03/09/2026
አስደሳች ዜና
በሀገሊ02 ጤና ጣቢያ ለመጀመሪያ ጊዜ እናት በቀዶ ጥገና በሰላም ተገላገለች
ነሐሴ 28፣ 2018 (ዳውሮ ዞን ጤና መምሪያ) በዳውሮ ዞን ኢሰራ ወረዳ ሀገሊ 02 ጤና ጣቢያ አንድ እናት ለመጀመሪያ ጊዜ በቀዶ ጥገና ማዋለጃ አገልግሎት በሰላም መገላገሏ ተገልጿል ፡፡
እናትና በቀዶ ጥገና የተወለዶ ህፃን በአሁኑ ወቅት በጥሩ የጤና ሁኔታ ላይ እንደሚገኙ ነው የተገለጸው፡፡
የተቀናጀ የድንገተኛ ቀዶ ጥገና ባለሙያ የሆኑት (ISO) አቶ አግኝቸው አምሳሉ እንደገለጹት፣ በሌሎች ጤና ጣቢያና ሆስፒታል ደረጃ በቀዶ ጥገና ማዋለድ የተለመደ ቢሆንም፤ በኢሠራ ወረዳ እና ለእናቶች በአቅራቢ ሌላ አማራጭ ቀዶ ጥገና ማዋለጃ ሆስፒታል ባለመኖሩ ከዚህ ቀደምስል በርካታ እናቶችና ህፃናት በወሊድ ምክንያት ለሞትና ለተዛማች ህመም ስቃይ ስዳረግ በመቆየቱ በዛሬው ዕለት በሀገሊ02 ጤና ጣቢያ አንድ እናት በቀዶ ጥገና በሰላም ማዋለድ መቻሉ የመጀመሪያ ጊዜ በመሆኑ ጤና ባለሙያዎችንና አከባቢ ማህበረሰብን እንዳስ ደሰታቸው ተገልጿል ።
የቅድሜ ወሊድ ምርመራ እየተደረገላት እንደቆየችና ምጥ ከመጀመሯ በፊት ወደ ጤና ጣቢያ መምጣት እንዳለባት በቂ ግንዛቤ ስለነበረ አንድ ቀን ቀደም ብሎ ወደ ጤና ጣቢያ መጥተው የሕክምና ክትትል ስር ከቆየች በኃላ በዛሬው ዕለት በቀዶ ጥገና በሰላም መገላገላቸው እንዳስ ደሰታቸው ቤተሰቦቿና ወላድ አባት አቶ ንጉሰ በጋጆ ገልጸዋል።
የጤና ጣቢያ ኃላፊ አቶ ማሞ መኩሪያ እንደገለፁት በአሁኑ በጤና ጣቢያ ደረጃ በቀዶ ጥገና የማዋለጃ አገልግሎት ለመስጠት በቂ ዝጅት ተደረጎ አገልግሎት እየተሰጠ እንደሆነ አብራርቷል።
የዳውሮ ዞን ጤና መምሪያ ኃላፊ አቶ ያዕቆብ ሌንጫ እና የወረዳው ጤና ጽ/ቤት ተወካይ አቶ ዘላለም ተረፈ እንደገለፁት በጤና ጣቢያው ያልተቋረጠ የቀዶ ጥገና የማለጃ አገልግሎት ሥራ ጎን ለጎን ሁሉ አቀፍ የእናቶችና ህፃናት ህክምና አገልግሎት ትግብራ ለማጠናከር በትኩረት የድጋፍና ክትትል ብሎም የግብዓት አቅርቦት ሥራ እንደሚሰሩ ገልጿል።
ዘገባው : የዳውሮ ዞን ጤና መምሪያ ነው።