26/02/2026
በታርጫ ከተማ በቤቶች ማህበር ለተደራጁ 11 ማህበር በዛሬው ዕለት መሬት ተላልፏል።
መንግሥት በአነሰተኛ ቁጠባ ዘጎች የቤት ባለቤት ለማድረግ በተቀመጠው መመሪያ መሰረት ሙሉ መስፈርቶችን አሟልተው የተገኘ 154 አባላት ዛሬ የዕጣ ማስነሳት መርሀግብር ተከናውኗል።
የታርጫ ከተማ ማዘጋጀ ቤታዊ አገልግሎት ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ባቲሳ ወንድሙ የታርጫ ከተማ ማዘጋጃ በተለያዬ ማህበራዊ መሠረት ለተደራጁ ነዋሪዎች ከሀገር መከላከያ በክብር ለተሰናበቱት አባላት፣ ለመምህራን፣ ለነዋሪዎች ከዚህ በፊት ከሶስት መቶ በላይ ማህበራት የቤት መስሪያ ቦታ ያስተላለፈ ሲሆን በዛሬ ቀን ደግሞ ለ11 ማህበራት መሬት በማዘጋጀት አስተላልፏል።
የታርጫ ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት አደረጃጀት ዘርፍ ኃላፍ ወ/ሮ ብርቱካን ዘውዴ በመርሀግብሩ ላይ በመገኘት ፓርቲያችን ብልጽግና ለዜጎች ቅድሚያ የሚሰጥ ፓርቲ በመሆኑ ዘጎች የመኖሪያ ቤት እንዲያገኙ ከሁሉም የቅድሚያ ቅድሚያ በመሰጠት ያመቻቸ መሆኑን ተናግሯል።
በመጨረሻም በዛሬው ዕለት መሬት የተረከቡት የማህበሩ አባላት በበኩላቸው መሬት በማገኘት የተሰማቸውን ደስታ በመግለጽ የከተማ መንግሥትን አመስግነዋል ሲል የዘገበው የታርጫ ከተማ አስተዳደር የመንግሥት ኮሚዩኒኬሽን ነው።
Tarcha Town Municipality fans Southwest Communications