ኮንሶ ዞን ሥራና ክህሎት መምሪያ Konso Zone Labor and Skills Department

  • Home
  • Ethiopia
  • Konso
  • ኮንሶ ዞን ሥራና ክህሎት መምሪያ Konso Zone Labor and Skills Department

ኮንሶ ዞን ሥራና ክህሎት መምሪያ Konso Zone Labor and Skills Department በዞናችን የወጣቱን ስራ ክህሎትና የስራ ፈጣሪነት አመለካከት በማጎልበት የቁጠባ ባህሉን በማሻሻል የስራ አጥነት ችግሩን መቅረፍ።

27/08/2026
 :- በኮንሶ ዞን ካራት ከተማ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ጽ/ቤት  ከዞኑ ሥራና ክህሎት መመሪያ ጋር በመተባበር ለሠራተኞችና አመራር "ብልሹ አሠራርን መከላከል ይቻላል "በሚል ሪዕስ ሥልጠና ሰ...
21/08/2026

:- በኮንሶ ዞን ካራት ከተማ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ጽ/ቤት ከዞኑ ሥራና ክህሎት መመሪያ ጋር በመተባበር ለሠራተኞችና አመራር "ብልሹ አሠራርን መከላከል ይቻላል "በሚል ሪዕስ ሥልጠና ሰጠ ።

የሥልጠና መድረኩን በንግግር የከፈቱት የከተማው ምክትል ከንቲባና የጽ/ቤቱ ኃላፊ አቶ ተስፋዬ ገለቦ፣ ያለንበት ዘመን የመልካም አስተዳደር ችግር የገነገነበት፣ባለሙያው ለተጣለበት ኃላፊነት ዋጋ የማይሰጥበት ሁኔታ ውስጥ የገባንበት ስለሆነ ከጽ/ቤታችን ጀምረን ሥር-ነቀል ለውጥ ማምጣት ይጠበቅብናል ብለዋል።

በመቀጠል የዞን ሥራና ክህሎት መምሪያ ሥነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና መከታትያ ቡድን መሪ አቶ ሔኖክ በየነ"ሥነ-ምግባርና ሙስና" በሚል ሠነድ ሥልጠና የሠጡ ስሆን፣በሥነ-ምግባር ምንነትን በዝርዝር፣የሙስና ምንነት፣የመከላኪያ ዜዴዎ፣የእርማት ደረጃዎችና የዕርማት ዓላማዎች ላይ አትኩረው ሰፊ ግንዛቤ ለማስጨበጥ ጥረዋል።

የዞኑ ሥራና ክህሎት መምሪያ የማስፈጸም አቅም ግንባታ ባለሙያ አቶ አብርሃም ኦርካይዶ :- በቲም ምንነት፣እንደት ይደራጃል፣ጥቅሙስ በምሉ ሐሳቦች ላይ አተኩረው ሥልጠና ተሰጥተዋል።

በመቀጠል ተሳታፊዎቹ በሁለቱ ሠነዶች በቀረበው ሥልጠና ላይ ጥያቄና አስተያየት እንድያነሱ ዕድል የተሰጠ ስሆን፣የውይይት መድረኩን የዞን ሥራና ክህሎት መመሪያ የሥነ-ምግባርና
የፀረ-ሙስና መከታትያ ቡድን መሪ የሆኑት አቶ ሔኖክ በየነና የጽ/ቤቱ ኃላፊ አቶ ተስፋዬ ገለቦ መርተዋል።

በመጨረሻ ተሰብሳቢዎች በሁለቱ ሠነዶች በተሰጡት ሥልጠናዎች ላይ ጥያቄና አስተያየት አንስተው፣
የመድረክ መሪዎቹ በተነሱት አስተያየቶችና ጥያቄዎች ላይ ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተው የመድረኩ መደምደሚያ ሆነዋል።

ነሀሰ 15/2018 ዓ.ም
የYouTube https://www.youtube.com/ subscribe በማድረግ

የpage
https://www.facebook.com/profile.php?id=100068159616347&mibextid=ZbWKwL like and Sher በማድረግ ቤተሰብ በመሆን መረጃ ይከታተላሉ!

መረጃው፦
የካራት ከተማ አሰተዳደር መንግስት ኮሚኒኬሽን አገልግሎት ዩኑት ነው

21/08/2026

የኢንተርፕራይዞች አዲሱ የእድገት መንገድ፡ ከባህላዊ ገበያ ወደ ዲጂታል ምህዳር

ዲጂታል ቴክኖሎጂ የንግድ አሠራርን በከፍተኛ ሁኔታ እየቀየረ ባለበት በዚህ ዘመን፣ ምርትን ከመሸጥ ይልቅ ገበያ ማግኘት ትልቁ ፈተና ሆኗል። ይህንን መዋቅራዊ ለውጥ ተከትሎ፣ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የኢንተርፕራይዞችን የገበያ ትስስር ከማስፋት ባሻገር ዲጂታል ገበያን እንደ አዲስ የንግድ መድረክ ለማስፋፋት በትኩረት እየሰራ ይገኛል።

ለአንድ ኢንተርፕራይዝ እድገትና ዘላቂነት ምርት ማምረት ብቻውን በቂ አይደለም። ምርቱን ተደራሽ የሚያደርግበት ሰፊ ገበያ፣ ገዢ እና ሁለቱን የሚያገናኝ ቀልጣፋ የግብይት ሥርዓት ካልተዘረጋ፣ የምርት አቅም ብቻውን ወደ ተሻለ ንግድ ሊያሸጋግር አይችልም።

ይህንን እውነታ በመገንዘብ ሚኒስቴሩ ባለፉት አምስት ዓመታት የገበያ ትስስርን ማጠናከር ከትኩረት መስኮቹ አንዱ አድርጎ ሲሰራ ቆይቷል። በዚህም በ5 ዓመቱ ዕቅድ 252 ቢሊዮን ብር የገበያ ትስስር ለመፍጠር ታቅዶ፣ 295 ቢሊዮን ብር (116%) ማስመዝገብ ተችሏል። በዚሁ ሂደትም ከ1.2 ሚሊዮን በላይ ኢንተርፕራይዞችን የዕድሉ ተጠቃሚ ማድረግ ተችሏል።

ከዚህም በላይ ኢንተርፕራይዞች ተጠቃሚ ለማድረግ ወደ ዲጂታል የገበያ አማራጮች መግባት አማራጭ የሌለው ጉዳይ ነው፡፡

በባህላዊ የገበያ አሠራር አንድ ኢንተርፕራይዝ ምርቱን ለማስተዋወቅ አካላዊ ቦታ፣ የገበያ መድረክ ወይም በቀጥታ ገዢ መፈለግ ይጠይቅ ነበር። ዲጂታል ገበያ ግን ይህንን ሂደት በቴክኖሎጂ በማስተሳሰር ምርትን ከገዢ ጋር በፍጥነትና በሰፊ የገበያ ክልል ማገናኘት ያስችላል።

ኢንተርፕራይዞች በሀገር ውስጥም ሆነ በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ እንዲሆኑ ለማስቻል ሚኒስቴሩ በኢትዮጵያ የሥራ ገበያ መረጃ ሥርዓት (LMIS) በኩል ያበለጸገው «ሉሲ» (Lucy) ዲጂታል ገበያ ሁነኛ ማሳያ ነው። ሉሲ ዲጂታል ገበያ ኢንተርፕራይዞች ምርትና አገልግሎታቸውን በዲጂታል መድረክ ላይ እንዲያስገቡ፣ እንዲያስተዋውቁና ለተጠቃሚዎች እንዲያቀርቡ የሚያስችል ዘመናዊ መድረክ ነው።

እስካሁን ባለው እንቅስቃሴ ከ3,000 በላይ ኢንተርፕራይዞች ፕላትፎርሙን ተቀላቅለዋል። ይህ ቁጥር በቁጥር ብቻ የሚለካ ሳይሆን፣ ከአሮጌው አሠራር ወደ ዘመናዊው የዲጂታል ንግድ ሥነ-ምህዳር እየተደረገ ያለውን መዋቅራዊ ሽግግር ያመላክታል። ፕላትፎርሙ በአካባቢው ብቻ ተወስኖ ይሸጥ የነበረን ምርት በዲጂታል መድረክ በማስተዋወቅ ከመላው ዓለም ጋር ለማገናኘት ትልቅ ዕድል ፈጥሯል።

ዲጂታል ገበያ የሚሰጠው ዕድል የምርት ማስተዋወቂያ ብቻ አይደለም፤ የገዢና ሻጭ መረጃን ማሰባሰብ፣ የገበያ ፍላጎትን መረዳት፣ የምርት ጥራትን ማሻሻል እና የንግድ ውሳኔዎችን በመረጃ ላይ መመስረትም የሥርዓቱ አካል ናቸው።

በአሁኑ ወቅት ይህ አዲስ አሠራር በአዲስ አበባ ከተማ በልዩ ንቅናቄ እየተመራ ይገኛል። አሠራሩ ይበልጥ ውጤታማ እንዲሆንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች በስፋት እንዲጠቀሙበት የዲጂታል ክህሎት ግንባታ፡ የጥራት እና አቀራረብ ማሻሻያ፡ የምርት ጥራትና የዲጂታል ክፍያ ሥርዓት ድጋፎች ተጠናክረው ሊቀጥሉ ይገባል፡፡

19/08/2026
በዛሬው ቀን ማለትም ነሐሴ 12/2018 ዓ.ም በኬና ወረዳ ሥራና ክህሎት ጽ/ቤት በመገኘት ድጋፋዊ ክትትል አድርገናል። በክትትሉም በዋናነት የእስከአሁን የሥራ አጥ ወጣቶች ልየታ፣ የግንዛቤ ሥ...
18/08/2026

በዛሬው ቀን ማለትም ነሐሴ 12/2018 ዓ.ም በኬና ወረዳ ሥራና ክህሎት ጽ/ቤት በመገኘት ድጋፋዊ ክትትል አድርገናል። በክትትሉም በዋናነት የእስከአሁን የሥራ አጥ ወጣቶች ልየታ፣ የግንዛቤ ሥራዎች፣ የሥራ ሥምርት፣ የELMIS ምዝገባ፣ ቁጠባ፣ ብድር ስርጭትና አመላለስ እንድሁም በጽ/ቤቱ በክረምት በጎ ፈቃድ የተሰሩ ተግባራት ታይተዋል። በውይይቱም ጠንካራና ደካማ ጎኖችን በመለየት በቀጣይ ትኩረት የምሹ ጉዳዮችን በመለየት የጋራ መግባባት ተፈጥሯል።

Address

Ethiopia, South Ethiopia Regional State
Konso

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ኮንሶ ዞን ሥራና ክህሎት መምሪያ Konso Zone Labor and Skills Department posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share