Konso Zone Karat Zuria Woreda Prosperity Party

Konso Zone Karat Zuria Woreda Prosperity Party በኮንሶ ዞን የካራት ዙሪያ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት

በካራት ዙሪያ ወረዳ የ2018 የበጀት ዓመት የፓርቲና የመንግስት ስራዎች አፈፃፀም ግምገማ እና የአመራር ምዘና መድረክ ተጠናቀቀ፦ #ካራት ዙሪያ ወረዳ: ነሐሴ 09/2018 ዓ.ም (ካዙወመኮአገ...
15/08/2026

በካራት ዙሪያ ወረዳ የ2018 የበጀት ዓመት የፓርቲና የመንግስት ስራዎች አፈፃፀም ግምገማ እና የአመራር ምዘና መድረክ ተጠናቀቀ፦

#ካራት ዙሪያ ወረዳ: ነሐሴ 09/2018 ዓ.ም
(ካዙወመኮአገ/ት)

በኮንሶ ዞን ካራት ዙሪያ ወረዳ "ትጋት ለላቀ ስኬት'' በሚል መሪ ቃል ለ3 ተከታታይ ቀናት ሲያካሄድ የነበረውን የ2018 በጀት አመት የፓርቲና የመንግስት ስራዎች አፈፃፀም እና የአመራር ምዘና መድረክ ተጠናቋል።

በመድረኩም የኮንሶ ዞን ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ መምሪያ ኃላፊ ክብርት ወ/ሮ አስቴር ኩሲያ እንደገለፁት፤ግምገማው አንድነትና ቅንጅታዊ አሰራር በማጠናከር ተቋም ማሻገር ላይ በቀጣይ አመራሩ በግምገማውና በምዘናው መሰረት ጉድለቱን በማረም ጥንካሬውን በማስቀጠል ብሎም በመግባባት ሊሰራ እንደሚገባም አቅጣጫ አስቀምጠዋል።

አክለውም የትኛውም ስኬታማ ተግባር የጋራ የቅንጅት ስራ ውጤት እንደመሆኑ በቀጣይም የበለጠ ቅንጅታዊ አሰራርን አጠናክሮ በመስራት የማህበረሰቡ ተጠቃሚነት ማስፋት ላይ አቅዶ መስራት እንደሚገባ ጠቁመዋል፡፡

የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ ክቡር አቶ ኩሴ ጭሎ በግምገማ ማጠቃለያ መድረኩ ላይ በግምገማው የተለዩ የአመራሩ ችግሮችን አስመልክቶ የቀጣይ የትኩረት አቅጣጫ ላይ ማብራሪያ የሰጡ ሲሆን፤የወረዳው ህዝብ ሁለንተናዊ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ አመራሩ ቅንጅታዊ አሠራሮችን አጠናክሮ በማስቀጠልና በምዘናና ግምገማ መድረኩ በጉድለት የታዩ ጉዳዮችን በማረም በፓርቲ እሴት፣ መርህና ዲሲፕሊን ላይ ተመስርቶ ለላቀ ዉጤት በቁርጠኝነት መስራት እንደሚገባ እና ለዉጤታማነቱም የጋራ ርብርብ ማድረግ ይጠበቅብናል በማለት መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

የወረዳ ዋና የመንግስት ተጠሪ እና የብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ግርማ ግለዴ በበኩላቸው ምዘናው አመራሩ የተጣለበትን የህዝብ አደራ ከመወጣትና ከአገልግሎት አሰጣጥ ጋር ተያይዞ የነበሩ ውስንነቶች በማረም ለተሻለ ስራ የሚያዘጋጅ እንደሆነ አብራርተዋል።

አክለውም የመንግስትና የፓርቲ አደረጃጀቶች በማጠናከር እስከታችኛው መዋቅር በመውረድ ከአስተሳሰብ ጀምሮ ስራ መስራት እንደሚገባ ገለፀው፤በተለይም የፓርቲና የመንግስት አደረጃጀቶችን በማጠናከር አደረጃጀትን ተልዕኮ መፈፅም እንዲቻል ሰፊ ስራ መሰራት እንደሚገባ ገልፀዋል።

በተደረገው ጥልቅ የአመራር ግምገማ የወረዳው
አመራር ጉድለቱን በሚገባ ያየበት እና ችግሮችን በመለየት ለቀጣይ ተግባር የሚያነሳሳ የግምገማ መድረክ ሆኖ ተጠናቋል።

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡
የpage
https://www.facebook.com/profile.php?id=100069342064100
whatapp:https://whatsapp.com/channel/0029VbBzfVYCRs1tubeysJ1J
Youtube፡ https://www.youtube.com/
Like and Share በማድረግ ቤተሰብ በመሆን መረጃ ይከታተላሉ!

መረጃው፦
የካራት ዙሪያ ወረዳ መንግስት ኮሚዪኒኬሽን አገልግሎት!!
ነሐሴ 09/2018 ዓ.ም

14/08/2026
በካራት ዙሪያ ወረዳ የ2018 በጀት ዓመት የመንግሥትና የፓርቲ የሥራ አፈጻጸም የአመራሮች ግምገማና ምዘና መድረክ እያካሄደ ነው፦"ትጋት ለላቀ ስኬት""በሚል መሪ ቃል በኮንሶ ዞን ካራት ዙሪያ...
13/08/2026

በካራት ዙሪያ ወረዳ የ2018 በጀት ዓመት የመንግሥትና የፓርቲ የሥራ አፈጻጸም የአመራሮች ግምገማና ምዘና መድረክ እያካሄደ ነው፦

"ትጋት ለላቀ ስኬት""በሚል መሪ ቃል በኮንሶ ዞን ካራት ዙሪያ ወረዳ የ2018 በጀት ዓመት የፓርቲና የመንግስት ሥራዎች አፈፃፀም ማጠቃለያ ግምገማ እና በቀጣይ አቅጣጫዎች ላይ የምመክር ወረዳዊ የመካከለኛና ዝቅተኛ አመራር መድረክ እያካሄደ ይገኛል።

​በመድረኩ ላይ ተገኝተው መልእክት ያስተላለፉት የኮንሶ ዞን ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ መምሪያ ኃላፊ ክብርት ወ/ሮ አስቴር ኩሲያ እንደገለጹት፤ከምዘናው የሚገኙ ግብዓቶችን በአግባቡ በመውሰድና የታዩ ክፍተቶችን በቁርጠኝነት በመሙላት የሕዝቡን የልማትና የኢኮኖሚ ተጠቃሚነት ለማፋጠን በትኩረት መረባረብ እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል።

አያይዘውም ለቀጣዩ በጀት ዓመትም የተመዘገቡ በጠንካራ ተሞክሮዎችን በላቀ ደረጃ በማስቀጠል፣ የታዩትን ክፍተቶች በተቀናጀ አሠራር በመሙላት የሕዝቡን የልማትና የብልጽግና ተጠቃሚነት በተግባር ማረጋገጥ እንደሚገባ ወ/ሮ አስቴር አጽንኦት ሰጥተዋል።

የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ ክቡር አቶ ኩሴ ጭሎ በበኩላቸው ከምርጫው አፈጻጸም አንጻር ምርጫውን ፍትሐዊ ዲሞክራሲያዊና ታማኝ ማድረግ እንዲሁም በሙሉ ድምፅ ማሸነፍ የሚሉ ሁለት ዋና ዋና ግቦችን አስቀምጦ መሥራቱንና ሁለቱንም ማሳካት መቻሉን ገልጸዋል።

አያይዘውም ይህ ስኬት የተመዘገበው በተመቻቹ ሁኔታዎች ሳይሆን፣ የውስጥና የውጭ የጥፋት ኃይሎች ጥምረት ፈጥረው በተንቀሳቀሱበት ፈታኝ ሁኔታ ውስጥ በብርቱ ጥረትና ፈተናዎችን ወደ ድል በመቀየር መሆኑንም አስገንዝበዋል።

​ መድረኩ በ2018 በጀት ዓመት የተከናወኑ የፓርቲና የመንግሥት ሥራዎችን አፈጻጸም በጥልቅ በመገምገም አመራሩ ጥንካሬዎቹን አጠናክሮ እንዲቀጥልና የታዩ ክፍተቶችን በዝርዝር በመፈተሽ ቀጣይ ለላቀ ስኬት እንዲዘጋጅ ለማድረግ ያለመ መሆኑን ዋና አስተዳዳሪው ገልጸዋል።

የአመራር ምዘናና ግምገማ ሂደቱ እስከ ቀበሌ መዋቅር ድረስ በመውረድ በየቀበሌው በሚገኙ አመራሮችና አባላት ላይ በተመሳሳይ መልኩ እንደሚቀጥል አቶ ኩሴ አሳስበዋል።

​በመድረኩ የወረዳው ዋና የመንግሥት ተጠሪና የብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ግርማ ግለዴ አማካኝነት የፓርቲና የመንግሥት የሥራዎች አፈጻጸም ሪፖርት እየቀረበ ሲሆን በቀጣይ ውይይት ይደረግበታል ተብሎ ይጠበቃል።

በመድረኩ የዞን ምድብተኛ አመራሮች፣አጠቃላይ የወረዳው የአመራር ፑል እንድሁም የቀበሌያት ዋና አስተዳዳሪዎችና የብልጽግና ፓርቲ ኃላፊዎች ተሳትፈዋል።

ነሐሴ 07/2018 ዓ.ም


የ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ድል የህዝብ እምነት ውጤት በመሆኑ ለህዝቡ የተገቡ ቃሎች በተግባር ሊፈጸሙ ይገባል - አቶ ኩሴ ጭሎየኮንሶ ዞን ካራት ዙሪያ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የ7ኛ...
02/08/2026

የ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ድል የህዝብ እምነት ውጤት በመሆኑ ለህዝቡ የተገቡ ቃሎች በተግባር ሊፈጸሙ ይገባል - አቶ ኩሴ ጭሎ

የኮንሶ ዞን ካራት ዙሪያ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የ7ኛውን ሀገራዊ ምርጫ የድል ብስራትን አስመልክቶ የምስጋና መርሃ ግብር አካሂዷል።

የምስጋናው መርሃግብር በሀይማኖት አባቶች ቡራኬ የተጀመረ ስሆን በመርሃ ግብሩ የኮንሶ ዞን ምክትል ዋና አስተዳዳሪና የግብርና ልማት መምሪያ ኃላፊ አቶ ጉራሾ ጎስኬ፣ የዞን፣ የወረዳና የቀበሌ ከፍተኛ የመንግሥትና የፓርቲ ኃላፊዎች፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ተወካዮች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ የፀጥታ አካላት፣ የሴቶችና ወጣቶች ተወካዮች እንዲሁም በርካታ የአካባቢው ነዋሪዎች ተገኝተዋል።

የካራት ዙሪያ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ኩሴ ጭሎ ባደረጉት ንግግር፣ በ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ህዝቡ በንቃት በመሳተፍ የዲሞክራሲ መብቱን መጠቀሙንና ለብልጽግና ፓርቲ የሰጠውን እምነት በማመስገን፣ የተገኘው ድል የሁሉም የጋራ ድል መሆኑን ገልጸዋል።

በቀጣይም የህዝቡን የልማት፣ የሰላምና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች በተግባር ለመመለስ አመራሩና አባላቱ በትጋት እንዲሰሩ ጥሪ አቅርበዋል።

አቶ ኩሴ አክለውም፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች በሰላማዊ ውድድር ያሳዩትን ብስለት በማድነቅ፣ ከምርጫ በኋላ ሁሉም የኮንሶን ልማትና ሰላም ለማረጋገጥ በጋራ እንዲሰሩ ጥሪ አቅርበዋል።

ለሃይማኖት አባቶች፣ ለሀገር ሽማግሌዎች፣ ለንግዱ ማህበረሰብ፣ ለወጣቶችና ለሴቶችም በሰላም፣ በልማትና በህብረተሰብ አንድነት ግንባታ የሚጠበቅባቸውን ሚና በስፋት አስቀምጠዋል።

የካራት ዙሪያ ወረዳ ዋና የመንግሥት ተጠሪና የብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ግርማ ግላዴ፣ የ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ሰላማዊ፣ ፍትሃዊ፣ ዴሞክራሲያዊና ተዓማኒ በሆነ ሁኔታ መጠናቀቁ የኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ጉዞ አስፈላጊ ምዕራፍ መሆኑን ገልጸዋል።

የምርጫው ስኬት በህዝቡ፣ በፓርቲ አመራሮችና አባላት፣ በፀጥታ አካላት፣ በምርጫ ቦርድ፣ በሀገር ሽማግሌዎች፣ በሃይማኖት አባቶችና በሁሉም ተቋማት የተደረገ የጋራ ጥረት ውጤት መሆኑንም አስታውቀዋል።

አቶ ግርማ በመጨረሻ የተገኘው ድል የሚለካው በህዝብ ህይወት ላይ በሚመጣ ተጨባጭ ለውጥ፣ በሰላም ማስፈን፣ በፍትህ ማረጋገጥና በልማት ስኬት መሆኑን በመግለጽ፣ ሁሉም አካላት በአንድነት በመስራት የኮንሶን ዕድገትና ብልጽግና እንዲያረጋግጡ ጥሪ አቅርበዋል።

በማጠቃለያው የኮንሶ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊና ዋና የመንግሥት ተጠሪ አቶ ጉራሾ ለሚታ ባስተላለፉት መልዕክት፣ የተገኘው ድል የህዝቡ እምነትና የጋራ ትግል ውጤት መሆኑን ገልጸው፣ ይህን እምነት በተግባር በመመለስ ለህዝቡ የተገቡ ቃሎችን በመፈጸም፣ ሰላምን በማጠናከርና ልማትን በማፋጠን ሁሉም በአንድነት እንዲሰሩ አሳስበዋል።

01/08/2026
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የ 2018 አጠቃላይ የፓርቲ ስራዎች አፈፃፀምን እየገመገመ ነዉሰኔ 29/2018 ዓ.ምየደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ...
06/07/2026

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የ 2018 አጠቃላይ የፓርቲ ስራዎች አፈፃፀምን እየገመገመ ነዉ

ሰኔ 29/2018 ዓ.ም

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የ 2018 አጠቃላይ የፓርቲ ስራዎች አፈፃፀምን እየገመገመ ይገኛል።

በመድረኩ በበጀት ዓመቱ የተከናወኑ አጠቃላይ የፓርቲ ስራዎች አፈፃፀም እንዲሁም የ 2019 ዓ.ም ጠቋሚ ዕቅድ ቀርቦ ዉይይት እንደሚደረግ ይጠበቃል።

በመድረኩ በ 2018 በጀት ዓመት በቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ በዝግጅት፣ በትግበራና በማጠቃለያ ምዕራፎች የተከናወኑ አበይት ክንውኖች የሚገመገሙ ሲሆን በተጨማሪም ወቅታዊና የንቅናቄ አጀንዳዎች ላይ ዉይይት እንደሚካሄድ ታዉቋል።

በመድረኩ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ገብረመስቀል ጫላን ጨምሮ ሁሉም የቅ/ጽ/ቤቱ አመራሮች በመሳተፍ ላይ ናቸው።

በኮንሶ ዞን የካራት ዙሪያ ወረዳ  "ከምርጫ ድል ማግስት፣ ጠንካራ መንግሥት" በሚል መሪ ቃል የፐብሊክ ሰርቫንት  የሰባተኛውን ጠቅላላ የምርጫ ሥራዎች አፈጻጸም እና የድህረ ምርጫ ሥራዎች ዕቅ...
20/06/2026

በኮንሶ ዞን የካራት ዙሪያ ወረዳ "ከምርጫ ድል ማግስት፣ ጠንካራ መንግሥት" በሚል መሪ ቃል የፐብሊክ ሰርቫንት የሰባተኛውን ጠቅላላ የምርጫ ሥራዎች አፈጻጸም እና የድህረ ምርጫ ሥራዎች ዕቅድ ላይ ውይይት አካሂዷል።

በመድረኩ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የካራት ዙሪያ ወረዳ የመንግስት ረዳት ተጠሪና የፖለቲካ ርዕዮት ዓለም ኃላፊ ኩቹሎ ኩሲታ ምርጫውን የመራንበት ስኬታማ መንገድ፣ ከምርጫው ማግስት ዉጤታማ የድህረ ምርጫ ሥራ በመሥራትና እንድናገለግል ዕድሉን ለሰጡን ለህዝባችን በታማኝነት ማገለገል ይገባናል ብለዋል።

አቶ ኩቹሎ ኩሲታ አክሎም የመድረኩ ዋና ዓላማ ከምርጫው በኋላ የተገኙ ውጤቶችን መገምገም፣ የታዩ ጠንካራ ጎኖችን ማጠናከር እና ያጋጠሙን ችግሮችን በመለየት የፐብሊክ ሰርቫንቱ በአገልግሎት ግንባር ቀደም ሚና መጫወት እንዳለባቸው አሳስበዋል።

በመድረኩ የቅድመ ምርጫ ዝግጅት፣ የምርጫ ዕለት ተግባራት አፈጻጸምና የቀጣይ አቅጣጫዎች ላይ የተሰነዱ ሰነዶችን ያቀረቡት የወረዳው ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ካፍታ ካሳሞ ለተሳታፊ የፓርቲው አባላት አቅርበዋል።

ምርጫውን የመራንበት ስኬታማ መንገድ፣ ከምርጫው ማግስት የሕዝባችንን ሁለንተናዊ እርካታና ተጠቃሚነት በላቀ ደረጃ በሚያረጋግጥ መልኩ በቁርጠኝነት የምንቀጥልበት መሆኑን አውስተው ሁሉም የፓርቲው አባላት ከወዲሁ መዘጋጀት ይገባቸዋል ሲል ገልጸዋል።

እንዲሁም ተሳታፊዎች ደግሞ በቅድሜ ምርጫ ጊዜና በድህረ ምርጫ ጊዜ የነበረውን አጠቃላይ ሁኔታዎች ላይ ገንቢ የሆኑ አስተያየቶችንና ሀሳቦችን አንስተው በሰፊው ምክክር ተካሂዶበታል።

ሰኔ 13/2018ዓ.ም
zuriya woreda prosperity

"ከምርጫ ድል ማግስት ጠንካራ መንግስት" በሚል መሪ ቃል የኮንሶ ዞን ካራት ዙሪያ ወረዳ መካከለኛ አመራሮች የውይይት መድረክ እንደቀጠለ ነው። #ካራት ዙሪያ ወረዳ: ሰኔ 12/2018 ዓ.ም ሁ...
19/06/2026

"ከምርጫ ድል ማግስት ጠንካራ መንግስት" በሚል መሪ ቃል የኮንሶ ዞን ካራት ዙሪያ ወረዳ መካከለኛ አመራሮች የውይይት መድረክ እንደቀጠለ ነው።

#ካራት ዙሪያ ወረዳ: ሰኔ 12/2018 ዓ.ም


ሁለተኛ ቀኑን የያዘው መድረኩ ምርጫው ሠላማዊ እና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ በድል መጠናቀቁን ምክንያት በማድረግ በድህረ ምርጫ ግቦች አፈፃፀም ላይ ትኩረት ያደርጋል ተብሎ ይጠበቃል::

እንደዚሁም በሀገራዊ ምርጫ አፈፃፀም ወቅት በጥንካሬና በክፍተት የተለዩ ጉዳዮችን ትኩረት ሰጥቶ በመገምገም ቀጣይ አቅጣጫ እንደሚቀመጥ ይጠበቃል::

"ከምርጫ ድል ማግስት ጠንካራ መንግስት" በሚል መሪ ቃል የኮንሶ ዞን ካራት ዙሪያ ወረዳ መካከለኛ አመራሮች የውይይት መድረክ እየተካሄደ ይገኛል። #ካራት ዙሪያ ወረዳ: ሰኔ 11/2018 ዓ.ም...
18/06/2026

"ከምርጫ ድል ማግስት ጠንካራ መንግስት" በሚል መሪ ቃል የኮንሶ ዞን ካራት ዙሪያ ወረዳ መካከለኛ አመራሮች የውይይት መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።

#ካራት ዙሪያ ወረዳ: ሰኔ 11/2018 ዓ.ም
(ካዙወመኮአገ/ት)

ከሰኔ 11-12/2018 ዓ/ም ለሁለት ተከታታይ ቀናት የምቆየው "ከምርጫ ድል ማግስት ጠንካራ መንግስት" በሚል መሪ ቃል የኮንሶ ዞን ካራት ዙሪያ ወረዳ መካከለኛ አመራሮች የውይይት መድረክ መካሄድ ጀምሯል።

በመድረኩ የዞን ምድብተኛ አመራሮች፣የወረዳ አስተባባሪዎች፣የወረዳው አጠቃላይ የአመራር ፑል ተገኝተዋል።

መሉ መረጃውን ከመድረኩ መጨረሻ የምናደርሳችሁ ይሆናል።

Address

Konso Karat
Konso
4400

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Konso Zone Karat Zuria Woreda Prosperity Party posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share