29/04/2026
ግዙፉ ሺንግሻን ኢንዱስትሪ(Tsingshan Industry) በኢትዮጵያ በብረትና አይረን ምርት ዘርፍ ኢንቨስት ማድረግ እንደሚፈልግ ተገለፀ።
አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 21/ 2018 ዓ.ም(ኢ.ኢ.ኮ) ፦ የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር አቶ ዳጋቶ ኩምቤ ከሺንግሻን ኢንዱስትሪ (Tsingshan Industry) ልኡካን ቡድን ጋር ኩባንያው በኢትዮጵያ መዋለ ንዋዩን ማፍሰስ በሚችልበት ሁኔታ ላይ ውይይት አካሂደዋል።
በውይይቱም ምክትል ኮሚሽነር አቶ ዳጋቶ ኩምቤ ኢትዮጵያ የኢንቨስትመንት ከባቢውን ለማሻሻል ተግባራዊ እያደረገች ያለው የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ባለሃብቶች የሚያነሱትን ጥያቄ ለመፍታት እንዳስቻለ ተናግረዋል።
ምክትል ኮሚሽነሩ አክለውም መንግስት ለሺንግሻን ኢንዱስትሪ ስኬታማነት አስፈላጊ የሆኑ እንደ ኤሌክትሪክ ኃይል ያሉ መሰረተ ልማቶችን በበቂ ሁኔታ የሚያቀርብ መሆኑን ጠቅሰው የኢንቨስትመንት ኮሚሽንም ለኩባንያው አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ አረጋግጠዋል።
በኢትዮጵያ መዋዕለ ንዋይ ማፍሰስ መላው አፍሪካ ላይ እንደማፍሰስ እንደሚቆጠር የገለጹት አቶ ዳጋቶ፣ ኩባንያው በድሬዳዋ እና በገዳ የነፃ ንግድ ቀጠናዎች ጨምሮ በሌሎች አማራጮች ኢንቨስት እንዲያደርግ ጥሪ አቅርበዋል።
የኩባንያው አመራሮች በበኩላቸው በኢትዮጵያ በብረትና አይረን ምርት ዘርፍ መሰማራትና መዋዕለ ንዋያቸውን ማፍሰስ እንደሚፈልጉ በውይይቱ ወቅት ገልጸዋል።
ሺንግሻን ኢንዱስትሪ እ.ኤ.አ. በ1992 በቻይና የተመሰረተና በዓለም አቀፍ ደረጃ በብረት፣ በኒኬል እና በሊቲየም ባትሪ ምርት ቀዳሚነቱን የያዘ ግዙፍ ተቋም ሲሆን፤ በአሜሪካ፣ በቻይና፣ በኢንዶኔዥያ፣ በህንድ፣ በዚምባብዌ እና በአርጀንቲና የምርት ማዕከላት አሉት።
ኩባንያው እ.ኤ.አ በ2025 ከ60 ቢሊዮን ዶላር በላይ የሽያጭ ገቢ ማስመዝገብ የቻለ ሲሆን፤ በየዓመቱ ከ22 ሚሊዮን ቶን በላይ ብረት (stainless steel) እና 1.5 ሚሊዮን ቶን ኒኬል በማምረት በዘርፉ በስፋት እየሰራ ይገኛል።
Global Giant Tsingshan Industry Expresses Interest in Investing in Ethiopia’s Steel and Iron Sector
Addis Ababa, April 29, 2026 (EIC):
The Deputy Commissioner of the Ethiopian Investment Commission, H.E. Dagato Kumbe, held discussions with a delegation from Tsingshan Industry regarding the company’s potential investment opportunities in Ethiopia.
During the meeting, H.E. Dagato Kumbe stated that the macroeconomic reforms currently being implemented by Ethiopia to improve the investment climate have been instrumental in addressing key questions raised by investors.
The Deputy Commissioner further emphasized that the government is committed to providing essential infrastructure, such as adequate electric power, to ensure the success of Tsingshan Industry's operations. He also reaffirmed that the Investment Commission will provide all necessary support to the company.