የኮንሶ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ወጣቶች ክንፍ ጽ/ቤት Konso Zone Prosperity Party Youth Wing

  • Home
  • Ethiopia
  • Konso
  • የኮንሶ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ወጣቶች ክንፍ ጽ/ቤት Konso Zone Prosperity Party Youth Wing

የኮንሶ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ወጣቶች ክንፍ ጽ/ቤት Konso Zone Prosperity Party Youth Wing This is the official page of Konso Zone Prosperity Party Youth Wing Office.

"ወሰን ተሻጋሪ የበጎ ፈቃድ መርሃ ግብር የአብሮነትና የትብብር እሴቶችን አጠናክሯል" የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ወጣቶችና በጎ ፈቃድ ኮሚሽን ነሐሴ 27/2018 ዓ.ም በክልሉ ከሚገኙ ሁሉም አከባ...
02/09/2026

"ወሰን ተሻጋሪ የበጎ ፈቃድ መርሃ ግብር የአብሮነትና የትብብር እሴቶችን አጠናክሯል" የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ወጣቶችና በጎ ፈቃድ ኮሚሽን

ነሐሴ 27/2018 ዓ.ም

በክልሉ ከሚገኙ ሁሉም አከባቢዎች የተውጣጡ በጎ ወጣቶች በሲዳማ፣ ኦሮሚያና ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልሎች ተዘዋዉረው የተለያዩ የበጎ ፈቃድ ተግባራትን አከናውነዋል።

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ወጣቶችና በጎ ፈቃድ ኮሚሽን ኮሚሽነር በጎ ፈቃደኛ ወጣቶች በ3ቱ ክልሎች ተንቀሳቅሰው ያከናወኑት ተግባራት ስኬታማ መሆናቸውን ጠቁመዋል።

ወጣቶቹ በተንቀሳቀሱባቸው ክልሎች የደም ልገሳ፣ ችግኝ ተከላ፣ አረጋውያንን የመመገብ፣ የከተማ ጽዳት እንዲሁም የተማሪዎችን የመማሪያ ቁሳቁስ ድጋፍ ማድረጋቸውንም ኮሚሽነሩ አብራርተዋል።

የበጎ ፈቃድ መርሃ ግብሩ ከበጎ ተግባር ባሻገር ወጣቶችን በአንድ ዓላማ በማሰባሰብ የመተሳሰብ፣ የመረዳዳትና የትብብር እሴቶችን አጠናክሯል ሲሉም አቶ ማርቆስ ጠቅሰዋል።

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ብልጽግና ፓርቲ ወጣቶች ክንፍ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ሚካኤል ዋዳ በበኩላቸው መርሃ ግብሩ በሕዝቦች መካከል ያለውን የተሳሰረ ማንነትና አብሮነት የሚያጠናክር መሆኑን ገልጸዋል።

ወጣቶች ደም በመለገስ ለሕይወት መዳን የሚያበረክቱት አስተዋጽኦ የሕዝቦችን በደም የተሳሰረ አብሮነት እንደሚያሳይ አቶ ሚካኤል ገልፀዋል።

በቀጣይም ከማዕከላዊ ኢትዮጵያ፣ ከሲዳማ እና ከአዲስ አበባ የሚመጡ ወሰን ተሻጋሪ ወጣቶች በተመሳሳይ በክልሉ የበጎ ተግባር መርሃ ግብር ላይ እንደሚሳተፉም አመላክተዋል።

በመርሃ ግብሩ የተሳተፉ ወጣቶችም በቆይታቸው በርካታ ልምድ መቅሰማቸውን ተናግረዋል።

በየኔዓሐም ሳሙኤል

02/09/2026
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ወጣቶች ወሰን ተሻጋሪ የክረምት  የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ልኡካን ቡድን በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የልማት ፕሮጀክቶችን ተመለከቱ ወጣቶቹ በክልሉ በነበራቸው ቆይታ ግንባ...
02/09/2026

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ወጣቶች ወሰን ተሻጋሪ የክረምት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ልኡካን ቡድን በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የልማት ፕሮጀክቶችን ተመለከቱ

ወጣቶቹ በክልሉ በነበራቸው ቆይታ ግንባታቸው በስድስት ወራት ብቻ የተጠናቀቁ የልማት ፕሮጀክቶችን ተመልክተዋል።

የርዕሰ መስተዳድር ጽ/ቤት፣የመሰብሰቢያ አዳራሽ እና ቤተ መንግስት ወጣቶቹ ከተመለከቷቸው የልማት ፕሮጀክቶች ውስጥ ተጠቃሽ ናቸው።

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ወጣቶች ወሰን ተሻጋሪ የክረምት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ልኡካን ቡድን በክልሉ ልዩ ልዩ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት እያከናወነ ይገኛል።

በተስፋዬ መኮንን

  የደቡብ ኢትዮጵያ ወሰን ተሻጋሪ ወጣቶች ለበጎ ፈቃድ አገልግሎት ኦሮሚያ ክልል ሻሸመኔ ከተማ ሲደርሱ አቀባበል ተደርጎላቸዋል። የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ወጣቶችና በጎ ፈቃድ ኮሚሽን ኮሚሽነር ...
01/09/2026

የደቡብ ኢትዮጵያ ወሰን ተሻጋሪ ወጣቶች ለበጎ ፈቃድ አገልግሎት ኦሮሚያ ክልል ሻሸመኔ ከተማ ሲደርሱ አቀባበል ተደርጎላቸዋል።

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ወጣቶችና በጎ ፈቃድ ኮሚሽን ኮሚሽነር ማርቆስ ማቴዎስ ወጣቶቹ የመጡበት ዋና ዓላማ በጎ ተግባራትን በመፈጸም ለማኅበረሰቡ የሚጠቅም አስተዋጽኦ ለማበርከት እንደሆነ አቀባበል በተደረገላቸው ጊዜ ገልፀዋል።

ወሰን ተሻጋሪ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት የሕዝብ ለሕዝብ ትስስርን ለማጠናከር እና የወጣቶችን የጋራ ተሳትፎ ለማሳደግ የጎላ አበርክቶ እንዳለው ተናግረዋል።

የሻሸመኔ ከተማ ብልጽግና ጽ/ቤት አደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ አቶ አብደላ አማን በበኩላቸው ወጣቶቹ በከተማዋ እያከናወኑ ያለው የበጎ ፈቃድ ሥራ ከበጎነት በላይ ትልቅ ሀገራዊ ትርጉም ያለው መሆኑን ገልጸዋል።

የበጎ ፈቃድ ተግባሩ የነገዋን ኢትዮጵያ በጋራ ለመገንባት የሚያግዝ መሆኑንም አቶ አብደላ አስረድተዋል።

በተለይም ለዓመታት የተለመደውን የጥገኝነት አስተሳሰብ በመቀየር፣ የሌሎችን እጅ ከማየት ይልቅ እርስ በርሳችን እንድንረዳዳ በየክረምቱ በተለያዩ የበጎ ፈቃድ ሥራዎች መጀመራቸው የሚደነቅ መሆኑን ጠቁመዋል።

የሻሸመኔ ከተማ የወጣቶች ክንፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሰይድ በሽር በበኩላቸው የደቡብ ኢትዮጵያ ወሰን ተሻጋሪ ወጣቶች በከተማዋ መገኘታቸው ልምድና እሴቶችን ለመለዋወጥ እንዲሁም የሕዝብ ለሕዝብ ወዳጅነትን ለማጎልበት የሚያግዝ መሆኑን ገልጸዋል።

ወጣቶቹ በቆይታቸው አረጋውያንን መመገብ፣ ደም መለገስ፣ ለተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ ማድረግን ጨምሮ ሌሎች ማኅበራዊ በጎ ተግባራትን አከናውነዋል።

  የደቡብ ኢትዮጵያ ወሰን ተሻጋሪ ወጣቶች በሲዳማ ክልል የተለያዩ በጎ ተግባራትን አከናወኑ ነሐሴ 26/2018 ዓ.ም “በጎነት ለኢትዮጵያ ከፍታ፣ የተጋመደ ማንነት፣ የማይለያይ ሕዝብ” በሚል ...
01/09/2026

የደቡብ ኢትዮጵያ ወሰን ተሻጋሪ ወጣቶች በሲዳማ ክልል የተለያዩ በጎ ተግባራትን አከናወኑ

ነሐሴ 26/2018 ዓ.ም

“በጎነት ለኢትዮጵያ ከፍታ፣ የተጋመደ ማንነት፣ የማይለያይ ሕዝብ” በሚል መሪ ቃል በሚካሄደው የበጎ ፈቃድ ተግባር በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ወጣቶችና በጎ ፈቃድ ኮሚሽነር አቶ ማርቆስ ማቴዎስን ጨምሮ ከ60 በላይ ወሰን ተሻጋሪ ወጣቶች የደም ልገሳን፣ አረጋውያንን መመገብንና ሌሎች በጎ ተግባራትን አከናውነዋል።

የበጎ ተግባሩ ዓላማ የወጣቶችን የበጎ ፈቃደኝነት መንፈስን በማዳበር በክልሎች መካከል ያለውን ትስስርና ወንድማማችነት ለማጠናከር መሆኑም ተጠቁሟል።
በሲዳማ ክልል በተከናወነውየበጎ ፈቃድ አገልግሎት ደም የመለገስ፣ለተማሪዎች የመማሪያ ቁሳቁስ ድጋፍ ማድረግ ፣የጽዳት ፕሮግራም ፣አረጋውያንን መመገብና ሌሎች መርሃ ግብሮች ተከናዉነዋል።

በተያያዘም ወጣቶቹ በሐዋሳ ከተማ አዳሪ ሆስፒታል የሚገኙ ህሙማንን ጎብኝተዋል።

በየኔዓለም ሳሙኤል

  የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ወሰን ተሻጋሪ ወጣቶች የበጎ ፈቃድ ሥራዎችን ለማከናወን ሲዳማ ክልል ደርሰዋል ነሐሴ 25/2018 ዓ.ም ከደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የተውጣጡ ወሰን ተሻጋሪ ወጣቶች “በጎ...
01/09/2026

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ወሰን ተሻጋሪ ወጣቶች የበጎ ፈቃድ ሥራዎችን ለማከናወን ሲዳማ ክልል ደርሰዋል

ነሐሴ 25/2018 ዓ.ም

ከደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የተውጣጡ ወሰን ተሻጋሪ ወጣቶች “በጎነት ለኢትዮጵያ ከፍታ” በሚል መሪ ሐሳብ የበጎ ፈቃድ ሥራዎችን ለማከናወን ሲዳማ ክልል ገብተዋል።

ወጣቶቹ የክልሉ ርዕሰ መዲና በሆነችው ሐዋሳ ከተማ ሲደርሱ የሲዳማ ክልልና የሐዋሳ ከተማ አስተዳደር አመራሮች፣ አቀባበል አድርጎላቸዋል።

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ወጣቶችና በጎ ፍቃድ ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ ማርቆስ ማቴዎስ የክልሉ ወጣቶች አንድነትንና ፍቅርን ይዘው ሌሎችን ለማገዝ መምጣታቸውን ተናግረዋል።

ወጣቶቹ በሐዋሳ ቆይታቸው የደም ልገሳ፣ የከተማ ጽዳትና የአረጋውያን ምገባን ጨምሮ በጎ ተግባራትን በማከናወን በሁለቱ ክልሎች መካከል ወዳጅነትን ከማጠናከር ባሻገር የልምድ ልውውጥን እንደሚያደርጉም አብራርተዋል ።

የወሰን ተሻጋሪ የበጎ ፈቃድ መርሃ ግብሩ ከበጎ ተግባር ባለፈ ወጣቶች በሁለቱ ክልሎች ያሉ የልማት ልምዶችን እንዲጎበኙ፣ ባህልና ልምድ እንዲለዋወጡ እና የጋራ ትብብርን እንዲያሳድጉ ዕድል የሚፈጥር መሆኑንም ገልፀዋል።

የሲዳማ ክልል ሴቶችና ወጣቶች ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ እመቤት ኢሳያስ በአቀባበል መርሃ ግብሩ ባስተላለፉት መልዕክት፣ በጎነት በገንዘብ የማይለካና ከቅን ልብ የሚመነጭ ተግባር መሆኑን ገልጸዋል።

ወጣቶቹ በአካባቢያቸው ብቻ በጎ ሥራ ማከናወን እየቻሉ ወሰን ተሻግረው ወደ ሲዳማ በመምጣታቸው የወንድማማችነትን፣ የፍቅርንና የአንድነትን መልዕክት በተግባር የሚያሳይ መሆኑንም አውስተዋል።

የሲዳማ ክልል ሴቶች፣ ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ምክትል ኃላፊ እና ወጣቶች ዘርፍ ኃላፊ አቶ ደስታ ለገሰ ባስተላለፉት መልዕክት ቀደም ሲል በሀገር ደረጃ የሚከናወነውን ወሰን ተሻጋሪ ትብብር አሁን ላይ ወደ ክልሎች ወርዶ እየሰፋ ይገኛል ብለዋል።

የደቡብ ኢትዮጵያ ወጣቶቹ ለበጎ ሥራ ወሰን ተሻግረው ወደ ሲዳማ መምጣታቸው ክልሎች በሁለቱ ክልሎች መሀከል የአንድነትና የወንድማማችነት እሴቶችን እንዲያጠናክሩ የሚያደርግ ተግባር መሆኑን አመልክተዋል።

የሐዋሳ ከተማ ሴቶች ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ መምሪያ ኃላፊ ወ/ሮ ፍሬሕይወት ወልደጻዲቅ በበኩላቸው የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ወጣቶች ከአካባቢያቸው ወጥተው በክልላችን የበጎ ተግባር ማከናወናቸው የመረዳዳትን፣ የመተሳሰብን፣ የአብሮነትና የኢትዮጵያዊነትን እሴቶች በተግባር ለማጠናከር ከፍተኛ አስተዋፅኦ አለው ብለዋል።

በጎ ፈቃደኛ ወጣቶች በክልሉ ከሚገኙ 12 ዞኖችና 3 ሪጂዮፖሊሲ ከተሞች የተውጣጡ ሲሆን፣ ከወጣቶችና በጎ ፍቃድ ኮሚሽን ከተለያዩ የወጣቶች አደረጃጀቶች የተውጣጡ ወጣቶች መሆናቸውም ተመላክቷል።

በየኔዓለም ሳሙኤል

  ከደቡብ ኢትዮጵያ ወደ ማዕከላዊ፣ ሲዳማና ኦሮሚያ ክልሎች ለሚያቀኑ ወሰን ተሻጋሪ ወጣቶች የሽኝት መርሃ-ግብር ተካሄደነሐሴ 25/2018 ዓ.ምከደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ወደ ማዕከላዊ ኢትዮጵያ፣...
31/08/2026

ከደቡብ ኢትዮጵያ ወደ ማዕከላዊ፣ ሲዳማና ኦሮሚያ ክልሎች ለሚያቀኑ ወሰን ተሻጋሪ ወጣቶች የሽኝት መርሃ-ግብር ተካሄደ

ነሐሴ 25/2018 ዓ.ም

ከደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ወደ ማዕከላዊ ኢትዮጵያ፣ ሲዳማና ኦሮሚያ ክልሎች በመጓዝ የወሰን ተሻጋሪ የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ለሚያከናውኑ ወጣቶች የአሸኛኘት መርሐ ግብር ተካሂዷል።

በመርሐ ግብሩ ላይ የደቡብ ኢትዮጵያ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ገብረመስቀል ጫላ ባስተላለፉት መልዕክት፣ ወጣቶች የሚያከናውኑት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ከክልል ወሰን ባሻገር ያለውን የወጣቶች ትስስር ለማጠናከርና የጋራ እሴቶችን ለማጎልበት ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል።

ወጣቶች በሚያከናውኑት የበጎ ፈቃድ ተሳትፎ በሌሎች ክልሎች ከሚገኙ ወጣቶችና ማህበረሰቦች ጋር በመስራት የመተባበር፣ የመረዳዳትና የአብሮነት ባህልን እንዲያጎለብቱ አቶ ገብረመስቀል አሳስበዋል።

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በጎ ፈቃድ አገልግሎት ኮሚሽን ኮሚሽነር ማርቆስ ማትዮስ በበኩላቸው፣ ወሰን ተሻጋሪ የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ወጣቶች ያላቸውን የበጎ ፈቃድ ተግባራት በተጨባጭ ለማሳየት እና በክልሎች መካከል ያለውን የወጣቶች ትስስር ለማጠናከር የሚያግዝ መሆኑን ጠቁመዋል።

ኮሚሽነሩ ወጣቶቹ በሚሄዱባቸው አካባቢዎች ኃላፊነታቸውን በአግባቡ በመወጣት፣ የበጎ ፈቃድ እሴትን በማስፋትና የአብሮነት መልዕክትን በማስተላለፍ አርአያ እንዲሆኑ ጥሪ አቅርበዋል።

የወሰን ተሻጋሪ የክረምት በጎ ፈቃድ መርሃ- ግብር ወጣቶች በተለያዩ ክልሎች በመሳተፍ ለማህበረሰቡ የሚጠቅሙ በጎ ሥራዎችን እንዲያከናውኑ ከማስቻሉም በላይ የወጣቶችን የጋራ ተሳትፎና ማህበራዊ ትስስር ለማጠናከር የሚያግዝ መሆኑ ተገልጿል።

በአሸኛኘት መርሃ- ግብሩ ላይ የክልሉ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ገብረመስቀል ጫላ፣ የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ንጋቱ ዳንሳ፣ የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ፍሬዘር ኮርባይዶ እንዲሁም የክልሉ የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።

  ‎እየተካሄደ በሚገኘው የኮንሶ ምሁራን ማህበር 4ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ የክረምት በጎ ተግባር እየተከናወነ ነው፣‎‎ካራት:ነሐሴ:22/2018 ዓ.ም (ኮንሶ ዞን ኮሙኒኬሽን)‎‎በመካሄድ ላይ...
28/08/2026

‎እየተካሄደ በሚገኘው የኮንሶ ምሁራን ማህበር 4ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ የክረምት በጎ ተግባር እየተከናወነ ነው፣

‎ካራት:ነሐሴ:22/2018 ዓ.ም (ኮንሶ ዞን ኮሙኒኬሽን)

‎በመካሄድ ላይ በሚገኘው የምሁራን ማህበር 4ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ የክረምት በጎ አካል የሆኑ የደም ልገሣ መርሃግብር እየተካሄደ ነው።

‎የኮንሶ ዞን ከፍተኛ አመራሮች በወቅቱ እንደገለጹት ደም መለገስ ሊተካ በሚችል ደም ሊተካ የማይችል ህይወትን የማዳን ኃላፊነታችንን እየተወጣን ነው ሲሉ ገልጸው ሁሉም በዚህ በጎ ተግባር የበኩሉን እንዲወጣ ጥሪ አቅርበዋል።

‎በጎ ማድረግ የጽድቅ ስራና የመልካምነት መገለጫ መሆኑን ያስገነዘቡት የዞኑ ከፍተኛ አመራሮቹ፤ለበጎነት እጃችንን በመዘርጋት ድጋፍ ለሚሹ አካላት የድርሻችንን ሊንወጣ ይገባልም ብለው የደም ልገሳ መርሃግብር እንደሚቀጥልም ተመላክቷል።

"በ 2019 የበጀት ዓመት የፓርቲውን አቅም በተሟላ መንገድ በመጠቀም የተቀመጡ ግቦችን ለማሳካት በትኩረት ይሰራል"- አቶ ገብረመስቀል ጫላነሐሴ 19/2018 ዓ.ምጠንካራ ፓርቲ ለጠንካራ መንግ...
25/08/2026

"በ 2019 የበጀት ዓመት የፓርቲውን አቅም በተሟላ መንገድ በመጠቀም የተቀመጡ ግቦችን ለማሳካት በትኩረት ይሰራል"- አቶ ገብረመስቀል ጫላ

ነሐሴ 19/2018 ዓ.ም

ጠንካራ ፓርቲ ለጠንካራ መንግስትና ለጠንካራ ሀገረ-መንግስት ግንባታ ወሳኝ መሆኑን በማረጋገጥ የፓርቲውን ተቋማዊ አቅም ለማጠናከር በትኩረት ይሰራል ተብሏል።

በብልጽግና ፓርቲ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ቅ/ጽ/ቤት የ 2018 የፓርቲ ስራዎች የማጠቃለያ ግምገማና የ 2019 ዕቅድ ኦሬንቴሽን መድረክ በሳዉላ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል።

በበጀት ዓመቱ በክልሉ በተከናወኑ የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚና የማህበራዊ ተግባራት ተጨባጭ ዉጤት የተገኘበት ስኬታማ አመት እንደነበር ተጠቅሷል።

የክልሉ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ገብረመስቀል ጫላ የአስተሳሰብና የተግባር አንድነት ፈጥሮ ሀገርን ለማሻገር ጠንካራ ፓርቲ ወሳኝ መሆኑን ገልፀዋል።

በ 2018 ዓ.ም የምርጫና መደበኛ የልማት ስራዎች ጎን ለጎን መመረታቸውን ያስታወሱት ኃላፊዉ በተቀናጀ መንገድ በተሰራው ስራ ፍሬያማ ዉጤት መገኘቱን አስረድተዋል።

ከአጠቃላይ የፓርቲ ስራዎች አንፃር ጠንካራ ፓርቲ ለጠንካራ መንግስትና ለጠንካራ ሀገረ-መንግስት ግንባታ ወሳኝ መሆኑን ማረጋገጥ ቅድሚያ የሚሰጠው ተግባር ነዉ ብለዋል።

የፓርቲውን አቅም አሟጦ አለመጠቀም፣ የአመራር የስነ-ምግባር ልህቀት ማረጋገጥ አለመቻል፣ እንዲሁም ነጠላ ትርክቶችን በሚፈለገው ደረጃ መድፈቅ አለመቻል የተስተዋሉ ተግዳሮቶች መሆናቸውን አቶ ገ/መስቀል አብራርተዋል።

በአዲሱ የበጀት ዓመት የአመራርና አባላት ጥራትን ማረጋገጥ፣ የብሔራዊነት ገዢ ትርክትን ማስረፅ እና የፓርቲውን ተቋማዊ ስራዎች በግልፅ በሚቀመጡ ደረጃዎች ማረጋገጥ ትኩረት የሚደረግባቸው መሆናቸዉን አስረድተዋል።

በተለይም ክልላዊ አንድነትን የሚያጠናክሩ አስተሳሳሪ ትርክቶች መገንባት ላይ በከፍተኛ ትኩረት በመስራት የሕዝብ ለሕዝብ ትስስርን ማጠናከር እንደሚገባ አፅንኦት ሰጥተዋል።

በተደራጀ መንገድ ስልጠናዎችን በመስጠት የአቅም ግንባታ ስራ መስራት፣ የንቅናቄ ስራዎችን በሚለካ መንገድ መፈፀም፣ የብልጽግና አደረጃጀቶች የመደመር መንግስት የማዕዘን ዲንጋይ መሆናቸዉን ተረድቶ ጠንካራ አደረጃጀቶችን ማጠናከር አስፈላጊ መሆኑን አስምረዋል።

በምርጫ ወቅት ከፖለቲካ ፓርቲዎችና ሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ጋር የተጀመረውን ትብብር ማጠናከር፣ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ማስፋትና ባህል ማድረግ፣ ከሀገር ግንባታ ስራዎች ጋር ማስተሳሰር ይገባል ብለዋል።

ከሕዝብ ግንኙነትና ሚዲያ አንፃር የብሔራዊነት ትርክትን ማስረፅና ሚዲያዎችን መምራት ትኩረት ተሰጥቶታል።

Address

Konso
4400

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የኮንሶ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ወጣቶች ክንፍ ጽ/ቤት Konso Zone Prosperity Party Youth Wing posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share