Wolaita Sodo City Land Administration Department ዎላይታ ሶዶ ከተማ መሬት አስተዳደር መምሪ

  • Home
  • Ethiopia
  • Sodo
  • Wolaita Sodo City Land Administration Department ዎላይታ ሶዶ ከተማ መሬት አስተዳደር መምሪ

Wolaita Sodo City Land Administration Department ዎላይታ ሶዶ ከተማ መሬት አስተዳደር መምሪ _Build_Vibrant_&_Digital_City!! Striving to Build Vibrant Digital City

የወላይታ ምድር ንጋት ያለ ጊፋታ እሳት አይሞቅም፤ የጊፋታ እሳትም ያለ  #ዱንጉዛ ማዕረግ አይደምቅም። ወላይታ ሶዶ ፦መስከረም 02/2019ዓ.ምጊፋታና ዱንጉዛ የአንድ ጥንታዊ ሥልጣኔ ሁለት ቅ...
12/09/2026

የወላይታ ምድር ንጋት ያለ ጊፋታ እሳት አይሞቅም፤ የጊፋታ እሳትም ያለ #ዱንጉዛ ማዕረግ አይደምቅም።

ወላይታ ሶዶ ፦መስከረም 02/2019ዓ.ም

ጊፋታና ዱንጉዛ የአንድ ጥንታዊ ሥልጣኔ ሁለት ቅዱስ ገጾች ናቸው። አንዱ የአዲስ ዘመን ማብሰሪያ የዘመን መለወጫ አዋጅ ሲሆን፣ ሌላኛው ደግሞ ያንን አዋጅ በክብር የሚያሸልም የክሮች ወርቃማ ምስጢር ነው።ይህ ታሪካዊና ባህላዊ ቁርኝት ትውልድን ከተውልድ እያገናኘ ዘመናትን የተሻገረ የሕይወት ድልድይ ነው።

በዓሉ በዓለም አቀፍ ደረጃ በዩኔስኮ (UNESCO) በማይዳሰስ የሰው ልጅ ቅርስነት ሲመዘገብ፣ የዱንጉዛ ልብስ ዋነኛ እና የማይነጠል የጊፋታ እሴት ተደርጎ መወሰዱ ለዚህ ጥበባዊ ቁርኝት ሕያው ምስክር ነው።

በጊፋታ አደባባይ ዱንጉዛን መልበስ እንዲሁ ጨርቅን መጣጣል አይደለም፤ የማንነትን ታላቅነት በሰውነት ላይ መሳል እንጂ! በዓሉን የሚታደሙት ንጉሡ (ካዎ) እና ሹማምንቱ፣ ምድሪቱንና ሕዝቡን በምረቃ የሚያጠቡ "ጨራቻማ" የተባሉ የአገር ሽማግሌዎች፣ አንቱታን ያተረፉ የጎሳ መሪዎችና ሁዱጋዎች ይህንን የዱንጉዛ ሐዴ ለብሰው አደባባይ ሲወጡ፣ አየሩ ሁሉ በጥጥ ሽታና በክብር መዓዛ ይሞላል።

ይህ ትዕይንት የወላይታን ጥንታዊ ማንነት ለዓለም በኩራት የሚመሰክር ሕያው ታሪክ ነው።

የፈትል ምስጢር፡ ዱንጉዛ ለምን ቀደመ?

የወላይታ ማኅበረሰብ "ፑቷ" (ጥጥ)ን ከማልማት ጀምሮ፣ በጥረት ፈትሎ (ሱቅ ድልእድ) አልባሳትን የማዘጋጀት የረጅም ዘመናት የዕደ-ጥበብ ታሪክ አለው።

ከእነዚህ በጥበብ ከሚሸመኑ ደማቅ የቀለማት ውህደትና ምስጢራዊ የክር መስመሮች መካከል "ሐዴ" (Hadee) የጥበብ ሁሉ መደምደሚያ ተደርጎ ይወሰዳል።

በወላይታ አምስት የሐዴ ዓይነቶች አሉ፤ እነሱም፦ ዱንጉዛ፣ ሴሪያ፣ ጉቱማ፣ ፓታላ እና ጎማራ በመባል ይታወቃሉ።

ከእነኚህ ሁሉ ግን ዱንጉዛ ሐዴ ዘውድ ጭኖ ይቀድማል። ታሪክ አዋቂዎች እንደሚመሰክሩት፣ ዱንጉዛ ሕዝቡ ከተፈጥሮ ሀብቱ ማህፀን አውጥቶ የራሱን ስልጣኔ የገነባበት የጥንታዊ ዕደ-ጥበብና የኢንዱስትሪ ማሳያ በመሆኑ የሐዴዎች ሁሉ መጀመሪያና መሪ ሊሆን ችሏል።

👉የሥልጣንና የክብር ቋንቋ

በቀደምት የወላይታ መንግሥታት ዘመን ዱንጉዛ ሐዴ የለበሰ ሰው ዝም ቢልም ልብሱ ይናገራል። ልብሱ በንጉሥ (ካዎ)፣ በጦር መሪዎችና በአገር ሽማግሌዎች ዘንድ የክብርና የስልጣን መግለጫ ተደርጎ ይለበስ ነበር።

ጨርቁ ላይ የሚቀመጡት ነጠብጣቦችና የመስመር ቅርጾች እንዲሁ የተሰመሩ ሳይሆኑ፣ የማኅበረሰቡን ደረጃና የባለቤቱን ማዕረግ የሚያመላክቱ ጥንታዊ የክብር ምልክቶች ናቸው።

👉የቀለማቱ ስውር ምስጢር

የአገር ሽማግሌዎችና የባህል አጥኚዎች በትውልድ ቅብብሎሽ ባስተላለፉት ምስክርነት መሠረት፣ በዱንጉዛ አልባሳት ላይ የፈሰሱት ቀለማት እያንዳንዳቸው የራሳቸው ጥልቅ ትርጉም አላቸው፦

🔴 ቀይ፦ መስዋዕትነትንና የጀግንነትን ዋጋ ያመለክታል።

⚫ ጥቁር፦ የጽናትን፣ የጥንካሬንና የመጽናናትን ኃይል ይገልጻል።

🟡 ቢጫ፦ የተስፋን ብርሃን፣ የሰላምን አየርና የተፈጥሮን በረከት ያንጸባርቃል።

የእነዚህ ሦስት ቀለማት ውህደት ከሩቁ ጎልቶ በሚታይ፣ ሆኖም በስውርና ቀጫጭን መስመሮች ተውቦ የሚሠራ በመሆኑ፤ ነገሥታት፣ የጦር መሪዎችና ታላላቅ የአገር ሽማግሌዎች መርጠው የሚለብሱት ሆነ።

ይህ መመረጥ ዱንጉዛን ከሐዴዎች ሁሉ ይበልጥ ተወዳጅና የተከበረ አድርጎታል።

👉ከዳሞታ መንግሥት እስከ ዘመናዊው የፋሽን አደባባይ

የዱንጉዛ ሐዴ እውቅና የዛሬ የትላንት እሸት አይደለም፤ ከሺህ ዓመታት በፊት የነበረ እንጂ።

በተለይም ከዳሞታ መንግሥት ዘመን ጀምሮ የወላይታ ባህላዊ አልባሳት በምሥራቁ ዓለም አገራት ዘንድ የታወቁና የሚፈለጉ ነበሩ።

የምስል መረጃዎች መያዝ ከተጀመረበት ጊዜ አንስቶ ደግሞ የብሔሩ ዋነኛ መጠሪያ ሆኖ እስከ ዛሬ ዘልቋል።

በዘመናችን ደግሞ የኪነ-ጥበብ ሰዎች በሙዚቃና በውዝዋዜ ባደረጉት ታላቅ ተጋድሎ፣ የዱንጉዛ ልብስና የወላይታ ውብ ጭፈራ በዓለም አገራት የቴሌቪዥን መስኮቶች ላይ የውበት ማዕበል ፈጥረዋል።

ከዚህም ባለፈ፣ የዱንጉዛን የልብስ ጥበብና የሕብር ቀለማት ከዘመናዊ አልባሳት ጋር በማቀናጀት በዓለም አቀፍ የፋሽን ትርዒቶች (Fashion Shows) ላይ የሚያቀርቡ የብሔሩ ተወላጅ ዲዛይነሮች፣ ዱንጉዛን በኩራት መርጠው በማቅረብ ልብሱ የወላይታ ብሔራዊና ዓለም አቀፋዊ አርማ እንዲሆን አስችለውታል።

ዱንጉዛ ሐዴ የራሱ የሆነ ልዩ የሕብር ቀለማት ውህደት፣ የቀይ፣ ጥቁር፣ ቢጫ መስመሮችና የነጠብጣብ ጥበብ አሠራር ያለው በመሆኑ፤ በሌሎች የኢትዮጵያም ሆነ የዓለም አገራት ከሚሠሩ ባህላዊ ጨርቆች ሙሉ በሙሉ የተለየና በሩቅ የሚለይ የውበት ማኅተም ነው።

በምክክር የፀናችው ኢትዮጵያ የአዲሱ ዓመት የሰላም፣ የአንድነትና የብልፅግና አዲስ ምዕራፍ*****************ትላንት የጀመርነው አዲስ ዓመት እና አዲስ ቀን ነገ የምንሰጠውን ታሪክ የሚ...
12/09/2026

በምክክር የፀናችው ኢትዮጵያ የአዲሱ ዓመት የሰላም፣ የአንድነትና የብልፅግና አዲስ ምዕራፍ
*****************

ትላንት የጀመርነው አዲስ ዓመት እና አዲስ ቀን ነገ የምንሰጠውን ታሪክ የሚወስን አዲስ ዕድል በሚፈጥርበት ታሪካዊ ወቅት ላይ እንገኛለን።

ኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት ያስተናገደቻቸውን ፖለቲካዊና ማህበራዊ ውጥረት የሞሉባቸውን ምዕራፎች በዘላቂነት ለመሻገር የታሪክ፣ የሐሳብ እና የፍላጎት ልዩነቶችን ወደ አንድ ጠረጴዛ በማምጣት በታሪኳ ለመጀመሪያ ጊዜ ልዩነቶቿን በሰለጠነ መንገድ ለመፍታት ያስቻላትን ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ በስኬት ያጠናቀቀችበት ዓመት ነበር።

ይህ በስኬት የተጠናቀቀው ሀገራዊ ምክክር ከአንድ ጉባኤ ማብቃት በላይ የኢትዮጵያን ፅናት፣ የልጆቿን ጥበብ እና የራሷን ዕጣ ፈንታ በራሷ የመወሰን ብስለት ያረጋገጠ ታሪካዊ ክስተት ነው።

ኢትዮጵያውያን በታሪካቸው የውጭ ወራሪዎችን በመመከት ለጥቁር ሕዝቦች የነፃነት ምልክት እንደሆኑ ሁሉ፣ ዛሬም ውስብስብ የሆኑ ፖለቲካዊና ማህበራዊ ውዝግቦችን በጠመንጃ አፈሙዝ ከመፍታት ይልቅ በሰለጠነ ውይይት በመደማመጥና በመግባባት መፍታት እንደሚችሉ ለአለም አስመስክረዋል።

ሂደቱም የፖለቲካ ኃይሎችን፣ ተቋማትን፣ ሠራተኞችን፣ ዳያስፖራዎችን እና የማህበረሰብ ክፍሎችና መሪዎችን ያሳተፈ፣ ግልፅነት ያለው እና ሕብረ ብሔራዊ አንድነትን ያጎለበተ በመሆኑ ሕዝቡ ሂደቱን በባለቤትነት ስሜት እንዲመራው አድርጓል።

"የፖለቲካ ነፃነት ወደ ውይይት፣ ውይይት ደግሞ ወደ ሕግ የበላይነት ያድጋል" እንደሚባለው የፖለቲካ ነፃነት የፈጠረውን ምቹ ሁኔታ ወደ ፍሬያማ ውይይት በመቀየር ረገድ ምክክሩ ትልቅ ታሪካዊ ኃላፊነት ተወጥቷል።

ውይይት የዜጎችን ድምፅ በማንፀባረቅና የጋራ ጥቅምን በማስቀደም ለሕጎች፣ ለፖሊሲዎችና ለሕገ መንግስታዊ ማሻሻያዎች መሠረት በመሆን ጠንካራ ተቋማትና የሕግ የበላይነት የነገሰባትን ሀገር ለመገንባት መሠረት ጥሏል።

በዚህ አዲስ ዓመት የምክክሩ ስኬት ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ እምርታን ይዞ መጥቷል። የሀገር ሀብትና ዕውቀት ወደ ምርታማነት፣ ኢንቨስትመንት፣ ቴክኖሎጂ፣ ትምህርት፣ ጤና እና መሠረተ ልማት እንዲዞር ምቹ ሁኔታዎች ተፈጥረዋል።

ይህም የዜጎችን የሥራ ዕድል የሚያሰፋና የሀገር ልማትን የሚያፋጥን ሲሆን፣ ኢትዮጵያ በምሥራቅ አፍሪካ ያላትን የዲፕሎማሲና የኢኮኖሚ አቅም በመጠቀም በቀጠናዊ መረጋጋት ላይ ንቁና መሪ ሚናዋን እንድትወጣ ያስችላታል።

አደይ አበባ የሚያምረው ብዙ አበቦች በአንድ ሜዳ ላይ በጋራ ሲያብቡ እንደሚሆነው ሁሉ፣ ኢትዮጵያም በልዩነቷ ስትተባበር ውበቷና ጥንካሬዋ ይገለጣል።

ከምክክሩ የተገኙ መግባባቶችን ወደ ተጨባጭ ተግባር በመቀየር የሚጎዱንን አሮጌ አስተሳሰቦች ወደ ጎን ትተን በጠቃሚ አዳዲስ እሴቶች በመተካት የጋራ ብልፅግናችንን ማረጋገጥ ይጠበቅብናል።

የአዲስ ዘመንን በተስፋ በመቀበል፣ በምክክር የተገኘውን ድል በማስቀጠል፣ በመተባበርና በጋራ በመሆን በሌሎች ሀገራዊ ተግባራት ላይም የራሳችንን አሻራ በማሳረፍ የነገዋን ውብ ኢትዮጵያ በመገንባት በጋራ ልንጓዝ ይገባል።

በብሌን ደምበሎ

የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መልዕክት"በብሪክስ ፕላስ የቤተሰብ መድረክ ማዕቀፍ ውስጥ፣ ከኢራኑ ፕሬዚዳንት መስዑድ ፔዜሽኪያን ጋር ተወያይተናል። ‎‎ከጉባኤው ጎን ለጎን ባደረግነ...
12/09/2026

የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መልዕክት

"በብሪክስ ፕላስ የቤተሰብ መድረክ ማዕቀፍ ውስጥ፣ ከኢራኑ ፕሬዚዳንት መስዑድ ፔዜሽኪያን ጋር ተወያይተናል።

‎ከጉባኤው ጎን ለጎን ባደረግነው ውይይት በቀይ ባሕር አካባቢ ባሉ ወቅታዊ ሁነቶች እና አጠቃላይ በቀጣናው የደኅንነት ሁኔታ ላይ ያተኮረ ሲሆን፣ የውይይትን አስፈላጊነት እና የቀጣናውን መረጋጋት እውን ማድረግ በሚቻልባቸው ጉዳዮች ዙሪያም መክረናል።"

🇪🇹 🇮🇷

የፖሊሲ ጉዳይ ቅኝት - መስከረም 2፣ 2019ዓ.ም
12/09/2026

የፖሊሲ ጉዳይ ቅኝት - መስከረም 2፣ 2019ዓ.ም

12/09/2026

#የጊፋታን #ጊፋታ #የትውልድ

 #ጊፋታ - ከወላይታ ምድር እስከ ዓለም የባህል መድረክ!! #የትውልድ ቅርስን እንጠብቅ፣  #የጊፋታን ውርስ እናስቀጥል!”የአንድ ሕዝብ ታሪክ፣ ባህል፣ እሴት እና ማንነት በመጻሕፍት ብቻ አይ...
12/09/2026

#ጊፋታ - ከወላይታ ምድር እስከ ዓለም የባህል መድረክ!!

#የትውልድ ቅርስን እንጠብቅ፣ #የጊፋታን ውርስ እናስቀጥል!”

የአንድ ሕዝብ ታሪክ፣ ባህል፣ እሴት እና ማንነት በመጻሕፍት ብቻ አይቀመጥም። በትውልድ ተሻግረው በሚመጡ ልማዶች፣ በበዓላት፣ በሙዚቃና ውዝዋዜ፣ በምግብና መጠጥ፣ በባህላዊ አለባበስ፣ በአባቶች ምክርና በማኅበራዊ ግንኙነት ውስጥ ይኖራል። የወላይታ ብሔር ዘመን መለወጫ በዓል ጊፋታ ደግሞ ከእነዚህ የባህል መገለጫዎች ሁሉ የላቀ ትርጉም ያለው፣ የሕዝቡን ታሪክና ማንነት በሕያው መልኩ የሚያስተላልፍ ታላቅ ባህላዊ በዓል ነው።

ጊፋታ የወላይታ ሕዝብ አዲስ ዓመትን የሚቀበልበት በዓል ሲሆን፣ በወላይታ ማኅበረሰብ ዘንድ ከመስከረም አጋማሽ እስከ ጥቅምት መጀመሪያ ባለው ጊዜ ይከበራል። በዓሉ አንድ ቀን ብቻ የሚዘከር ሥነ-ሥርዓት ሳይሆን ለቀናት የሚቀጥል ሰፊ ማኅበራዊና ባህላዊ ሂደት ነው። ይህም ጊፋታ የዘመን መለወጫ ብቻ ሳይሆን የሰላም፣ የይቅርታ፣ የአንድነት እና የእርቅ በዓል መሆኑን ያሳያል። የተጣሉ ሰዎች ይታረቃሉ፤ ቤተሰቦች ይሰበሰባሉ፤ ወጣቶችና አዛውንቶች በአንድ መድረክ ይገናኛሉ። በዚህ ሂደት የአዛውንቶች ሚና ልዩ ነው። አዛውንቶች ግጭትን በመፍታት፣ ምክር በመለገስ እና ቡራኬን በመስጠት ለማኅበረሰቡ መሪ የሆነ ሚና ይጫወታሉ።

የጊፋታ ዋና ዕለት ደግሞ የቤተሰብና የማኅበረሰብ መተሳሰብ በግልጽ የሚገለጽበት ጊዜ ነው። ቤተሰቦች ይሰበሰባሉ፣ ባህላዊ ምግብና መጠጥ ይዘጋጃል፣ ከዚያም ከአዛውንቶች በረከት ይቀበላሉ። በማታ ደግሞ ማኅበረሰቡ በእሳት ዙሪያ በመሰብሰብ ሥነ-ሥርዓት፣ ዝማሬና ውዝዋዜ ያከናውናል። ለቀናት የቆየው የበዓሉ ዝግጅት በ‘ጎሎ-ኢጌታ’ በተባለው ታላቅ የማኅበረሰብ ደስታ ይደመደማል፤ በዚህም የፈረስ ጉግስ፣ ሙዚቃ፣ የሕዝብ ደስታና የአዛውንቶች የመጨረሻ በረከት ይካተታል።

ጊፋታ በተለይ የሚያስደንቀው ከትውልድ ወደ ትውልድ የሚተላለፈው የእውቀትና የባህል ሀብት መሆኑ ነው። ሴት ልጆች ከእናቶቻቸው ጋር ባህላዊ ምግብና መጠጥ በማዘጋጀትና ቤትን በማስዋብ ይሳተፋሉ፤ ወንድ ልጆች ደግሞ ከአባቶቻቸው ጋር የማገዶ እንጨት በመሰብሰብ፣ የበዓሉን እሳት በማዘጋጀት እና ቤት በመጠገን ይሳተፋሉ። በዚህ መልኩ ጊፋታ የባህል ማስተላለፊያ ትምህርት ቤትም ነው።

ጊፋታ በዩኔስኮ መመዝገቡ የታሪካዊ ዕውቅና ምልክት
በወላይታ ሕዝብ ብቻ ሳይሆን በመላው ኢትዮጵያ በኩራት ሊከበር የሚገባው ታላቅ ስኬት ጊፋታ በዩኔስኮ የሰው ልጅ የማይዳሰስ ባህላዊ ቅርስ ተወካይ ዝርዝር ላይ መመዝገቡ ነው። ዩኔስኮ በ2025 በ20ኛው የማይዳሰስ ባህላዊ ቅርስ የመንግሥታት ኮሚቴ ውሳኔ ጊፋታን በ“Gifaataa, Wolaita people New Year festival” በሚል ስያሜ በዓለም የሰው ልጅ የማይዳሰስ ባህላዊ ቅርስ ተወካይ ዝርዝር ላይ አስገብቷል።

ዩኔስኮ በምዝገባው ውስጥ ጊፋታ ሰላምን፣ ማኅበራዊ ትስስርን፣ ትውልድ ተሻጋሪ ግንኙነትን፣ አንድነትን እና መተባበርን እንደሚያጎለብት አስተውሏል። በተጨማሪም ባህሉ ለምግብ ዋስትና፣ ለአካባቢ ጥበቃ እና ለአካባቢያዊ ኢኮኖሚ የራሱን አስተዋጽኦ እንዳለው የዩኔስኮ ውሳኔ ያሳያል።

ለኢትዮጵያ ቱሪዝም የሚኖረው ፋይዳ
ጊፋታ በዩኔስኮ መመዝገቡ በወላይታ ብቻ የሚገደብ ውጤት አይደለም፤ ለኢትዮጵያ የቱሪዝም ዘርፍ አዲስ የማስተዋወቂያ አቅም የሚፈጥር ታላቅ እድል ነው። ኢትዮጵያ በታሪኳ፣ በተፈጥሯዊ ሀብቷ፣ በብሔረሰቦቿ ባህልና ቋንቋ፣ በሃይማኖታዊ ቅርሶቿና በልዩ የማኅበረሰብ አኗኗር የበለጸገች አገር ናት። ጊፋታ ደግሞ ይህን ባለብዙ ገጽታ የቱሪዝም ሀብት ለዓለም ለማሳየት የሚችል አዲስ መስኮት ነው

የመደመር አንቀጽበአዲሱ ዘመን ዕሳቤ ከተሞች ለመኖሪያ ምቹ፣ ለንግድ ማሣለጫ፣ ለፈጠራና ለቢዝነስ መጀመሪያና መጎልበቻ፣ ለቱሪስት መዳረሻ ሆነው እንዲቆረቆሩ ማድረግ ያስፈልጋል። እንዲሁም ከአም...
12/09/2026

የመደመር አንቀጽ

በአዲሱ ዘመን ዕሳቤ ከተሞች ለመኖሪያ ምቹ፣ ለንግድ ማሣለጫ፣ ለፈጠራና ለቢዝነስ መጀመሪያና መጎልበቻ፣ ለቱሪስት መዳረሻ ሆነው እንዲቆረቆሩ ማድረግ ያስፈልጋል።

እንዲሁም ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር የተሣሠሩና ገጠሩን ከከተማው በማቀናጀት የኢኮኖሚ መዋቅራዊ ሽግግር ለማፋጠን አስቻይ እንዲሆኑ ሊሠራ ይገባል።

ለዚህም አዲስ አበባና ሌሎች መካከለኛና አነስተኛ ከተሞችን የመሠረተ ልማት ችግሮቻቸውን መፍታት ይገባል። ያሉባቸውን የዕቅድና የአስተዳደር ፈተናዎች ማቃለል ያስፈልጋል።

የመጪውን ጊዜ ተግዳሮቶች ለመፍታትና ለመሻገር ደግሞ የላቀ ሐሳብ፣ ፈጠራና ፍጥነት ያለው ሥራ ይጠይቃል።

የመደመር መንግስት
ገጽ 234

ታሪካችንን በራሳችን ብዕር፡ የኢትዮጵያ የድልና የተስፋ አዲስ ዓመት(የዕለቱ መልዕክት)*******************የኢትዮጵያ አዲስ ዓመት ተፈጥሮ ራሷን የምታድስበት፣ የደፈረሱ ወንዞች የሚጠ...
12/09/2026

ታሪካችንን በራሳችን ብዕር፡ የኢትዮጵያ የድልና የተስፋ አዲስ ዓመት
(የዕለቱ መልዕክት)
*******************

የኢትዮጵያ አዲስ ዓመት ተፈጥሮ ራሷን የምታድስበት፣ የደፈረሱ ወንዞች የሚጠሩበት፣ ምድሪቱ በአደይ አበባ የምታጌጥበትና የመስቀል ወፎች ብቅ የሚሉበት ልዩ ወቅት ነው።

ይህ የተፈጥሮ ዑደት ለሀገራችን የብሩህ ተስፋና የአዲስ ምዕራፍ መጀመሪያ ተደርጎ ይወሰዳል።

አዲሱ ዓመት ከምንጊዜውም በተለየ ሁኔታ ፈተናችንን ከኋላ ትተን፣ ተስፋችንን ከፊት በማስቀደም ፊታችንን ወደ ኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ብልጽግና የምናዞርበት ታሪካዊ አጋጣሚ ነው።

እየተከናወኑ ያሉ ሰፋፊ የልማት ሥራዎች በተለይም የኮሪደር ልማቱን ጨምሮ የተጀመሩ ትላልቅ ፕሮጀክቶች ሀገራዊ ራዕይን እውን የማድረግ ማሳያዎች ናቸው።

"የምንሠራው ለዛሬ ብቻ ሳይሆን ለነገ እና ለቀጣዩ ትውልድ ነው በሚል መርህ፣ ለትውልድ የሚሻገር ዘላቂ ሥራ እየተሠራ ይገኛል።

ኢትዮጵያ ብልጽግናዋንና ድሎቿን ለመጻፍ ስትነሳ መጻፊያ ብዕሯ ዜጎቿ ሲሆኑ፣ ቀለሙም ከእያንዳንዱ የላብና የትጋት ውጤት የሚቀዳ ነው።

ኢትዮጵያ ፈተናን ወደ ዕድል በመቀየር ታሪክ ከሚያነሣቸው ሀገራት ተርታ ለመሰለፍ የሚያስችል በቂ አቅምም ሆነ ጽኑ አቋም አላት፤ ለዘመናት ያቆየችው የነጻነት ታሪክም የዚሁ ማሳያ ነው።

አዲሱ ዓመት ኅብረ ብሔራዊ አንድነታችን ይበልጥ የሚጸናበትና ዴሞክራሲያዊ ዕሴቶቻችን ሥር ሰደው የሚጎለብቱበት እንዲሆን እያንዳንዳችን የድርሻችንን መወጣት ይጠበቅብናል።

በሀገር ፍቅር የታነጸ፣ አካባቢያዊ ማንነቱን ከሀገራዊ ማንነቱ ጋር አዋሕዶ የያዘ፣ ለፈጠራ የተጋለጠና ያልተሄደበትን መንገድ ለመጓዝ ድፍረት ያለው ትውልድ መፍጠር የዘመኑ ግዴታ ነው።

አዲስ ዓመት አዲስ ተስፋን ይዞ የሚመጣው፣ እኛ ራሳችንን ለለውጥ ባዘጋጀንበት ልክ ብቻ ነው።

በሀገር ጉዳይ ላይ ጣት ከመጠቆም ይልቅ፣ “ከእኔ ምን ይጠበቃል?” የሚለውን ጥያቄ በማስቀደም ለጋራ ራዕይ መትጋት ይኖርብናል።

የሚጎዱንን አሮጌ አስተሳሰቦች ወደ ጎን ትተን፣ ጠቃሚ በሆኑ አዳዲስ ዕሴቶች መተካት የመጻኢው ጉዟችን መሠረት ነው።

ጊዜው ለሁሉም ባዶ ሆኖ የቀረበ አዲስ የዘመን መጽሐፍ ገልጦልናል። የዚህ መጽሐፍ ዋና ጸሐፊዎች እኛው ራሳችን ነን። እኛ ዝም ብንል ሌሎች በፈለጉት መንገድ ሊጽፉት እንደሚችሉ መገንዘብ ያሻል።

ይሁንና የራሳችንን የዘመን አቆጣጠር የፈጠርን ሕዝቦች፣ የራሳችንን ዕጣ ፈንታ በገዛ እጃችን ከመጻፍ የሚያግደን ምንም ዓይነት ኃይል የለም።

እኛው አቅደን፣ እኛው ሠርተን፣ ችግሮቻችንን በውይይትና በምክክር ፈትተን የራሳችንን ጉዳይ በራሳችን የመወሰን ባህል መለማመድ ጀምረናል፤ አቅሙም እንዳለን አሳይተናል።

ዘመኑ የኢትዮጵያውያንና የአዲሲቱ ኢትዮጵያ ነው። ዜጎች ልዩነታቸውን ጠብቀው በጋራ ጉዳዮች ላይ በአንድነት ሲቆሙና እርስ በርስ ሲደጋገፉ፣ የሀገራችን የብልጽግና ብዕር የላቀ አሸናፊነትን፣ ታላቅነትንና አንጸባራቂ ድልን አድምቆ ይጽፋል።

የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል

18ኛው የብሪክስ መሪዎች ጉባኤ በኒው ዴልሂ ይካሄዳል **********************በሕንድ አስተናጋጅነት በኒው ዴልሂ "ባራት ማንዳፓም" የሚካሄደው 18ኛው የብሪክስ የመሪዎች ጉባኤ፣ የ...
12/09/2026

18ኛው የብሪክስ መሪዎች ጉባኤ በኒው ዴልሂ ይካሄዳል
**********************

በሕንድ አስተናጋጅነት በኒው ዴልሂ "ባራት ማንዳፓም" የሚካሄደው 18ኛው የብሪክስ የመሪዎች ጉባኤ፣ የዓለም አቀፉን የጂኦፖለቲካ የኃይል ሚዛን ወደ አዲስ ምዕራፍ የሚያሸጋግር ታሪካዊ ክስተት ሆኖ ተጀምሯል።

በሕንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ ሰብሳቢነት "ዘላቂነትን፣ ፈጠራን፣ ትብብርን እና ጥንካሬን መገንባት" በሚል መሪ ቃል በሚካሄደው በዚህ ጉባኤ ላይ የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፣ የቻይናው ፕሬዝዳንት ሺጂንፒንግ፣ የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቪላዲሚር ፑቲን፣ የኢራኑ ፕሬዝዳንት ማሱድ ፔዜሽኪያን እና የደቡብ አፍሪካው ፕሬዝዳንት ሲሪል ራማፎሳን ጨምሮ በርካታ የዓለም መሪዎችና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ይሳተፋሉ።

ሕንድ ከአውሮፓውያኑ ጥር 1 ቀን 2026 የብሪክስ ሊቀመንበርነቱን ከተረከበች በኋላ ትኩረቷን ጥንካሬና መቋቋም፣ ፈጠራና ቴክኖሎጂ፣ ትብብርና የግሎባል ሳውዝ ድምፅ እንዲሁም ዘላቂነት በተባሉ 4 ዋና ዋና አዕማድ ላይ አድርጋለች።

በጉባኤው ላይ የዶላር የበላይነት ጉዳይ፣ የኢራን እና አሜሪካ ውጥረት እንዲሁም የሕንድ እና ቻይና የሁለትዮሽ ግንኙነት በዋና አጀንዳነት ይወያዩባቸዋል።

በአዲሱ ልማት ባንክ በኩል ከሚፈቀዱ ፋይናንሶች ውስጥ ከ43.5% በላይ የሚሆነው በሀገር ውስጥ ገንዘቦች የሚሸፈን ሲሆን፣ ይህም ከተለምዷዊው አሰራር የተለየ እና ስትራቴጂካዊ እርምጃ ነው።

ኢትዮጵያ፣ ብራዚል፣ ቻይና፣ ግብፅ፣ ሕንድ፣ ኢንዶኔዢያ፣ ኢራን፣ ሩሲያ፣ ሳውዲ አረቢያ፣ ደቡብ አፍሪካ እና የተባበሩት አረብ ኤምሬትስን ያቀፈው ይህ ስብስብ በአሁኑ ወቅት የዓለምን 49.5% ሕዝብ፣ የዓለም አቀፉን ጠቅላላ ሀገራዊ ምርት 40% እና የዓለም አቀፍ ንግድ 26% ድርሻ በመሸፈን የዓለምን ኢኮኖሚያዊ የኃይል ሚዛን ወደ ባለብዙ ማዕከልነት እየቀየረ ይገኛል።

በሰለሞን ገዳ

Address

Frew Altaye Avenue
S**o

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Wolaita Sodo City Land Administration Department ዎላይታ ሶዶ ከተማ መሬት አስተዳደር መምሪ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share