03/06/2026
በእስቴ ወረዳ እና በመካነ ኢየሱስ ከተማ አስተዳደር የጋራ የፀጥታ ምክክር መድረክ ተካሄደ፤
በደቡብ ጎንደር ዞን የእስቴ ወረዳ እና የመካነ ኢየሱስ ከተማ አስተዳደር የፀጥታ መዋቅሮች የአካባቢውን ዘላቂ ሰላምና የህብረተሰቡን ደህንነት በጋራ ለማስጠበቅ የሚያስችል የምክክር መድረክ አካሂደዋል።
በመድረኩ ላይ የተገኙት የደቡብ ጎንደር ዞን ምክትል አስተዳዳሪና የትምህርት መምሪያ ኃላፊ አቶ ደስታ አስራቴ ባስተላለፉት መልዕክት ሰላም የልማት መሰረት በመሆኑ ሁለቱ የፀጥታ መዋቅሮች በቅንጅትና በትብብር መስራት እንዳለባቸው አሳስበዋል።
አቶ ደስታ አክለውም ህብረተሰቡ ያለምንም ስጋት የዕለት ተዕለት እንቅስቃሴውን እንዲያከናውን የፀጥታ ስጋቶችን አስቀድሞ መከላከል ላይ ትኩረት ሊደረግ እንደሚገባ አጽንኦት ሰጥተዋል።
የ59ኛ ክፍለ ጦር አዛዥ ኮሎኔል አለሜ በበኩላቸው ሰላምን በዘላቂነት ለማረጋገጥ የፀጥታ መዋቅሩ ህገ-ወጥ እንቅስቃሴዎችን በቁርጠኝነት የማስቆምና የህግ የበላይነትን የማስከበር ኃላፊነቱን መወጣት እንዳለበት ገልጸዋል።
የውይይቱ ተሳታፊ የነበሩት የወረዳውና የከተማ አስተዳደሩ አመራሮችና አባላትም የተሰጣቸውን ተልዕኮ በቅንጅት መፈፀም ውጤታማ እንደሚያደርግ በመጥቀስ፤ የሚስተዋሉ ክፍተቶችን በጋራ በመሙላት የህብረተሰቡን ሰላም በዘላቂነት ለማስጠበቅ ቁርጠኛ መሆናቸውን አረጋግጠዋል።
መረጃ:- እስቴ_ኮሙኒኬሽን