጋና አቅርበው፣ ተማሪዎች የቴክኒክና ሙያ ትምህርቱን በጥራት አጠናቀው ለዚህ በመብቃታቸው ያላቸውን አድናቆት ገልጸዋል።

ተማሪዎች ይህንን የምስጋና ፕሮግራም በማዘጋጀታቸው መደሰታቸውን የገለፁት የኮሌጁ ምክትል ዲን አቶ ፈጅረዲን ሱልጣን እንዲህ አይነቱ ተግባር የእርስበርስ መከባበርንና አንድነትን የሚያጠናክርና ለአሰልጣኞች እንዲሁም ለኮሌጁ አመራር አካላት ትልቅ መነቃቃትን ይፈጥራል ብለዋል።

በፕሮግራሙ ተመራቂ ተማሪዎች በትምህርት ቆይታቸው ላደረጉላቸው ያልተቆጠበ ድጋፍና ክትትል ለኮሌጁ አመራሮች እና ለአሰልጣኝ መምህራኖቻቸው ልባዊ ምስጋናቸውን በማቅረብ የዕውቅና ሽልማት አበርክተዋል።

በተጨማሪም በትምህርት ክፍለ-ጊዜያቸው አብረዋቸው ለነበሩና ልዩ ድጋፍ ለሚሹ ተማሪዎች ልዩ ዕውቅና በመስጠት የወንድማማችነት እና የጋራ አብሮነት እሴታቸውን በተግባር አሳይተዋል።

ተመራቂ ተማሪዎቹ በተለያዩ ጊዚያት ስራዎቻቸውን በማጉላት ከጎናቸው ለነበሩት እንዲሁም የምረቃ ፕሮግራሙን ሚዲያ ሽፋን ሲሰጡ ለነቀሩ የቅበት ከተማ የመንግስት ኮሚዩኒኬሽንና ለስልጢ ወረዳ መንግስት ኮሚዩኒኬሽን ፅ/ቤቶች የምስጋና ሰርተፍኬት አበርክተዊል።

በምስጋና ፕሮግራሙ ላይ የቅበት ከተማ አስተዳደር ዋና የመንግስት ተጠሪ አቶ መሀመድ ኑራቶ ረዳት: የመንግስት ተጠሪ ወ/ሮ ሸሚማ ኑሪ : የኮሌጁ ዋና ዲን አቶ አብዱረዛቅ በሽር:ምክትል ዲን አቶ ነስረዲን አብደላ የኮሌጁ አስተዳደር ባለሙያዎችና ተመራቂ ተማሪዎች ተገኝተዋል።

  ---------------
01/09/2026


---------------

Address

Silte Zone Kibet Ketema Astedader
Kibet

Opening Hours

Monday 09:00 - 17:00
Tuesday 10:00 - 17:00
Wednesday 09:00 - 17:00
Thursday 09:00 - 17:00
Friday 09:00 - 17:00
Saturday 09:00 - 17:00
Sunday 09:00 - 17:00

Telephone

+251954201649

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Kibet Town Government Communication Affairs Office posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share