የደሃና ወረዳ የአካባቢና የደን ጥበቃ ጽ/ቤት/Dehana woreda Enviroment and forest protection

  • Home
  • Ethiopia
  • Sokota
  • የደሃና ወረዳ የአካባቢና የደን ጥበቃ ጽ/ቤት/Dehana woreda Enviroment and forest protection

የደሃና ወረዳ የአካባቢና የደን ጥበቃ ጽ/ቤት/Dehana woreda Enviroment and forest protection የአካባቢና የደን ጥበቃ ጽ/ቤት የደንበኞች የፌስቡክ ድረ ገጽ ላይክና ሼር በማድረግ መረጃዎች ያጋ

አደገኛ መጤ አረም ምንድን ነው?አደገኛና መጤ አረም ማለት በተፈጥሮ ባልነበሩበት /ባልኖሩበት/ ሥፍራ በከፍተኛ ደረጃ በመስፋፋት ነባር ዝርያን የሚፈታተኑ ዝርያዎች ማለት ነዉ፡፡ ይኸዉም በቀጥ...
16/08/2026

አደገኛ መጤ አረም ምንድን ነው?

አደገኛና መጤ አረም ማለት በተፈጥሮ ባልነበሩበት /ባልኖሩበት/ ሥፍራ በከፍተኛ ደረጃ በመስፋፋት ነባር ዝርያን የሚፈታተኑ ዝርያዎች ማለት ነዉ፡፡ ይኸዉም በቀጥታ በመሻማት፤ በሽታ አስተላላፊ ወይም ጥገኛ በመሆንና የነባር ዝርያዎችን ሥነ-ምህዳር በመለወጥ እሰከ መጨረሻዉ እንዲጠፉ በማድረግ አካባቢዉ ይሰጥ የነበረዉን አገልግሎት እንዲቋረጥ በማድረግ ነው፡፡ አደገኛ የሆኑ በመሬትና ውሃ አካላት ላይ ተስፋፊ እፅዋት ሆነው ከትናንሽ የውሃ ላይ ተንሳፋፊ እስከ ትላልቅ ዛፍ የሚያካትት ነው፡፡
አደገኛና መጤ አረሞች በብዙ አካባቢዎች በሰው ጤና ፣ በግብርና ሥራዎች ፣ በመዝናኛ ቦታዎች ፣ በዱር እንስሳት ፣ በደኖች ወዘተ ላይ ጉዳት የሚያስከትሉ ተብለው የተለዩ አረሞች ማለት ነው፡፡
በክልል ደረጃ አንድ አረም አንድ ጊዜ በአደገኛ አረምነት ከተለየ በኋላ የሚመለከተው የተቆጣጣሪ መ/ቤት ባለስልጣን አረሙ ከቦታ ቦታ እንዳይዛመት የውስጥና የውጭ ቁጥጥር ተግባራትን በአረሙ ላይ ይፈፅማል፡፡ አረሙን ለመቀነስ ወይም ለማጥፋት የተለያዩ እርምጃዎችን ይወስዳል አረሞችም ከአካባቢው ጋር የመላመድ ችሎታ ስላላቸውና በአጠቃቀም ጉድለት የተገኘውን አጋጣሚ በመጠቀም ራሳቸውን በማስፋፋት ይታወቃሉ፡፡
ልዩ ባህሪያቸው ምንድን ነው፡-
በፍጥነት የማደግ ፣በፍጥነት የመራባት ፣ዘራቸው በርቀት የመሰራጨት ፣ራሳቸውን ከአካባቢው በቀላሉ የማላመድና የመራባት ችሎታ ወ.ዘ.ተ አላቸው፡፡

አደገኛና መጤ አረም የሚያስከትለው ጉዳት

1. በብዝሃህይወት፤ በእርሻ፤ በዉሃ ሀብትና በሰው ልጅ ጤና ላይ ጉዳት ያስከትላሉ፡፡
2. የተፈጥሮ ሚዛንን በማዛበት የስነ-ምህዳር ሂደቶችን ያራቁታል
3. ነባር ዝርያዎችን በየትኛውም ስነ ምህዳር በመላ አለም ዙሪያ በመስፋፋት በተለያየ መንገድ በመሻማትና ጥገኛ በመሆን አሉታዊ ተፅዕኖ በመፍጠር ያጠፋሉ፡፡
4. በተለያዩ የመሬት ይዞታዎች ፣ በእርሻ ማሳ ፣ በግጦሽ መሬት ወ.ዘ.ተ በመስፋፋት የሰብል ምርትና ምርታማነትን ይቀንሳል፡፡
5. የመኖ ዝርያን በማጥፋት ከእንስሳት የሚገኘውን ምርት ይቀንሳል፡፡
6. በውሃ አካላትና ጥብቅ ስፍራዎች ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ ያሳድራሉ፡፡
7. የእንስሳት መኖና ተዋፅኦ ጣዕም ማበላሸትና የተዋፅኦ ጥራቱን መቀነስ /የወተትና የማር ጣዕም መቀየር/
8. ለሌሎች ተባዮች መጠጊያ መሆን
9. በሰብል ላይ ጥገኛ መሆንና ጉዳት ማድረስ
10. በመስኖ ቦታዎችና ቦዮች ላይ ችግር በመፍጠርና የውኃውን ፍሰት መዝጋት

በቅርቡ በተካሄደ ጥናት በአገራችን 35 መጤና ወራሪ የሆኑ አረሞች ተለይተው የታወቁ ሲሆን ከነኝህም መካከል ፕሮሶፒስ ጁሊፍሎራ/Prosopis juliflora, ፓርቲኒየም/Parthenium hysterophorus), እንቦጭ/Water hyacinth (Eichhornia crassipes), የወፍ ቆሎ/Lantana camara, የተለያዩ የግራር ዝርያዎች/Acacia species, እና ኦሮባንቼ/Orobanche የተባሉት ዝርያዎች ዋና ዋናዎቹ ናቸው፡፡

በአማራ ክልል ጉዳት እያደረሱ ያሉ መጤ ወራሪ ዕፅዋቶች …
1.ቅንጨ /Parthenium hysterophorus/
2.Eichhornia crassipe
3. የወፍ ቆሎ/Lantana camara/
4. ነጭ ለባሽ/ /የአህያ ሾህ /Argemone ochroleuca/
5.በግድ ዘመድ/ደርግ /Xanthium strumarium
6. አሚኬላ /Hygrophila auriculata/
7. ፕርፕሮሶፒስ /ወያኔ ዛፍ/ Prosopis juliflora/
8. ሰርክ አበባ /Senna didymobotrya /
9. ቦረን /Chrysanthium segetem/
10. አቀንጭራ
ዳይመረጭ/የጅብ ራስ /Orobanche spp/
12. ኑግ አንበሳ /Cuscuta spp/
13.እንቦጭ Eichhomiae crossipe

ማን ይሥራው ?

• ኅ/ሰቡንና ሌሎች አጋር አካላት
• በሰው ጉልበት በራሱ የልማት መሣሪያዎች
• በቀበሌዎች የክትትልና የአስወጋጅ ግብረ ኃይል ማቋቋም
• የት/ቤት ማኅበረሰብን ከአካባቢው ኅብረተሰብ ጋር አቀናጅቶ ማንቀሳቀስ
የመጤ ተስፋፊ ዕፅዋት/አረም አያያዝ ፕሮገራም ጥቅል ስልቶች
መከላከል-ተስፋፊ መጤ ዕፅዋት አዲስ መሬት እንዳይወሩ ማድረግ(የዘር ንፅህናን መጠበቅ፣ አረሞችን ዘር ከመፍጠራቸው በፊት ማስወገድ፣ ዘሮችንና ሌሎች የመራቢያ አካላት ስርጭት መከላከል፣የዘር ኝፅህናን የሚያስከብሩ ህጎችን ማውጣት)
መቆጣጠር- ተስፋፊ መጤ ወራሪ ዕፅዋቱ በምጣኔ ሀብት ላይ የሚፈጥረውን አሉታዊ ተፅዕኖ መቀነስ
ማስወገድ- ከተወረረው አካባቢ ሁሉንም የተስፋፊ መጤ ወራሪ ዕፅዋቶችና የመራቢያ አካላት ማስወገድን ይጨምራል
ምንጭ ፡-ባ/ዳር ብዛሂዎት
nvasive alien plant species in Ethiopia: ecological impacts on biodiversity a review paper

በደሃና ወረዳ በ18 ቀበሌዎች ላይ የ2018 ዓ.ም የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር ተጀመረ፡፡=====================================ሐምሌ 20/2018 ዓ.ም፤ ...
28/07/2026

በደሃና ወረዳ በ18 ቀበሌዎች ላይ የ2018 ዓ.ም የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር ተጀመረ፡፡

=====================================
ሐምሌ 20/2018 ዓ.ም፤
አምደወርቅ

የደሃና ወረዳ አካባቢና ደን ጥበቃ ፅ/ቤት የሬድ ፕላስ ፕሮጀክት ከደሃና ወረዳ ግብርና ፅ/ቤት ጋር በመተባበር የ2018 ዓ.ም የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር የወረዳና የከተማ አስ/ር አመራሮች እና ሰራተኞች፣የሃገር መከላከያ ሰራዊት፣ የፊደራል ፖሊስ፣ሰላም አስከባሪዎች፣ አ/አደሮች፣ የከተማ ነጋዴዎች እንዲሁም የክረምት በጎ ፈቃደኞች በተገኙበት ተጀምሯል፡፡

የደሃና ወረዳ አካባቢና ደን ጥበቃ ፅ/ቤት ሃላፊ ወ/ሮ ትዕግስት መንግስቴ እንደገለጹት በየዓመቱ በሚካሄደው የአረንጓዴ አሻራ ልማት እንቅስቃሴ በርካታ ቁጥር ያላቸው የተለያዩ የሃገር በቀልና የውጭ የችግኝ ዝርያዎች መተከላቸውን ገልፀዋል።

በዛሬው ዕለትም በ18 ቀበሌዎች ላይ የ2018 ዓ.ም አረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የተዘጋጁ የተለያዩ ችግኞችን በመትከል በይፋ ተጀምሮ በቀጣይ የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብሮች ሌሎች በርካታ ቁጥር ያላቸው የችግኝ ዝርያዎች የሚተከሉ መሆናቸውን ገልጸዋል፡:
ችግኞችን መትከል ብቻ ሳይሆን በባለቤትነት ሊኖር በሚገባ ሁሉም የተተከሉ ችግኞችን መንከባከብና መጠበቅ ነው።

27/07/2026
በደሃና ወረዳ ግብርና/ል/ጽ/ቤትና በሬድ ፕላስ ፕሮጀክት የአረንጓዴ አሻራ  ችግኝ ተከላ  መርሃግብር በንቅናቄ  ተጀመረ።ደሃና፣ ጭላ፣ሃምሌ 17/2018 ዓ.ም ( Dehana Woreda Comm...
27/07/2026

በደሃና ወረዳ ግብርና/ል/ጽ/ቤትና በሬድ ፕላስ ፕሮጀክት የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ መርሃግብር በንቅናቄ ተጀመረ።

ደሃና፣ ጭላ፣ሃምሌ 17/2018 ዓ.ም ( Dehana Woreda Communication) በዋግ ኽምራ ብሄረሰብ አስተዳደር የደሃና ወረዳ ግብርና ልማት ጽ/ቤት እና በሬድ ፕላስ ፕሮጀክት በ022 ጭላ ቀበሌ "ተስፋን እንትከል" በሚል መረቃል የ20 18 ዓ.ም የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ መርሃግብር በንቅናቄ ተጀምሯል።

የደሃና ወረዳ ግብርና ልማት ጸ/ቤት የተፈጥሮ ሃብት ቡድን መሪ የሆኑት አቶ ገ/ ህይወት ኃይሌ እንደተናገሩት በ2018 ዓ.ም ለ2019 በጀት ዓመት 2 ሚሊዮን 50 ሽህ 643 የተዘጋጀውን የደን :የመኖ ችግኝና ቁርጥራጭ (ግንጣይ )እንዲሁም የፌራፍፌ ችግኝ በ20 ቀበሌዎች 48 የወል ተከላ ሳይት ፣ በሃይማኖት ተቋማት ፣ በግለሰብ ፣ በአግሮ ፎረስተሪ 1221 ሄ/ር መሬት ላይ ተከላ እንደሚካሄድ አስረድተዋል።

አክለውም ሁሉም ተከላ የሚካሄዱ ቀበሌዎች ቀጣይ ሳምንት ሙሉ በሙሉ የችግኝ ተከላ ሰራው እንደሚከናወን ጠቁመዋል ።

በተከላ ግዜ እና ድህረ ተከላ ግዜ ከምናከናውናቸው ለችግኝ ፅድቀት ወሳኝ የሆኑ ተግባራት በተጨማሪ ተከላ በሚካሄድበት ሳይት የዕርጥበት እቀባ ሰራዎችንም ተቀናጅቶ መተግበር እንዳለበት አቶ ገብረህይዎት ኃይሌ አመላክተዋል።

በዚህ ፕሮግራም የደሃና ወረዳ ተቀዳሚ ዋና አስተዳዳሪ ዘገየ አለልኝ ዶ/ር እንደተናገሩት
የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ-ግብር ለአየር ንብረት ጥበቃ ሚያበረክተው አስተዋፅዖ ከፍተኛ እና ለሰው ልጅ የመኖርና ያለመኖር የህልውና ጉዳይ እንደሆነ አመላክተው የችግኝ ተከላ ስራን በመርሃ-ግብር የሚሰራ ሳናደርገው ባህላችን አድርገን ልንተክልና ልንከባከብ ይገባናል ብለዋል።

ዋና አስተዳዳሪው አክለውም ችግኝ መትከልን የነገ ተስፋችን እና እራያችን ነው በማለት ሁሉም ማህበረሰብ መትከል ብቻ ሳይሆን መንከባከብም ጭምር እንዳለበት አሳስበዋል።

የደሃና ወረዳ ግብርና ልማት ጽ/ቤት ኃላፊ የሆኑት አቶ ዘነበ ማሞ በበኩላቸው ዛሬ የችግኝ ተከላ መርሃግብር ተጀመረ እንጅ አልጨረስነውም በመሆኑም ችግኝ ለመትከል ስንመጣ ለተከላ የሚያስፈልጉ ቁሳቁሶችን በመያዝ በአግባቡ መተከል እንዳለባቸው ገልጸዋል።

በተጨማሪም ችግኝ የተተከለባቸውን ተፋሰሶች ዘበኛ ብቻ ሳይሆን መጠበቅ ያለበት ህብረተሰቡ የኔ ብሎ በመያዝ በወቅቱ በመኮትኮት እና ዝናብ ሲያቆም ማጠጣት ከእንሰሳት ንክኪ ነጻ ማድረግ እንደለበት የሁሉም ማህበረሰብ ኃላፊነት እንደሆነ አመላክተዋል።

በዚህ ፕሮ ግራምም የወረዳ አሰተባባሪ ኮሚቴ :የፌደራል ፖሊስ አባላት : የበጎፍቃድ ወጣቶች :የወረዳ አመራሮችን እና አጋር አካላት በተገኙበት በይፋ ተጀምሯል።

#በአምጣቸው አዳነ

ተጨማሪ መረጃዎችን እንድናደርስዎት የደሃና ወረዳመንግስት ኮሙኒኬሽንን ለማግኘት ቀጣዮቹን ሊንኮች ይጫኑ።

Facebook
https://www.facebook.com/profile.100066304790042
👉YouTube ፤
https://youtube.com/channel/UCBbTi4Tq6iNrrxwMyg22FtQ
👉Telegram
https://t.me/amd1512
👉TikTokሀ
tiktok.com/
👉
https://x.com/wereda169222/status/2000868480283730223?t

05/07/2026

ኢትዮጵያ በ2050 የካርበን ልቀትን ሙሉ በሙሉ ለመቀነስ እየሰራች ነው
+++++++++++++++++

│ኢትዮጵያ በሚቀጥሉት 10 ዓመታት የሙቀት አማቂ ጋዞች ልቀትን በ70 ነጥብ 3 በመቶ ለመቀነስ፣ እንዲሁም በ2050 የካርበን ልቀትን ወደ ዜሮ ለማድረስ እየሰራች መሆኑን የፕላንና ልማት ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡

የፕላንና ልማት ሚኒስትር ዴኤታ ስዩም መኮንን፣ የካርበን ሽያጭን (Carbon Market) በአዲስ አቅጣጫ ለመጀመር በተዘጋጀው መድረክ ላይ እንደገለጹት፤ ኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥን ለመከላከል ከፖሊሲ ቀረጻ ጀምሮ በርካታ ተጨባጭ ተግባራትን እያከናወነች ትገኛለች፡፡

በ2050 የሙቀት አማቂ ጋዞች ልቀትን ወደ ዜሮ ለማድረስ ግብ አስቀምጣ እየሰራች መሆኑን የገለጹት ሚኒስትር ዴኤታው፤ የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖን ለመከላከልና ለመቋቋም የሚያስችል ብሔራዊ የፖሊሲ ዕቅድ ተቀርጾ ተግባራዊ እየተደረገ እንደሚገኝም አብራርተዋል፡፡

ይህንን ግብ ለማሳካት በአጭርና በረጅም ጊዜ የሚተገበሩ ኢኒሼቲቮች ወደ ሥራ መግባታቸውን የጠቀሱት አቶ ስዩም፤ በተለይም የአረንጓዴ አሻራ መርሐግብር፣ የታዳሽ ኃይልና መሰል ተግባራት ተጨባጭ ውጤት አስመዝግበዋል።

የፓሪሱን የአየር ንብረት ስምምነት ተከትሎ፣ ኢትዮጵያ በፍቃደኝነት ላይ የተመሰረተና የአየር ንብረት ለውጥን ለመቀነስ የሚያስችላትን 3ኛውን የኤንዲሲ (NDC) ሰነድ ባለፈው መስከረም ወር ለተባበሩት መንግስታት ድርጅት ማስገባቷንም ሚኒስትር ዴኤታው አስታውሰዋል፡፡

በታደሠ ብናልፈው

#ኢትዮጵያ

05/07/2026
05/07/2026
የመጠቀሚያ ጌዜ ያለፈባቸውን ኬሚካሎች የማስወገጃ ማዕከል ሊገነባ መሆኑን በኢፌደሪ አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ይፋ ተደረገ።
05/07/2026

የመጠቀሚያ ጌዜ ያለፈባቸውን ኬሚካሎች የማስወገጃ ማዕከል ሊገነባ መሆኑን በኢፌደሪ አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ይፋ ተደረገ።

ከሕዳሴው ግድብ ቀጥሎ መላው ኢትዮጵያዊ በአንድ ፅኑ ሐሳብ የተመመበት የአረንጓዴ አሻራ ንቅናቄ*******************በ2011 ዓ.ም የተጀመረውና ላለፉት ሰባት ዓመታት በተከታታይ ከሕፃ...
25/06/2026

ከሕዳሴው ግድብ ቀጥሎ መላው ኢትዮጵያዊ በአንድ ፅኑ ሐሳብ የተመመበት የአረንጓዴ አሻራ ንቅናቄ
*******************

በ2011 ዓ.ም የተጀመረውና ላለፉት ሰባት ዓመታት በተከታታይ ከሕፃናት እስከ አዋቂ ከ20 ሚሊዮን በላይ ዜጎችን በብሔራዊ ንቅናቄ ያሳተፈው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር፣ በሀገሪቱ ሁለንተናዊ ገጽታ ላይ ታሪካዊና ተጨባጭ ለውጦችን እያስመዘገበ ይገኛል። እስካሁን ባለው ሂደት በመላው ሀገሪቱ ወደ 48 ቢሊዮን የሚጠጉ ችግኞች የተተከሉ ሲሆን፣ ይህም የሀገሪቱን የደን ሽፋን ከነበረበት 17.2 በመቶ ወደ 23.6 በመቶ ከፍ እንዲል አድርጎታል።

ይህ መርሃ-ግብር በሥነ-ምህዳርና በውሃ ሀብት ጥበቃ ላይ ያመጣው ተፅዕኖ ከፍተኛ ሲሆን፣ በተለይም ላለፉት 18 ዓመታት ደርቆ የነበረው የሐሮማያ ሐይቅ እና ከስምጥ ሸለቆ ሐይቆች አንዱ የሆነው የአባያ ሐይቅ እንዲያገግሙ አስችሏል። ከዚህም በተጨማሪ የተቆፈሩት ዘጠኝ አኃዝ ያላቸው ጉድጓዶች እንደ ሰው ሠራሽ የውሃ ማጠራቀሚያ ጋን በመሆን ውሃ ወደ መሬት እንዲሰርግ በማድረጋቸው፣ የከርሰ-ምድር ውሃ መጠን እንዲጨምርና ደርቀው የነበሩ ምንጮች ዳግም እንዲፈልቁ ምክንያት ሆኗል።

በአረንጓዴ አሻራው የምግብ ዋስትናን ከማረጋገጥ አኳያም መርሃ-ግብሩ እንደ አቮካዶ ባሉ ለምግብነት፣ ለንብ ማነብ፣ ለኢኮኖሚ ጠቀሜታና ለውጭ ገበያ የሚውሉ የፍራፍሬ ዝርያዎች በብዛት አንዲመረቱ በማስቻልም ረገድ ትልቅ እገዛ አድርጓል።

በቀጣናዊና ዓለም አቀፋዊ መድረኮችም ኢትዮጵያ የአብዛኞቹ የጎረቤት ሀገራት የውሃ መነሻ በመሆኗ፣ የምታከናውነው የተፋሰስ ልማት የቀጠናውን የውሃ ፍላጎት ለማዳረስ ከፍተኛ ሚና እያበረከተ ይገኛል። በዚህም ለአረንጓዴ ዲፕሎማሲ ማሳያ የሚሆን የችግኝና የልምድ አካፍሎት ለጅቡቲ፣ ለደቡብ ሱዳንና ለኬንያ የተደረገ ሲሆን፣ ከዛምቤዚ ሪቨር ኮርስ ኮሚሽን የተውጣጡ የ7 ሀገራት ልዑካንም የኢትዮጵያን ተሞክሮ ወስደዋል።

በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት፣ በዓለም ኢኮኖሚ ፎረም እና በምግብና እርሻ ድርጅት (FAO) 80ኛ ዓመት የምሥረታ በዓል ላይ የኢትዮጵያ አረንጓዴ አሻራ ከፍተኛ ዓለም አቀፍ እውቅናን አትርፏል።

ከፖለቲካና ከግል ጥቅም ባለፈ ከ“እኔ” ይልቅ ለ“እኛ” የሚያስብ ብሔራዊ እሴት ሆኖ የዳበረው ይህ መርሃ-ግብር፣ በገጠርም በከተማም ሠራተኞች ከአለቆቻቸው ጋር በአንድነት ወጥተው የሚተክሉበትና የሚወያዩበት መድረክ በመፍጠሩ ተቋማዊ ተግባቦትን አጎልብቷል። በዚህም ከሕዳሴ ግድብ ቀጥሎ መላው ኢትዮጵያዊ በአንድ ፅኑ ሀሳብ የተመመበት ትልቁ የጋራ መግባባት መርሃ-ግብር ተደርጎ ይወሰዳል።

በብሌን ደምበሎ

13/06/2026

አረንጓዴ አሻራ የ7 ዓመታት ጉዞ
***********

✅ ጠቅላላ የተተከሉ ችግኞች ➡ ከ48 ቢሊዮን በላይ

✅ የችግኞች የመጽደቅ ምጣኔ ➡ 84% (ከ40 ቢሊዮን በላይ የጸደቁ)

✅ የሀገራችን የደን ሽፋን ➡ ከነበረበት 3% ተነሥቶ ወደ 23.6% ደርሷል

✅ ያገገመ የተራቆተ መሬት ➡ ከ10 ሚሊዮን ሔክታር በላይ

✅ የተፈጠረ ጠቅላላ የሥራ ዕድል ➡ ከ1.2 ሚሊዮን በላይ ዜጎች

Address

Environment And Forest Protection , Climatic Change To Adaptation And Mitigation Measures
Sokota
WFRY

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የደሃና ወረዳ የአካባቢና የደን ጥበቃ ጽ/ቤት/Dehana woreda Enviroment and forest protection posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share