Afar Prosperity party - ብልጽግና

Afar Prosperity party - ብልጽግና This is official page of Prosperity Party Afar Region branch office in semera.
(1)

ጳጉሜ 2 — የማንሰራራት ቀን አፋር ክልል በአዲስ የተስፋና የልማት መንፈስ የማንሰራራት ጉዞውን እውን እያደረገ ይገኛል። በሀገራችን በታላቅ ዝግጅት እየተከበረ ከሚገኘው የጳጉሜን ወር መሸጋገ...
07/09/2026

ጳጉሜ 2 — የማንሰራራት ቀን

አፋር ክልል በአዲስ የተስፋና የልማት መንፈስ የማንሰራራት ጉዞውን እውን እያደረገ ይገኛል።

በሀገራችን በታላቅ ዝግጅት እየተከበረ ከሚገኘው የጳጉሜን ወር መሸጋገሪያ ቀናት መካከል ሁለተኛው ቀን የሆነው "የማንሰራራት ቀን" በአፋር ክልል በልዩ ልዩ የልማትና የመልካም አስተዳደር ሁነቶች በደመቀ ሁኔታ እየተከበረ ይገኛል።

​በዕለቱ ምክንያት በማድረግ የክልሉ ፕሬዚዳንት ባስተላለፉት የደስታና የመልካም ምኞት መልእክት፤ ክልላችን ላለፉት ዓመታት ያጋጠሙትን የተፈጥሮና የሰው ሰራሽ ተደራራቢ ፈተናዎች በጽናት በመጋፈጥ፣ በፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ መስኮች ዘላቂ ማንሰራራትን ማረጋገጥ መቻሉን ገልጸዋል።
​በአፋር ክልል ደረጃ የተረጋገጡ ዋና ዋና የማንሰራራትና የልማት ስኬቶች

የከተሞች የኮሪደር ልማትና የገጽታ ግንባታ ማንሰራራት በክልሉ ዋና ዋና ከተሞችና የንግድ ኮሪደሮች (በተለይም በሰመራ-ሎጊያና አካባቢው) የተከናወኑ የኮሪደር ልማት ስራዎች የከተሞችን ጽዳት፣ ውበትና የመሰረተ ልማት ደረጃ በጥራት አድሰዋል። መንገዶችን ማስፋፋት፣ የጎዳና ላይ መብራቶችን መትከል፣ የእግረኛ መንገዶችን ማዘጋጀትና የአረንጓዴ ስፍራዎችን ማስፋፋት የከተሞቻችንን ገጽታ ከመቀየሩም በላይ ለንግድና ኢንቨስትመንት ምቹ ሁኔታን ፈጥሯል።

የግብርናና የምግብ ዋስትና ማንሰራራት በመስኖ ልማትና በበጋ ስንዴ ምርት ረገድ አርብቶ አደሩን ወደ Agro-Pastoralist መስኖ ልማት) የመቀየር እንቅስቃሴ ትልቅ ውጤት አሳይቷል። ሰፊ መሬቶችን ወደ ምርታማነት በመቀየር በክልሉ የምግብ ዋስትናን የማረጋገጥ ጉዞ አዲስ ምዕራፍ ተክቷል።

የመሠረተ ልማትና የአገልግሎት ድርጅቶች መልሶ መገንባት ጉዳት ደርሶባቸው የነበሩ የትምህርት፣ የጤና እና የንጹህ መጠጥ ውሃ ተቋማት በአጭር ጊዜ ውስጥ መልሰው በመገንባታቸው ማህበረሰቡ ሙሉ በሙሉ ወደ መደበኛ አገልግሎት እንዲመለስ ተደርጓል።

የሰላምና ደህንነት መረጋጋት የክልላችን ህዝብ ከአጎራባች ክልሎች ጋር ያለውን የቆየ ወንድማማችነትና አብሮ የመኖር ባህል በማጠናከር፣ አስተማማኝ ሰላም በመገንባቱ ለልማትና ለንግድ እንቅስቃሴዎች ምቹ ሁኔታ ተፈጥሯል።

የወጣቶችና ሴቶች ኢኮኖሚያዊ ተሳትፎ በስራ ዕድል ፈጠራና በአነስተኛና ጥቃቅን ኢንተርፕራይዞች በኩል በርካታ ወጣቶችና ሴቶች ወደ ምርታማነት በመሸጋገር የራሳቸውንና የክልሉን ኢኮኖሚ በማንሰራራት ላይ ንቁ ተሳትፎ እያደረጉ ይገኛሉ።
​የአፋር ክልል ፕሬዚዳንት ሀጂ አወል አርባ በመልእክታቸው ጨምረው እንደገለጹት፤ "ማንሰራራት ማለት ያለፈውን ፈተና ወደ ድል በመቀየር፣ ከተሞቻችንን በማስበብና ልማትን በማፋጠን ለነገው ትውልድ የተሻለችና የበለፀገች አፋርን መፈጠር ነው" ያሉ ሲሆን፣ መላው የክልሉ ህዝብና ባለድርሻ አካላት በየዘርፉ የተጀመረውን የማንሰራራት ጉዞ አጠናክረው እንዲቀጥሉ ጥሪ አቅርበዋል።



ጳጉሜ 2 የማንሰራራት ቀን የ2018 ጳጉሜ ቀን '' ዘላቂ ልማት ለሀገራዊ መንሰራራት''  በሚል መሪ ቃል በተለያዩ የልማት ስራዎች ላይ ጉብኝት በማድረግ ተከብሯል። በጉብኝቱ የክልሉ ምክትል ...
07/09/2026

ጳጉሜ 2 የማንሰራራት ቀን

የ2018 ጳጉሜ ቀን '' ዘላቂ ልማት ለሀገራዊ መንሰራራት'' በሚል መሪ ቃል በተለያዩ የልማት ስራዎች ላይ ጉብኝት በማድረግ ተከብሯል።

በጉብኝቱ የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር እና መሬት አስተዳደር ቢሮ ሀላፊ የተከበሩ ኡመር አርባ ፣ የብልፅግና ፓርቲ አፋር ክልል ቅርጫፍ ፅ/ቤት የፖለቲካ እና አቅም ግምባታ ዘርፍ ሀላፊ የተከበሩ መሃመድ አህመድ ፣ የክልሉ ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች እና መንግስት ሰራተኞች ተገኝተዋል።

የአፋር ክልል ም/ርዕሰ መስተዳድር የተከበሩ ኡመር ኑር በመደመር መንግስት ፖሊሲዎች የአፋር ክልልን ሁለንተናዊ ለውጥ በተለያዩ ዘርፎች ላይ ማስመዝገብ መቻሉን ገልፀዋል።

ክልሉ ለግብርና ምቹ መሬት እና የውሃ ሀብት በአግባቡ በመጠቀም በመስኖ ልማት በክልሉ የማይታሰቡ የሚመስሉ የግብርና አብዮት ስራዎች በመስኖ ልማት ዘርፍ በማከናወን ትልቅ ማንሰራራት ተፈጥሯል ሲሉ ም/ርዕሰ መስተዳድሩ አንስተዋል።

በክልሉ በሁለት መልኩ የሚታወቀውን አዋሽ ወንዝን በመግራት ስጋቱን በመቀነስ በተፋሰስ አከባቢዎች ላይ በግብርናው ዘርፍ ከከፊል አርሶ አደር እስከ ትላልቅ ኢንቨስትመንስት ስራዎች በስፋት መከናወናቸውን እንዲሁ ገልፀዋል።

በክልሉ ከለውጡ በፊት ከፍተኛ መቀዛቀዝ ላይ የነበሩ የክልሉ ኢንቨስትመንት ፣ ኢንዱስትሪ እና ቱሪዝም ዘርፎች ሰፊ ትኩረት በመስጠት በስራ ዕድል ፈጠራ ፣ ገቢ ልማት እንዲሁም ምርታማነት ላይ የታዩ ለውጦች በዘላቂነት የማስቀጠል ስራዎች ተካናውኗል ሲሉ ገልፀዋል።

በክልሉ በተፈጥሮ እና ሰው ሰራሽ ጉዳዮች አማከኝነት የሚደርሱ እንዲሁም የባዳ እና ባንዳ ጫናዎችን በመቋቋም ፈተናዎችን ወደ እድል በመቀየር ጠንከራ ሀገር እና መንግስት ለመገንባት ትልቅ መሠረት ማፅናት መቻሉን ገልፀዋል።

የማንሰራራት ቀን ምሽቱን ስቀጥል የኢትዮጲያ የብልፅግና ትልሞቿ ፣ ፈተናዎችን ወደ ዕድል በመቀየር ያሳካቸቸው ድሎች እንዲሁም የነገዋን ጠንካረ መሠረት ላይ ያፀናቻቸው ትልሞች ላይ የሚያተኩር ፓናል ውይይት ይካሄዳል።

07/09/2026

Paagume 2 Ayro
''Saadiyyi Ayro''

Paagumek 2 hayttoh Ayro ''Sarrimaane le Daddos Baaxo Saadáh'' Inttah Tan Itrol Yessekexen.

Qafar Rakaakayak C/Prezxaanti Kee Ardi Xiinissoh Biiroh Saqal Tatruse Farmo.

Qafar Rakaakayak Naharsi Saqal Cajji Awwal Paagume 2 "Saadiyyi Ayro" Wagsiisaak Tatruse Farmo Saadiyyi Ayro Itiyoppiyah ...
07/09/2026

Qafar Rakaakayak Naharsi Saqal Cajji Awwal Paagume 2 "Saadiyyi Ayro" Wagsiisaak Tatruse Farmo

Saadiyyi Ayro Itiyoppiyah Saadiyya Inta Itrol Xeerih Tan Agat Mablal Nassakaxxeh Nan way Ni Baaxo Takku Nj Rakaakay Taturte Sanootat Centebbaaruk Tan Siyaasaay, Qidaddo kee Amni Aqayyaareera Xiiqil Taturak Aamantileeh, Yasgalle Daddaos Maddaga Fan Tabteh Tanim Qaddose .

Baaxoh Caddoh Gexso Taqabik Sarriinol Awquk Rekissooy, Sissikiih, Xer Udduurih Daddos Fayya Fan Abteh Tan Makcagguruk Yan Tabaatabsi Xiiq Abina kee Qaagoh Asta Kinnim Yescesse.

Dirrinuh Tan Baaxooy, Dariifa kee Baad Caddoh Xukkooka Ayyunti Debrime Sinni Xiiqil Tonnah Kaadu Doolat Cogdale Mablal Miraacise Miraaciini Macalal Diggowte Beeri Qaagoh Aydaadi Xisoh Duddi Ginniimeh Yaniimik Mayballa Kinnim Yiysixxige .

Ta Baaxoh Saadiyyih Aydaadi Amqussubiyyih Asmat Qafar Rakaakayal Abinah Geytimte Daddos Xalitte Kinnim Ascassuuk, Rakaakay Daboonah Dirab kee Hoxat Tan Daalissol Ulim Elle Aabuke Sinniih, Qaago Sinni Ardih Beyaanamih Aydaadi Mafdaga Milaaguk Lakal Beenih Yanin Margaqal Rekissoh Ikraaro kee Ogoysimle Macalal Milaagimtam Xiqtem Baxxaqse.

Qafar Rakaakayal Buqre Luddal Ayyunta kee Doolat Baxsaluk Efeq Daddoosul Caxaaxuwaay, Caxammiiru kee Qasri Buqreh Cogdaadit Rakaakay Isih Isi Dudda Dadlisaanamal Taamitak Geytimam Yescesse.

Inkih Yan Qafar Ayyunti Dacarsittoh Xiinaay, Buqre Abaay, Qunxaaneytaay, Inonti kee Abbobtiiy, Tonnah Kaadu Miraaciini Dagorti kee Daddos Maglableela Qimbisimeh Yan Aydaadi Asqassaabeey, Qidaddo Dadal kee Saadiyyi Gexsot Fayyale Macal kee Margaqal Ikoytiinu Kak Haysitak Foocah Haanam Faxximtaamih Seeco Tatrusem.

''የመጀመርያው አለም አቀፍ የፖለቲካ ፓርቲዎች የውይይት መድረክ የጋራ ብልፅግና፣ ፍትህና ርትዕ የተረጋገጠበት ዓለም ለመፍጠር አዲስ ምዕራፍ ከፋች ነው'' ክቡር አቶ አደም ፋራህ የብልፅግና ...
07/09/2026

''የመጀመርያው አለም አቀፍ የፖለቲካ ፓርቲዎች የውይይት መድረክ የጋራ ብልፅግና፣ ፍትህና ርትዕ የተረጋገጠበት ዓለም ለመፍጠር አዲስ ምዕራፍ ከፋች ነው'' ክቡር አቶ አደም ፋራህ የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንት እና ዋና ፅ/ቤት ኃላፊ

የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት ክቡር አቶ አደም ፋራህ በሴኡል ደቡብ ኮሪያ በመካሄድ ላይ በሚገኘው ዓለም አቀፍ የፖለቲካ ፓርቲዎች (ICDPP) የምክክር መድረክ ላይ በመሳተፍ ላይ ይገኛሉ።

ይህ ዓለም አቀፍ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምክክር (ICDPP) ከኤሺያ፣ ከአፍሪካ፣ ከአሜሪካ እና ከአውሮፓ የተወጣጡ የፖለቲካ ፓርቲዎች እና መሪዎችን የሚያገናኝ መድረክ ነው።

የመድረኩ ዋነኛ ዓላማ በልዩ ልዩ የፖለቲካ ባህሎች መካከል የእርስ በእርስ ግንዛቤን ማሳደግ፣ እምነትን ማጠናከር፣ በጋራ ዓለም አቀፋዊ ጉዳዮች ላይ ሀሳብ መለዋወጥ እና ቀጣይነት ያለው አለም አቀፍ ትብብር የሚደረግባቸውን መንገዶችን ማመላከት ነው።

በመድረኩ እየተሳተፉ የሚገኙት የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንት ክቡር አቶ አደም ፋራህ፣ የምክክር መድረኩ ሊኖረው ስለሚገባው ተልዕኮ በተለይም በዓለም አቀፍ ደረጃ የፖለቲካ ፓርቲዎች ዲፕሎማሲ ሚና፣ አወቃቀር፣ ሊከተላቸው የሚገቡ መርሆዎች እና በብልፅግና ፓርቲ የመደመር እሳቤ ተሞክሮዎች ዙሪያ ንግግር አድርገዋል።

ክቡር አቶ አደም በንግግራቸው፣ የምክክር መድረኩ የፖለቲካ ፓርቲዎች የሕዝብን ፍላጎት የሚያንፀባርቁ መሪዎችን የሚያፈሩና ፖሊሲዎችን የሚቀርፁ መሆናቸውን ታሳቢ ማድረግ እንዳለበት አንስተዋል።

መድረኩም በመንግስታት መደበኛ ዲፕሎማሲ እና በሕዝቦች መካከል ባለው ግንኙነት መካከል ያለውን ክፍተት የሚሞላ ወሳኝ የጋራ መድረክ ሊሆን እንደሚገባ ገልፀዋል።

በተለይም ዋና ትኩረቱ እምነትን መገንባት፣ የርዕዮተ-ዓለም ውጥረትን መቀነስ፣ ተቋማዊ ልምድ ልውውጥን ማጠናከር፣ ኃላፊነት የሚሰማቸው መሪዎች ማፍራት ላይ መተባበር፣ ግጭቶችን መከላከል እና ዓለም አቀፍ ትብብርን ማጠናከር መሆን እንዳለበት አብራርተዋል።

በተጨማሪም የሃሳብ ብዝሃነት፣ ሉዓላዊ እኩልነት፣ አካታችነት፣ ተቋማዊነት እና ተጨባጭ ትብብር መርሆዎች ሊመራ እንደሚገባም አክለዋል።

የምክክር መድረኩ በዋናነት ቅድሚያ ሊሰጣቸው የሚገባቸውም ዋና ዋና ጉዳዮች ሶስት መሆናቸውንም አንስተዋል።

የመጀመሪያው ዲሞክራሲያዊና ተቋማዊ ጥንካሬ ማረጋገጥ ሲሆን በዚህም ሰላማዊ ምርጫን፣ የህግ የበላይነትን እና ጠንካራ ተቋማትን መገንባት ማተኮር አስፈላጊ መሆኑን ገልፀዋል።

ሁለተኛው አካታች ልማትና ኢኮኖሚያዊ ትራንስፎርሜሽን ማምጣት ሲሆን ከዚህ አኳያ ብልፅግና ፓርቲ የሚመራበት የመደመር እሳቤ መሰረት በማድረግ፣ ሁሉንም አቅሞች ተጨማሪ እሴትና አቅም በሚፈጥር አኳኃን ደምሮ በመጠቀም በማጎልበት የምግብ ሉዓላዊነትን፣ ዲጂታል ትራንስፎርሜሽንን እና ዘርፈ ብዙ ምርታማነትን ማረጋገጥ እንደሚቻል አንስተዋል።

ትኩረት ሊሰጣቸው ከሚገቡ ጉዳዮች መካከል በሶስተኛነት ያነሱት ሰላም ግንባታና ቅድመ-ግጭት መከላከልን ማጠናከር ሲሆን ከጉዳዩ ጋር በተያያዘ የፖለቲካ ፓርቲዎች ግጭትንና ጂኦፖለቲካዊ ውጥረቶች ለመከላከል የሚያስችሉ ምክክሮች ላይ ትኩረት መስጠት እንዳለባቸው ገልፀዋል።

በአጠቃለይ ክቡር አቶ አደም፣ ዓለም አቀፍ የፖለቲካ ፓርቲዎች የምክክር መድረክ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች መርህን መሰረት ያደረገና በተግባር ላይ ያተኮረ ትብብራቸውን እንዲያጠናክሩ ካስቻለ ዘላቂ ሰላምና መረጋጋት፣ የጋራ ብልፅግና፣ ፍትህና ርትዕ የተረጋገጠበት ዓለም ለመፍጠር አዲስ ምዕራፍ እንደሚከፍት እምነታቸው መሆኑን አንስተዋል።

የጳጉሜን 2 “የማንሰራራት ቀን”ን አስመልክቶ ከአፋር ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ርዕሰ መስተዳድር ክቡር ሀጂ አወል አርባ የተላለፈ መልእክት “የማንሰራራት ቀን”ን “የኢትዮጵያ ማንሰራራት” በሚ...
07/09/2026

የጳጉሜን 2 “የማንሰራራት ቀን”ን አስመልክቶ ከአፋር ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ርዕሰ መስተዳድር ክቡር ሀጂ አወል አርባ የተላለፈ መልእክት

“የማንሰራራት ቀን”ን “የኢትዮጵያ ማንሰራራት” በሚል ታላቅና አርቆ አሳቢ ሀገራዊ መሪ ቃል ስናከብር፣ ሀገራችንም ሆነች ክልላችን ያለፉትን ዓመታት ውስብስብ የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚና የደኅንነት ፈተናዎች በጽናት አልፈው ወደ አስተማማኝና ሁለንተናዊ የዕድገት ምዕራፍ መሸጋገራቸውን በታላቅ ኩራት እያበሰርን ነው።

ሀገራዊ ጉዟችን ከቀውስና ከውጥረት አዙሪት በዘላቂነት ወጥቶ ወደ ተቋማዊ፣ ፈጣንና የረጅም ጊዜ የልማት ከፍታ ያደረገውን ስትራቴጂያዊ ሽግግር የሚያረጋግጥ የጽናት፣ የተግባርና የብሩህ መንፈስ መግለጫ ነው።

ተደራራቢ ሀገራዊ፣ ቀጣናዊና ዓለም አቀፋዊ ተጽዕኖዎችን በህዝባችን ያልተበገረ ጽናት፣ እንዲሁም በመንግሥታችን በጥበብና በበሰለ እይታ የተመራ አመራር ማልፋታችን በገዛ እጃችን የተረጋገጠ ብሩህ ነገን የመገንባት ታሪካዊ አቅም ላይ መድረሳችንን ቁልጭ አድርጎ ያሳያል።

የዚህ ሀገራዊ ማንሰራራትና የታሪክ መታደስ ሕያው ማረጋገጫ ደግሞ በአፋር ክልል በተግባር የተመዘገቡት አበይትና ታሪካዊ የልማት ስኬቶች ናቸው። ክልላችን ለዘመናት በተዛባና አሳሳች ትርክት “ምንም የማያበቅልና ተስፋ የሌለው” ተደርጎ ይገለጽ የነበረበት የታሪክ ምዕራፍ፣ ከለውጡ ወዲህ በተካሄደው ቆራጥ አመራር፣ መዋቅራዊ እቅድና በተቀናጀ ትጋት ሙሉ በሙሉ እንዲዘጋ ተደርጓል።

በክልላችን በግብርናው ዘርፍ የታየው አብዮታዊና መዋቅራዊ ለውጥ—በተለይም በቆላማ ስንዴ ምርታማነት፣ በስፋት በተከናወነው የመኖ ልማት፣ በአትክልትና ፍራፍሬ፣ በዘመናዊ የመስኖ አወቃቀር ዝርጋታና በአግሮ-ፕሮሰሲንግ የተመዘገቡት አስደናቂ ውጤቶች—ክልሉን ከጥገኝነትና እርዳታ ጠባቂነት ወደ እውነተኛ አምራችነትና ሀገራዊ ምርት አቅራቢነት የተሸጋገረበትን አዲስ ምዕራፍ ፈጥሯል።

ቀደም ሲል በድርቅና በምግብ ዋስትና ዕጦት ይገለጽ የነበረው የአፋር ምድር፣ ዛሬ በህዝባችን ላብ፣ ጥረትና ትጋት የኢትዮጵያ የምግብ ዋስትና ዋና መደገፊያና የሀገሪቱ የኢኮኖሚ ማንሰራራት ግንባር ቀደም መሪ ተዋናይ ለመሆን በቅቷል።

ከዚህ ግብርናን መሠረት ካደረገ ስኬት ጎን ለጎን የተከናወኑት ዘመናዊ የመሰረተ ልማት ዝርጋታዎች፣ የማህበራዊ አገልግሎት ተቋማት ተዳራሽነትና ማስፋፋት፣ እንዲሁም የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ጥረቶች የዜጎቻችንን የእለት ተእለት ህይወት፣ የጤና ሁኔታና የኑሮ ደረጃ መዋቅራዊ በሆነ መልኩ ለውጠዋል።

እነዚህ በገሃድ የሚታዩና በተግባር የተደገፉ አዎንታዊ እውነታዎች ክልላችንና ሀገራችን በጽኑና በማይናጋ መሠረት ላይ ሆነው ወደ ላቀ የዕድገት ማዕበል መሸጋገራቸውን የሚያረጋግጡ በመሆናቸው፣ ዘላቂ ሰላማችንን በማፅናትና አዎንታዊ ሀገራዊ ትረካዎችን በማጎልበት የጀመርነውን የዕድገት ጉዞ አፋጥነን ማስቀጠል ይጠበቅብናል።

ስለሆነም መላው የአፋር ህዝብ፣ ክቡራን አርብቶ አደሮች፣ ወጣቶች፣ እናቶችና አባቶች፣ እንዲሁም የአመራር አካላትና የልማት ባለድርሻ አካላት የተጀመረውን የታሪክ መታደስ፣ የኢኮኖሚ እድገትና የማንሰራራት ጉዞ በላቀ ትጋት፣ ቁርጠኝነትና የባለቤትነት ስሜት እንድታስቀጥሉ ጥሪዬን አቀርባለሁ።

በጽኑ አዎንታዊ አስተሳሰብ፣ በበሰለ የሥራ ባህልና በጠበቀ ህብረት በመቆም የኢትዮጵያን ማንሰራራት በተግባር እውን ማድረጋችንን አጠናክረን እንቀጥላለን።

07/09/2026
Paagume 1 Farakkah Ayro Baaxo Caddol Kullii Langittel Qunduguguluk Awquk Abneh Nan Taamomi Farakka Le Xaloot Geysise. Pa...
06/09/2026

Paagume 1
Farakkah Ayro

Baaxo Caddol Kullii Langittel Qunduguguluk Awquk Abneh Nan Taamomi Farakka Le Xaloot Geysise.

Paagume Ayroorat Warraye Sanat Farakka Luk Abbinowte Abnite Sarrimaane Fayya Fan Saadisak , Qusba Sanatih Soonol Xiggaluk Elle Taamitnuh Akah Massowna Uddur Kinni.

Massakaxxale Macammad Acmad Qali

Leedá Paartik Qafar Rakaakayih Luddih K/Buxak Siyaasa Kee Duddi Gablusiyih Langih Saqala

Afak Culta Murtitte Baaxoh Addih Murtittet Milaagak Baaxo Caddol Farakka Le Taama Abbinowte. Ciggila Prezxaanti Quma Nur...
06/09/2026

Afak Culta Murtitte Baaxoh Addih Murtittet Milaagak Baaxo Caddol Farakka Le Taama Abbinowte.

Ciggila Prezxaanti Quma Nur
********

Paagumek , 1 hayttoh Ayro Farakkah Ayro ,

''Farakká Sarrimaane Le Fayyah'' Inta Itrol Rakaakay Caddol Yessekexen.

Farakkah Ayroh Massakaxxal Qafar Rakaakayak Ciggila Prezxaanti Massakaxxale Qumar Nur , Leedá Paartik Qafar Rakaakayih Luddih K/buxak Siyaasa kee Duddi Gablusiyih Langih Saqal Massakaxxale Maacammad Acmad , Rakaakayak Fayyale Saqoltiy, Doolat Taama Abeenit kee Samará-Loogiyi Magaalah Xiinissoh Miraacinnu Kee Ummatta Kee Seeco Akah Abem Qibni Edde Yengele.

Qafar Rakaakayak Ciggila Prezxaantiy, Ardi Xiinissoh Biiroh Saqal Massakaxxale Qumar Nur Sanat 2018 Liggidal Baaxo Caddol Qembisen Itiyoppiya Tamrutay Uguugusut Baxaabaxsale Sanaaqarta Xisak Farakka Leh Tan Taama Edde Abbinowtem Qaddoose.

Buqre Luddal Qafar Ummatta Fidinih Tan Baaxo Kee Lee Gadda Aaluk Soonoh Sugte Baxaabaxsale Murtitte Abqurak Sanat Addat 140 Alfik Daga Yakke Hiktaar Abqurak Murtisso Qadad Farakka Edde Haanam Xiqqimtem Ciggila Prezxaanti Qaddose.

Qafar Rakaakay Baxsaluk Culenti Langil Baxsale Maaqatta Beyak Qemboh Addah Farakka Le Xaloot Elle Geytimem Kee Fooca Fanah Sarrimaanel Xiggowak Gexwaaa Gexsit Kinnim Massakaxxale Qumar Nur Yescesse.

Farakkah Ayroh Massakaxxal Samara-Loogiyi Magaalal Geytimtta 'Istaama Qasbo Masnaqatat Gufne tekke.

Tonnah Kaadu Miraacinnuy , Doolat Taama Abeenit Kee Samara-Loogiyi Magaalah Ummatta Coox Xabsih Taddira Gexsen.

Maddur Luddal Geytimte Mangatinaan Farakka , Gexsi Luddittel Akah Xiggowtanah Baar le Paanal Walal Gexsen.

Qagitaak Baxaabaxsale Luddittel Investi Abak Meqe Xaloot Tuybule Dagortih Faatit kee Mamaxaga Yacenimih Taddira Gexsen.

Address

Afar Region
Logya

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Afar Prosperity party - ብልጽግና posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share