11/05/2026
የወላይታ ሶዶ ከተማ ብልፅግና ፓርቲ በሁሉም ህብረት አባላት "ጠንካራ አደረጃጀት ለተሳካ ምርጫ" በሚል መሪ ሃሳብ ግምገማዊ የስልጠና መድረክ ተካሂዷል
ወላይታ ሶዶ፦ግንቦት 3/2018 ዓ.ም የወላይታ ሶዶ ከተማ ብልፅግና ፓርቲ በሁሉም ህብረት አባላት "ጠንካራ አደረጃጀት ለተሳካ ምርጫ" በሚል መሪ ሃሳብ ግምገማዊ የስልጠና መድረክ ተካሂዷል ።
መድረኩ 7ኛው ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ መንትያ ግቦች በማሳካት እንዲጠናቀቅ የሚያስችል መሆኑ ተገልጿል ።
"ምርጫ የዴሞክራሲ መገለጫና የህዝብ ድምጽ ማረጋገጫ መሆኑን የገለፁት የብልፅግና ህብረት አባላት ምርጫው ሰላማዊና ቅቡልነት ባለው መንገድ እንዲጠናቀቅ ከመስራት ባለፈ በፓርቲው አሸናፊነት እንዲጠናቀቅ የበኩላቸውን ድርሻ እንደሚወጡ ገልጿል ።
ፓርቲው በርካታ ስራዎችን እየሰራ እንደሆነ የገለጹት የብልፅግና ህብረት አባላት አደረጃጅቶችና አባላት የተሰሩ ስራዎችን በአግባቡ ማሳወቅ እንዳለበትም ገልጸዋል።
በከተማ ከ150 ሺህ በላይ መራጮች የምርጫ ካርድ ማውጣታቸው የህዝቡን ከፍተኛ ተሳትፎና የዴሞክራሲ ግንዛቤ የሚያሳይ መሆኑን ገልጸዋል።
በከተማ በሁሉም አካባቢዎች በተካሄዱ የምርጫ ቅስቀሳና የድጋፍ ሰልፎች የታየው ህዝባዊ ተሳትፎም ህብረተሰቡ ለፓርቲያችን ያለውን አለኝታነት በተግባር ያረጋገጠ መሆኑን ገልጸዋል።
በምርጫ ቅስቀሳው ወቅት የታየው ህዝባዊ ተሳትፎ ከምርጫው ሂደት እስከ ድህረ ምርጫው ድረስ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪ አቅርበዋል።
ጠንካራ አደረጃጅት ጠንካራ ፓርቲ፣ ጠንካራ መንግስትና ሀገረ መንግስት ለመገንባት ፋይዳው ጉልህ መሆኑን የገለፁት የብልፅግና ህብረት አባላት ለ7ኛው ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫ ምቹ አውድ በመፍጠር ሰላማዊና ዲሞክራሲያዊ ምርጫ አካሒዶ ምረጫውን በአሸናፊነት ለማጠናቀቅ አደረጃጅቶች ሚናቸውን መወጣት እንዳለባቸውም ገልጸዋል።
ብልጽግና ፓርቲ በከተማችን ፣ በክልላችንና እንደ ሀገር በርካታ ስራዎችን እየሰራ ያለ ፓርቲ መሆኑንም አንስተዋል።