Menz Gera Woreda Council Office

Menz Gera Woreda Council Office Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Menz Gera Woreda Council Office, Government Organization, mehalmeda, Mehal Meda.

🏆🏆🏆እንኳን ደስ አለን እንኳን ደስ አላችሁ፡፡🏆🏆🏆የመ/ጌ/ም/ወ/ም/ቤት /ቤት በ2017 በጀት አፈፃፀም በተደረገ የስራ አፈጻፀም ግምገማ ሁለተኛ ደረጃ መውጣቱ ይታወቃል፡፡የሰ/ሽዋ ዞን የተዋ...
23/09/2025

🏆🏆🏆እንኳን ደስ አለን እንኳን ደስ አላችሁ፡፡🏆🏆🏆
የመ/ጌ/ም/ወ/ም/ቤት /ቤት በ2017 በጀት አፈፃፀም በተደረገ የስራ አፈጻፀም ግምገማ ሁለተኛ ደረጃ መውጣቱ ይታወቃል፡፡
የሰ/ሽዋ ዞን የተዋረድ ም/ቤቶች ፎረም በደብረብርሀን ከተማ በደማቅ ሁኔታ ተካሄዷል፡፡ በፎረሙ ላይ የከተማ የወረዳ ም/ቤት አፈ-ጉባኤዎች፣ ም/አፈ-ጉባኤዎችና የቋሚ ኮሚቴዎች ሰብሳቢዎች ተሳትፈዋል፡፡
ፎረሙ የተዋረድ ም/ቤት የ2017 በጀት አመት እቅድ አፈፃፀም ግምገማና የቀጣይ የ2018 ዓ.ም እቅድ ትውውቅ መርሀ-ግብር አድርጓል፡፡
በበጀት አመቱ የመንዝ ጌራ ምድር ወረዳ ም/ቤት የላቀ ተግባር በመፈፀም ከ22 ወረዳ ም/ቤቶች ጋር ተወዳድሮ 2ኛ ደረጃን አግኝተናል፡፡
ለዚህ ውጤት መምጣት የቀበሌ ም/ቤቶቻችን ፣የወረዳ ም/ቤት ቋሚ ኮሚቴዎች፣ የወረዳ ም/ቤት አባላት እና ባለድርሻ አካላት ለነበራቸው አስተዋጽኦ በመንዝ ጌራ ምድር ወረዳ ም/ቤት ስም አመሰግናለሁ ፡፡
የመ/ጌ/ም/ወ/አፈ-ጉባኤ አቶ መከተ ጌታቸው፤

ምክር ቤቶች  የሕዝብ ውክልና ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ የአፈ ጉባኤዎች ፎረም ልምድና ተሞክሮ በማለዋወጥ ፋይዳው የጎላ መኾኑ ተገለጸ ደብረ ብርሃን ከተማ የሰሜን ሸዋ ዞን ወረዳዎች እና ከተማ ...
21/09/2025

ምክር ቤቶች የሕዝብ ውክልና ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ የአፈ ጉባኤዎች ፎረም ልምድና ተሞክሮ በማለዋወጥ ፋይዳው የጎላ መኾኑ ተገለጸ

ደብረ ብርሃን ከተማ የሰሜን ሸዋ ዞን ወረዳዎች እና ከተማ አስተዳደሮች የምክር ቤት አፈ ጉባኤዎች ፎረም መካሄድ ጀመረ።

የደብረ ብርሃን ከተማ ከተማ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ እና የሰሜን ሸዋ ዞን የምክር ቤት አፈ ጉባኤዎች ፎረም አስተባባሪ የተከበሩ መንግስቱ ቤት የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር አድርገዋል።

በንግግራቸው እንዳነሱት የፎረም ዋና ዓላማ ምክር ቤት ውክልናቸውን በአግባቡ እንዲወጡ ልምድና ተሞክሮ በማለዋወጥ አቅም የሚፈጥር ነው ብለዋል።

በተለይም የምክር ቤቶችን አሰራር፣ የክትትል እና ቁጥጥር ሥርዓት ከሚሸረሽሩ አሰራሮች ለመውጣት የሚያስችል ስለመኾኑም አብራርተዋል።

በመኾኑም በመድረኩ ለውይይት መነሻ የሚቀርበውን ሰነድ ተከታትለው ንቁ ተሳትፎ እንዲያደርጉ አሳስበዋል።

የደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ጽህፈት ቤት ኃላና የዕለቱ የክብር እንግዳ አቶ በኃይሉ ገብረህይወት መድረኩን ሲከፍቱ እንደተናገሩት ደብረ ብርሃን ከጊዜ ወደ ጌዜ እያደገች ያለች ከተማ መኾኗን አንስተዋል።
ለከተማዋ ዕድገት ደግሞ በየደረጃው ያሉ ምክር ቤቶች ያበረከቱት አስተዋጽኦ ከፍተኛ በመኾኑ አመስግነዋል።
የሰሜን ሸዋ ዞን ተዋረድ ምክር ቤቶች ዕቅድ ዝግጅት ክትትልና ግምገማ ቡድን መሪ አቶ ኃብታም ዘውዴ ለውይይት መነሻ ሰነድ አቅርበዋል።
የደብረ ብርሃን ከተማ ዋና አፈ ጉባኤ የተከበሩ መንግስቱ ቤተ፣የአማራ ክልል ምክር ቤት የሰው ሃብትና ቱሪዝም ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ የተከበሩ አበራ ፋንታሁንን ጨምሮ የሰሜን ሸዋ ዞን ወረዳዎች እና ከተማ አስተዳደሮች አፈ ጉባኤዎች፣ቋሚ ኮሚቴዎች እና ተጋባዥ እንግዶች ተገኝተዋል።

የመ/ጌ/ም ወረዳ ም/ቤት ፅ/ቤት ከጠቅላላ ሰራተኛው ጋር እና ከወረዳው   ቋሚ ኮሚቴዎች ጋር  በ2አጀንዳዎቾ ላይ ውይይት አደረገ። ‎‎ቀን 23/11/2017ዓ.ም (የመ/ጌ/ም/ወ/ም/ቤት)‎‎1...
30/07/2025

የመ/ጌ/ም ወረዳ ም/ቤት ፅ/ቤት ከጠቅላላ ሰራተኛው ጋር እና ከወረዳው ቋሚ ኮሚቴዎች ጋር በ2አጀንዳዎቾ ላይ ውይይት አደረገ።
‎
‎ቀን 23/11/2017ዓ.ም (የመ/ጌ/ም/ወ/ም/ቤት)
‎
‎1 የሴክተሮች የ4ኛ ሩብ ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም የቋሚ ኮሚቴዎች የምልከታ ሪፖርት፣
‎2 የ2018 በጀት ዓመት የ3ቱም ዘርፍ የቋሚ ኮሚቴዎች ዕቅድ ትውውቅ ማድረግ የሚሉት ሲሆኑ:-
‎
‎የመ/ጌ/ም ወረዳ ም/ቤት ፅ/ቤት አፈ- ጉባኤ የተከበሩ አቶ መከተ ጌታቸው ቋሚ ኮሚቴው ክትትል ቁጥጥር ሲያደርግ የህዝብ ውክልናን የያዘ መሆኑና የአሰራር ስነ ስርዓቱን ተከትሎ የሚሰራ ቋሚ ኮሚቴ መሆኑን ገልፀው የምልከታ ሪፖርቱና ዕቅዱ መቅረብ እንዳለበት ገልፀዋል።
‎
‎የመ/ጌ/ም ወረዳ ም/ቤት ፅ/ቤት የህ/ክ/ቁጥጥርና ሙያዊ ድጋፍ ቡድን መሪ እና የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ የሆኑት የተከበሩ ወ/ሮ ሕይወት በዛብህ የምልከታ ሪፖርቱንና የ3ቱንም ዘርፍ ማለትም የህግና ፍትህ ቋሚ ኮሚቴ፣ የኢኮኖሚ በጀትና ፋይናንስ ቋሚ ኮሚቴ እና የሴቶች ህፃናትና ማህበራዊ ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ የሚሉትን የተጠቃለለ ዕቅድ በዝርዝር አቅርበዋል።
‎
‎በተጨማሪም ቋሚ ኮሚቴዎቹ ምልከታ ሲደረግ በተጨባጭ መረጃ በመያዝ፣ ጥቆማዎችን በመቀበል የተሰበሰቡ መረጃዎችን ይዘን ሲሆን በዚህ 4ኛ ሩብ ዓመት ምልከታ ያደረግንባቸው 9ሴክተር መ/ቤቶች ተገቢና ወሳኝ ሴክተሮች መሆኑን አንስተው ሁል ጊዜ የተገመገመ ሪፖርት ለጉባኤው ሲቀርብ የጋራ እውቅና እንዲኖረን ያስችለናል በማለት የቀረበውም ዕቅድ የሚያሰራ መሆኑን እና የሁሉንም ባለድርሻ አካላት ርብርብ የሚጠይቅ ነው በማለት ውይይቱ ተጠናቋል።

30/07/2025
30/07/2025
26/07/2025
25/07/2025
የመ/ጌ/ም ወረዳ ም/ቤት ፅ/ቤት የበጀት ዓመቱን ዕቅድ አፈፃፀም ግምገማ አደረገ። ‎‎ቀን 03/11/2017ዓ.ም (የመጌምወምቤት)‎‎የመ/ጌ/ም/ወ/ም/ቤት ፅ/ቤት የበጀት ዓመቱን ዕቅድ አፈፃፀ...
10/07/2025

የመ/ጌ/ም ወረዳ ም/ቤት ፅ/ቤት የበጀት ዓመቱን ዕቅድ አፈፃፀም ግምገማ አደረገ።
‎
‎ቀን 03/11/2017ዓ.ም (የመጌምወምቤት)
‎
‎የመ/ጌ/ም/ወ/ም/ቤት ፅ/ቤት የበጀት ዓመቱን ዕቅድ አፈፃፀም ከፅ/ቤቱ ባለሙያዎች ጋር በጋራ እየገመገመ ይገኛል። ተግባሮቹን ስንገመግም በጥንካሬ እና በእጥረት የተተገበሩ ሲሆን በጥንካሬ የተፈፀሙትን አስቀጥለን እጥረቶቻችንን ደግም በቀጣይ የዕቅዳችን አካል አድርገን በቀጣይ ከዚህ የበለጠ ውጤት ለማምጣት ሁሉም ባለሙያ የበኩሉን ድርሻ መወጣት አለብን በማለት ግምገማውን አጠናቀናል።

የመ/ጌ/ም ወረዳ ም/ቤት ቋሚ ኮሚቴዎች  ውይይት አደረጉ።‎‎ቀን 13/10/2017ዓ.ም (የመጌምወምቤት)‎‎የውይይቱ አጀንዳ :- የ4ኛ ሩብ ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም ምልከታ  በተመለከተ ሲሆን፣ ...
20/06/2025

የመ/ጌ/ም ወረዳ ም/ቤት ቋሚ ኮሚቴዎች ውይይት አደረጉ።
‎
‎ቀን 13/10/2017ዓ.ም (የመጌምወምቤት)
‎
‎የውይይቱ አጀንዳ :- የ4ኛ ሩብ ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም ምልከታ በተመለከተ ሲሆን፣
‎
‎የወረዳው ም/ቤት ጽ/ቤት ኃላፊ የተከበሩ አቶ መከተ ጌታቸው እንደገለፁት በበጀት ዓመቱ የነበረን የቋሚ ኮሚቴ ምልከታ የተሰጠንን ኃላፊነት እና አሰራር ስነ ስርዓቱን በመከተል ክትትል ቁጥጥር ያደረግን ሲሆን ያየናቸው ሴ/መ/ቤቶች ወረዳው ችግርም ውስጥ ሆኖ ጥሩ አፈፃፀም ያየንበት እና በርካታ የመልካም አስተዳደር ችግሮች እፈታንና እውቅና የሚሰጠውን አካልም በወረዳው ም/ቤትም ዕውቅና እየሰጠን የሄድንበት በጀት ዓመት ነበር ብለዋል ።
‎
‎የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ የሆኑት ወ/ሮ ሕይወት በዛብህ እንደገለፁት እስካሁን የነበረው የቋሚ ኮሚቴ ምልከታ ጥሩ ነበር አሁን ግን ከወትሮ በተለየ መልኩ የተለየ የምልከታ ቼክ ሊስት በማዘጋጀት የክትትል ቁጥጥር ስራችንን ማከናወን አለብን ብለዋል።
‎
‎የወረዳው ቋሚ ኮሚቴዎች በተያዘው አጀንዳ እና በተነሱት ሃሳቦች መስማማታቸውን በመግለፅ በቀጣይ ምልከታ የሚደረግባቸውን 9 ሴክተር መ/ቤቶች ማለትም_ ትምህርት፣ሲቪል ሰርቪስ፣ ኮሙኒኬሽን፣ ገጠር መሬት፣ ግብርና፣ እስፖርት፣ማዕድን፣ ኢንቨስት መንት እና ሰላም ደህንነት ፅ/ቤትን በምረጥ ውይይቱ ተጠናቋል።

Address

Mehalmeda
Mehal Meda

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Menz Gera Woreda Council Office posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share