መሐል ሜዳ ከተማ ገቢዎች ጽ/ቤት

መሐል ሜዳ ከተማ ገቢዎች ጽ/ቤት Welcome to the official page of the mehal meda Revenue Office.

የግብር ከፋዮች የውይዮት መድረክ አካሄደ።ነሐሴ 17/2018 ዓ.ም የመ/ሜዳ ከተማ አሰ/ገቢዎች ጽ/ቤት ከግብር ከፋዩ ጋር ውይይት አደረገ።የመ/ሜዳ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ጽ/ቤት በ2019 ...
23/08/2026

የግብር ከፋዮች የውይዮት መድረክ አካሄደ።

ነሐሴ 17/2018 ዓ.ም የመ/ሜዳ ከተማ አሰ/ገቢዎች ጽ/ቤት ከግብር ከፋዩ ጋር ውይይት አደረገ።

የመ/ሜዳ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ጽ/ቤት በ2019 የሚሰበሰበውን ዕቅድ ትውውቅ እና በተሻሻለው የገቢ ግብር በአዋጅ ቁጥር 301/2018 እና የከተሞች አገልግሎት ግብር ማስከፈያ ደንብ ቁጥር 257/2018 ዓ.ም መሰረት በማድረግ የተዘጋጀውን ሰነድ የጽ/ቤቱ ኃላፊ አቶ መለሰ በላይግዛው አቅርበዋል።
አቶ መለሰ እንዳሉት በአዲሱ የቀን ገቢ የግብር ጥናት መሰረት ሁሉም ግብር ከፋይ በስልኩ ሜሴጅ በደረሰው በ30 ቀን ውስጥ መክፈል አለበት። ቅሬታ አለኝ የሚል ግብር ከፋይ ቅሬታ የማቅረብ መብቱ የተጠበቀ በመሆኑ እስከ 21 ቀን ድረስ ማቅረብ ይችላል በማለት አንስተዋል።

ግብሩን በተባለው ጊዜ የማይከፍል ከሆነ ለተጨማሪ ቅጣትና ወለድ ይዳረጋል ብለዋል።

የከተማ አገልግሎት ግብር አከፋፈልን በተመለከተ የተሻሻለው ደንብ ዋና ዋና ነጥቦችን አንስተው ግንዛቤ በማስጨበጥ ሁሉም በደንብ ቁጥር 257/2018 ዓ.ም መሰረት መክፈል አለበት ብለዋል።

በመጨረሻም የቀረበውን ሰነድ መነሻ በማድረግ በርካታ ጥያቄዎች ተነስተው ምላሽ ተሰጥቶባቸው እና መልካም መግባባት ተፈጥሮ የውይይት መድረኩ ተጠናቋል።
https://www.facebook.com/share/14j8LpeCdGf/
telegram : https://bit.ly/4fivr4o

የሀዘን መግለጫ በመ/ሜዳ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ጽ/ቤት በተለያዩ የስራ መደብ ላይ ተዘዋውረው ሲሰሩ የነበሩ አቶ ይልማ አምታታው ባደረባቸው ህመም ምክነያት በህክምና ሲረዱ ቆይተው ዛሬ በ1...
21/08/2026

የሀዘን መግለጫ
በመ/ሜዳ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ጽ/ቤት በተለያዩ የስራ መደብ ላይ ተዘዋውረው ሲሰሩ የነበሩ አቶ ይልማ አምታታው ባደረባቸው ህመም ምክነያት በህክምና ሲረዱ ቆይተው ዛሬ በ15/12/2018 ዓ.ም ከዚህ ዓለም አርፈዋል። ነፍሳቸውን በአፀደ ገነት ያሳርፍልን!!!
የጽ/ቤቱ ሰራተኞች

06/08/2026

በሰሜን ሸዋ ዞን በ2019 በጀት ዓመት 9 ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ለመሰብሰብ ታቅዶ እየተሠራ ነው።

​ደብረ ብርሃን፤ ሐምሌ 29/2018 ዓ.ም. (አሚኮ)፦ የዞኑ ገቢዎች መምሪያ የግብር ትምህርት እና ኮሙዩኒኬሽን ዋና ሥራ ሂደት አስተባባሪ እሸቱ ሽፈራው ለአሚኮ እንደገለጹት፤ በዞኑ በሚገኙ ወረዳዎች እና ከተማ አስተዳደሮች 9 ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ለመሰብሰብ ታቅዷል።

​ለዚህም እንዲያግዝ ከ28 ሺሕ በላይ ግብር ከፋዮች የቀን ገቢ ግምታቸው እንዲጠና ተደርጓል። ከ18 ሺሕ በላይ የሚሆኑት ውሳኔው መድረሱን አቶ እሸቱ አክለዋል።

​ገቢው የሚሰበሰበው ከመደበኛና ከአገልግሎት ገቢ መሆኑን የተናገሩት ሥራ ሂደት አስተባባሪው፤ እስካሁን ድረስ ከ1,700 ግብር ከፋዮች 17 ነጥብ 7 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ ከተለያዩ አርእስቶች ተሰብስቧል።

​የጥናቱ ውሳኔ የደረሳቸው ነጋዴዎችም ግብራቸውን በወቅቱ እንዲከፍሉ ግብር ሰብሳቢው መሥሪያ ቤት ጥሪ አቅርቧል።

​ዘጋቢ፦ ፋንታነሽ መሀመድ

20/07/2026

የመ/ሜዳ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ጽ/ቤት የ2018 በጀት ዓመት ማጠናቂያ የምስጋና እና የሽልማት ፕሮግራም አካሄደ።

የመ/ሜዳ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ጽ/ቤት
ሐምሌ 12/2018

በፕሮግራሙ የመ/ሜዳ ከተማ አስተዳደር አስተባባሪ አመራሮች፣በበጀት አመቱ የተሻለ ታክስ ያስገቡ ግብር ከፋዮች፣አጋር አካላት ፣ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶችና የጽ/ቤቱ አጠቃላይ ሰራተኞች በተገኙበት የተካሄደ ሲሆን የጽ/ቤቱ ኃላፊ አቶ መለሰ በላይ ግዛው በበጀት አመቱ የተከናወኑ ዋና ዋና ተግባሮችን በአጭሩ አቅርበዋል። በበጀት ዓመቱም ከባለፈው በጀት አመት ጋር ሲነፃፀር ከ41ሚሊዮን ብር በላይ በልዩነት በመሰብሰብ የተለያዩ ስራ ሂደቶች ከ1- 5 በመውጣት የተሻለ ደረጃ ይዘው አጠናቀዋል በማለት አቅርበዋል። ይህን መነሻ በማድረግ በርካታ የውይይት ሀሳቦች ተነስተው ውይይት ተደርጎባቸዋል።
ለአፈፃፀሙ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ላበረከቱ ባለሙያዎች፣የስራ ሂደቶች፣ግብር ከፋዩች እና አመራሮች የምስክር ወረቀትና ሽልማት ተበርክቷል።
በመጨረሻም ክቡር ከንቲባው አቶ ጌታቸር ባይሳሳሁ እና የብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊው አቶ ደረሰ ሙላቴ በበጀት አመቱ የተጣለውን የገቢ ዕቅድ ለማሳካት የተደረገውን ጥረትና የመጣውን ውጤት በማድነቅ በቀጣይ መሰራት ያለባቸውን ተግባራት ጥብቅ የስራ ስምሪት በመስጠት ፕሮግራሙ ተጠናቋል።

https://www.facebook.com/share/14j8LpeCdGf/
Telegram : https://bit.ly/4fivr4o

19/07/2026
16/07/2026

በ12 ወራት ከ5 ቢሊዮን ብር በላይ ግብር ተሰበሰበ!!
የሰሜን ሸዋ ዞን ገቢዎች መምሪያ በ2018 በጀት ዓመት በዞኑ ስር ከሚገኙ 31 ወረዳና ከተማ አስተዳደሮችን በማስተባበር የህብረተሰቡን የልማት እና የመልካም አስተዳደር ጉድለት መቅረፍ የሚያስችል 5.4 ቢሊዬን ብር ገቢ ለመሰብሰብ ዕቅድ አዘጋጅቶ በበጀት ዓመቱ የተሻለ ውጤት ለማምጣት ከፍተኛ ርብርብ ሲያደርግ ቆይቷል ፡፡
በዞኑ ስር በበጀት ዓመቱ ለመሰብሰብ ከታቀደው 5,382,020,938 ብር ውስጥ 4.803,391,949 ቢሊዬን ብር የሚሆነውን ከመደበኛ ገቢ እንዲሁም 578.628,981 ብር የሚሆነውን ደግሞ ከከተማ አገልግሎት ገቢ ለመሰብሰብ የታቀደ ሲሆን ባለፉት 12 ወራት የተመዘገበው ዓፈፃፀም ከመደበኛ ገቢ 4,595,345,023 ብር 95.67% ከከተማ አገልግሎት 443,543,019 ብር 76.65% ሲሆን ከጥቅል ዓመታዊ ዕቅድ ደግሞ ክንውን 5,038,888,042 ብር 93.6% ተሰብስቧል፣
ይህ ውጤት በ2018 በጀት ዓመት በ12 ወር የተሰበሰበው 5,038,888,042 ብር ገቢ በ2017 በበጀት ዓመቱ ከነበረው ተመሣሣይ ወቅት 3,618,802,748 ብር ጋር ሲነፃፀር 1,420,085,294 ብር ብልጫ ወይም 39.2% እድገት ያለው ገቢ በመሰብሰብ ከፍተኛ ውጤት የተመዘገበ ሲሆን ለመጣው ውጤት የገቢ ተቋሙ ባለሙያና አመራር፤ ታማኝ ግብር ከፋዮች እና በየደረጃው ያለ አመራር ባደረጉት ያላሰለሰ ጥረት የተመዘገበ አመርቂ ውጤት ነው ለቀጣዩ በጀት ዓመት መነሻ የሚሆን ጥሩ መሰረት የተጣለበት ዓመት ነው፡፡

ዘገባው፡- የሰሜን ሸዋ ዞን ገቢዎች መምሪያ የግብር ትምህርትና ኮሙዩንኬሽን ዋና የስራ ሂደት ነው ሀምሌ 2018 ዓ.ም

15/07/2026
ዜና ገቢየመ/ሜዳ ከተማ አሰተዳደር ገቢዎች ፅ/ቤት በ2018 በጀት ዓመት የ12 ወር እቅድ አፈጻጸም ግምገማ ከማኔጅመንት ኮሚቴ እና ከጠቅላላ ሰራተኛው ጋር ግምገማ አደረገ፡፡የመ/ሜዳ ከተማ አ...
14/07/2026

ዜና ገቢ
የመ/ሜዳ ከተማ አሰተዳደር ገቢዎች ፅ/ቤት በ2018 በጀት ዓመት የ12 ወር እቅድ አፈጻጸም ግምገማ ከማኔጅመንት ኮሚቴ እና ከጠቅላላ ሰራተኛው ጋር ግምገማ አደረገ፡፡
የመ/ሜዳ ከተማ አሰተዳደር ገቢዎች ፅ/ቤት /ሰኔ 7/2018 ዓ.ም/
የጽ/ቤቱ ኃላፊ አቶ መለሰ በላይግዛው በማኔጅመንት የተገመገመዉን የግምገማ ውጤት በአጭሩ አቅርበዋል፡፡ በሪፖርቱ እንደተገለፀው፡- በበጀት ዓመቱ ከመደበኛ ገቢ 71928751 ከአገልግሎት ገቢ 63,494,397 በጠቅላላው 135423148 ለመሰብሰብ በእቅድ ይዞ ወደ ተግባር በመግባት በተደረገ የተቀናጀ እንቅስቃሴ ከሀምሌ1/2017 እስከ ሰኔ 30/2018 በ12ወሩ ውስጥ ከመደበኛ ገቢ 80375916.80 የእቅዱን 111.74% እንዲሁም ከአገልግሎት ገቢ 33289587.69 የእቅዱን 52.42 % በአጠቃላይ ከመደበኛና አገልግሎት ገቢ 113665504.49 የእቅዱን 83.93% መሰብሰብ ተችሏል፡፡
በ2018 በጀት አመት በ12 ወሩ የተሰበሰበው ገቢ ከ2017 በጀት አመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር መደበኛ ገቢ በ2017 የተሰበሰበው መደበኛ 48617039.95 ሲሆን በ2018 የተሰበሰበው በ2017 ከተሰበሰበው 31758876.85 ብር በብልጫ ተሰብስቧል ፣ የአገልግሎት ገቢ በ2017 የተሰበሰበ 23097454.77 ሲሆን በ2018 ከተመሳሳይ ወቅት ጋር ከተሰበሰበው 10192132.92 ብር ብልጫ ያሳያል፡፡እንዲሁም አጠቃላይ ገቢ በ2018 የተሰበሰበው ከ2017 ከተሰበሰበው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር 41951009.77 ብር በብልጫ ተሰብስቧል በማለት አቅርበዋል፡፡
በ2018 በጀት ዓመት ከባለፈው በጀት ዓመት ጋር ሲነፃፀር የተሻለ ገቢ የሰበሰብንበት ዓመት መሆኑን አስቀምጠዋል፡፡ በበጀት ዓመቱ የተከናወኑ ተግባሮችን መሰረት በማድረግ በርካታ የውይይት ሀሳቦች ተነስተዋል፡፡ በመጨረሻም ጽ/ቤት ኃላፊው ለተነሱት ሀሳቦች በርካታ ማብራሪያዎችን በመስጠት በቀጣይ በ2019 በጀት ዓመት መሰራት ያለባቸውን ዝርዝር ተግባሮች አንድ በአንድ በማንሳት ተቋሙ በ2019 ከዚህ በተሻለ ሁኔታ መፈጸም እንዳለብን ጥብቅ የስራ ስምሪት በመስጠት ውይይቱ ተጠናቋል፡፡
Facebook : https://bit.ly/4yCSBLN
Telegram : https://bit.ly/4fivr4o

"ግብራችን ለህልውናችን"
የመ/ሜዳ ከ/አስ/ገ/ፅ/ቤት ግብር ት/ት/ኮ/የስራ ሂደት

የመ/ሜዳ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ጽ/ቤት በ2018 በጀት ዓመት 113,665,504.49  ብር ገቢ ሰበሰበ።/የመ/ሜዳ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ጽ/ቤትሐምሌ 4/2018/የጽ/ቤቱ ኃላፊ አቶ መ...
11/07/2026

የመ/ሜዳ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ጽ/ቤት በ2018 በጀት ዓመት 113,665,504.49 ብር ገቢ ሰበሰበ።

/የመ/ሜዳ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ጽ/ቤትሐምሌ 4/2018/

የጽ/ቤቱ ኃላፊ አቶ መለሰ በላይ ግዛው በሰጡት ማብራሪያ በበጀት ዓመቱ:-
✍️ከመደበኛ የእቅዱን 96.1 ከአገልግሎት ገቢ የእቅዱን 52.42 የተሰበሰበ ሲሆን።
በ2018 በጀት አመት ለመሰብሰብ የታቀደው የአመቱ እቅድ:-
✍️መደበኛ እቅድ 83634946 ክንውን 80375916.8 አፈፃፀም 96.1
#. ቀጥታ ታክስ እቅድ 50353323 ክንውን 48500783.9 አፈፃፀም 96.32
#.ቀጥታ ካልሆነ ታክስ ዕቅድ 26462506 ክንውን 16079980.99 አፈፃፀም 60.76
#. ታክስ ያልሆኑ ገቢዎች እቅድ 2965129 ክንውን 1636596.1 አፈፃፀም 55.19
#. ጠቅላላ ከመደበኛ እቅድ 83634946 ክንውን 80375916.8 አፈፃፀም 96.1
✍️ አገልግሎት እቅድ 63494397 በ6ወሩ የተሰበሰበ 33289587.69 አፈፃፀም 52.42
✍️ ከመደበኛ እና ከአገልግሎት እቅድ 147,129,343 ክንውን 113,665,504.49 አፈፃፀም 77.26% መሰብሰብ መቻሉን ኃላፊው ገልፀዋል። ኃላፊውም ለዚህ አፈፃፀም አስተዋፅኦ ያበረከቱ አካላትን ምስጋና አቅርበዋል:-
1. የዞን ማኔጅመንት እና ደጋፊ ባለሙያዎች ተከታታይ እና ቀጣይነት ያለው እርስ በርስ የሚያፎካክር ግብረ መልስ ከመስጠት እና ከማበረታታቱ አልፎ የማቴሪያል ድጋፍ ማድረጋቸው።🙏🙏🙏
2. የከተማ አመራሩ ለተቋሙ ልዩ ትኩረት በመስጠት የማቴሪያል እና አስፈላጊውን ሁሉ በማሟላት ግምገማና አቅጣጫ በመስጠት ጠንካራ የክትትልና ድጋፍ ስርዓት መዘርጋቱ🙏🙏🙏
3. አጋርና ባለድርሻ አካላት ሁሉም የሚጠበቅባቸውን በመወጣትና ጽ/ቤቱን በቀናነት በማገዛቸው በተለይ የፀጥታ ተቋማት🙏🙏🙏
4. ግብር ከፋዮቻችን ግብራቸውን መከፈል ባለበት ወቅት በወቅቱ በመክፈል እና ከተለያዩ ቦታዎች ተጫርተው ለከተማቸው ልማት ገቢ በማምጣታቸው🙏🙏🙏
5. የገቢ ተቋሙ ማኔጅመንትና ባለሙያ በቅንጅት በመስራቱ እና የሚያጋጥሙ ተግዳሮቷችን በማለፍ በተቻለ መጠን ዕቅዱን ለማሳካት ያላሰለሰ ጥረት ማድረጋቸው።🙏🙏🙏
የ2018 የአመቱ አፈፃፀም በዚህ የተጠናቀቀ ሲሆን የነበረውን ቅንጅታዊ አሰራር በ2019ኝም በማስቀጠል ከዚህ በተሻለ በመሰብሰብ ህ/ሰቡ የሚያነሳውን የመልማት ጥያቄ መመለስ እንደሚገባ አቶ መለሠ አሳስበዋል።
የግትኮ ዋና የስራ ሂደት

Address

Mehal Meda
0000

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when መሐል ሜዳ ከተማ ገቢዎች ጽ/ቤት posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share