11/08/2026
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ሰንደቅ ዓላማ እና አርማ ከክልሉ ሕገ-መንግስት አንጻር:-
ነሐሴ 05/2018 ዓ/ም
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ሕገ-መንግስት አንቀጽ 3 ንዑስ አንቀጽ 1 መሰረት የክልሉ ሰንደቅ አላማ ላይ ሊኖሩ የሚገባቸውን ቀለማትና የክልሉ አርማ እንደሚኖርበት ይገልጻል፡፡
ይሁን እንጂ በተለያዩ የሕትመት ውጤቶችና የማህበራዊ ሚዲያ ገፆች ላይ አንዳንድ ግለሰቦችና ድርጅቶች በማወቅም ሆነ ባለማወቅ ትክክለኛ ያልሆነውን የክልሉን ሰንደቅ አላማና አርማ ጥቅም ላይ እያዋሉ ይገኛሉ ፡፡
በዚህም የክልሉ ሰንደቅ ዓላማ ከላይ አረንጓዴ ፤ ከመሃል ውሃ ሰማያዊ ፤ ከታች ቀይ ሆኖ በአግድሚ የተቀመጡ ሲሆን ከአረንጓዴው እና ከቀዩ ቀለም መስቀያ ጠርዝ በመነሳት ሰማያዊው መደብ ላይ የሚያርፍ ሦስት ማዕዘን ቅርጽ ያለው ቢጫ ቀለም ሆኖ በመሃሉ በሚገኘዉ ውሃ ሰማያዊ መደብ ላይ የክልሉ ዓርማ የሚቀመጥ ስሆን እያንዳንዱ ቀለማት በጥቁር መስመሮች ተለያይዘዋል፡፡
በሰንደቅ ዓላማዉ ውሃ ሰማያዊ መደብ መሃል ላይ የሚቀመጠው የክልሉ ዓርማ ላይ የሚገኙት የተሰባጠሩ እያንዳንዱ ምስሎች የሚያስተላልፉት መልዕክት ያላቸው ስሆን መሀል ላይ የሚገኘው የነጭ እርግብ ምስል ክልሉ የሰላም ተምሳሌት መሆኑን ፣ ከምስሉ ጫፍ ላይ በጥቁር መደብ የተቀመጠዉ ምስል አብዛኞቹ በክልሉ ዉስጥ የሚገኙ አከባቢዎች ለማኑፋክቸሪንግ ምቹ መሆናቸዉን በአፅንኦት ይገልጻል።
እንድሁም ደግሞ በእግርጌው ያለዉ ያጎመራ የቡና ምስል ክልሉ የሀገር ኢኮኖሚ የጀርባ አጥንት የሆነዉ የቡና ምርት በስፋት ብሎም በጥራት የሚመረትበት ስለመሆኑ መገለጫ ነዉ ፣ በስተቀኝ ያለዉ ከአንገት በላይ ያለ የበሬ አካል ምስል በቆላማው አከባቢ ያለዉ የማህበረሰብ ክፍል አርብቶ አደር መሆኑን ስገልጽ በስተ ግራ ያለዉ እንሰት በከፍተኛ ሁኔታ ድርቅን በመቋቋም በክልሉ የተለያዩ አከባቢዎች በስፋት የሚመረት ለተለያዩ የምግብ ፍጆታዎች የሚዉል ምርት መገኛ የመሆኗ መገለጫ ነዉ።
ስለሆነም ማንኛውም ተቋም ሆነ ግለሰብ ትክክለኛ የሆነዉን የክልሉን ሰንደቅ ዓላማ እና አርማ በመለየት መጠቀም እንደሚገባው ሲሆን ትክክለኛ ያልሆነውን አርማም ሆነ ሰንደቅ ዓላማ መጠቀም በሕግ የሚያስጠይቅ መሆኑን እንገልፃለን።
መረጃዉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት ብሔረሰቦች ምክር ቤት