20/08/2026
በሀላባ ዞን ዌራ ወረዳ ለላይ በደኔ ቀበሌ በፍርሚ አፍሪካ (Farm Africa) ፕሮጀክት አማካኝነት የጤፍ ዘር ድጋፍ ተደረገ ።
ነሃሴ 14/18 ዓ.ም
የአካባቢው አርሶ አደሮች የዘሩት የበቆሎ ሰብል በወቅታዊ የዝናብ እጥረት ምክንያት መበላሸቱን ተከትሎ ለአርሶ አደሮቹ አስፈላጊውን የጤፍ ዘር እገዛ በማቅረብ የምግብ ዋስትናቸውን ለማረጋገጥ ያለመ ነው ።
የምርትና ምርታማነት ማደግና ጥራቱን የጠበቀ ምርጥ የጤፍ ዘር ለአርሶ አደሮች ማቅረብ በሄክታር የሚገኘውን ምርት በከፍተኛ ደረጃ ይጨምራል።
ከዘር ድጋፉ ጎን ለጎን አርሶ አደሮች ዘመናዊ የዘር አዘራርና እንክብካቤ ዘዴዎችን እንዲተገብሩ ያግዛል።
ፍርሚ አፍሪካ በሀገራችን ገጠር አካባቢዎች በእርሻና ተፈጥሮ ሀብት እንክብካቤ ላይ ትኩረት አድርጎ ከሚሰራቸው ስራዎች አንዱ ይህ አይነቱ የአቅም ግንባታና የግብአት ድጋፍ ነው።