28/08/2026
ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ በክልሉ የቅድመ መደበኛ የት/ቤቶች ግንባታ በተመለከተ ለክልል ተቋማት ተልዕኮ በመስጠት ቀጣይ አቅጣጫዎች አስቀመጡ
ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ በበይነ መረብ ባደረጉት ውይይት በክልሉ በሁሉም ዞኖች የሚገነቡ የቅድመ መደበኛ ት/ቤቶች ግንባታ በተመለከተ ለክልሉ ተቋማት ተልዕኮ በመስጠት ቀጣይ አቅጣጫዎች አስቀምጠዋል።
በስብሰባው በክልሉ በፌዴራል፤ በክልሉ መንግስት እና በየደረጃው ባሉ መዋቅሮች በጣምራ የሚገነቡ የ140 የቅድመ መደበኛ ት/ቤቶች ግንባታ ፕሮጀክት አፈጻጸም ቀጣይ ተልዕኮ የተመለከተ በክልሉ ትምህርብ ቢሮ በኩል ዝርዝር ሪፖርት ቀርቦ ሰፊ ውይይት ተደርጎበታል፡፡
ርዕሰ መስተዳድሩ በዚሁ ወቅት፤ መንግስት ለማህበራዊ ብልፅግና ትልም ስኬት ቁልፍ ለሆነው ለትውልድ የትምህርት ዘርፍ ልማት ልዩ ትኩረት በመስጠት ዘርፈ ብዙ የሪፎርም ስራዎች በመስራት ላይ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
በተለይ እንደ ሀገር ያጋጠመን የትምህርት ስብራት ለመጠገን በመደረግ ላይ ባለው ጥረት በጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፤ የትምህርት ለትውልድ ንቅናቄ ህብረተሰቡን ባለቤት ባደረገ መልኩ እየተሰሩ ባሉ ስራዎች ለዘርፉ ውጤታማነት መሰረት የጣሉ ውጤቶች በመገኘት ላይ መሆኑን ገልፀዋል፡፡
የዚሁ ጥረት አካል በተለይ ለታችኛው ዕርከን የትምህርት ልማት ልዩ ትኩረት በመስጠት በአሁኑ ወቅት የ140 የቅድመ መደበኛ ት/ቤቶች ግንባታን በፌዴራል መንግስት፤ በክልሉ መንግስት እና በየደረጃው ባሉ መዋቅሮች በጣምራ ገንብቶ በማጠናቀቅ ለ2019 የት/ዘመን ዝግጁ ለማድረግ በትኩረት በመሰራት ላይ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
የቅድመ መደበኛ ት/ቤቶቹ በክልሉ በሁሉም ዞኖች የሚገነቡ መሆኑን የጠቀሱት ርዕሰ መስተዳድሩ፤ ለዚህም የቦታ ርክክብ፤ የተቋራጭ ውለታ እና ሌሎች የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን በማከናወን እና ከክረምት የበጎ ፈቃድ ስራዎች ጋር በማስተሳሰር ወደ ስራ መገባቱን ገልፀዋል፡፡
በግንባታው ረገድ እሰካሁን የ82 ት/ቤቶች ግንባታን ሙሉ በሙሉ ወደ ስራ ማስገባት መቻሉ አበረታች ነው ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ፤ ለትምህርት ቤት ግንባታዎች አስፈላጊ የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን በፍጥነት በማጠናቀቅ ባለቤት ፈጥሮ ፈጠራና ፍጥነት በተካለበት አግባብ ግንባታዎችን ማከናወን እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡
የተያዘው ግብ የትምህርት ዘመኑ ትምህረት መስከረም 5 በይፋ ሲጀመር፤ በግንባታ ላይ ያሉ ት/ቤቶችን አጠናቆ ስራ እንዲጀምሩ ማስቻል መሆኑንም ጠቅሰው፤ ለዚህ የክልል ቢሮዎችና ተጠሪ ተቋማት ከዞኖች እና ወረዳዎች ጋር ተቀናጅተው ግንባታዎችን በባለቤትነት ክትትል በማድረግ ከዳር ማድረስ የሚጠበቅባቸው መሆኑን ገልፀዋል፡፡
የት/ቤቶች ግንባታ ሲጠናቀቅም ባለድርሻ አካላትን በማስተባበር ለትምህርት ቤቶች የቁሳቁስ ድጋፍ ማድረግን ጨምሮ በማህበረሰብ ተሳትፎ የትምህረት ቤት ምገባን ለማስጀመር መስራት የሚገባ መሆኑንም በአጽንኦት ተናግረዋል፡፡
ለተያዘው ግብ ስኬት በየደረጃው ያለው አመራር በከፍተኛ ኃላፊነትና የባለቤትነት ስሜት ፕሮጀክቶቹን መከታተልና መደገፍ፣ እስከታችኛው መዋቅር ባለቤት ፈጥሮ መስራት፣ ብቃት ያለው የፕሮጀክት ክትትል በማድረግ መፈፀም እና ማስፈፀም እንደሚገባው አስገንዝበዋል።
በተጨማሪም ግንባታው ከፍተኛ አቅም እና ድጋፍ የሚፈልግ በመሆኑ የህብረተሰቡን ተሳትፎ ማጠናከር፣ የግንባታ ግባዓቶችን ባለሀብቱን አስተባብሮ አስቀድሞ ዝግጁ ማድረግ እንዲሁም ትምህርት ቤቶችን ለመማር ማስተማር ብቁ ለማድረግ አስፈላጊ የሆኑ ቁሳቁሶች ለማሟላት መስራት ቁልፍ ጉዳይ መሆኑን ገልፀዋል።
ርዕሰ መስተዳድሩ ለግንባታው ውለታ