የጨና ወረዳ ኮሙኒኬሽን Chena Woreda Communications

  • Home
  • Ethiopia
  • Wacha
  • የጨና ወረዳ ኮሙኒኬሽን Chena Woreda Communications

የጨና ወረዳ ኮሙኒኬሽን Chena Woreda Communications Chena Woreda Communications

የቦንጋ መናሀሪያ ህጋዊ የታሪፍ ማሳወቂያ!!የቦንጋ ከተማ አስተዳደር ትራንስፖርት ጽሕፈት ቤት ከ ትራፊክ ፖሊስ ማስተባበሪያ ጋር በመቀናጀት ህገ-ወጥ የዋጋ ጭማሪን ለመከላከልና ተሳፋሪዎችን ከ...
30/08/2026

የቦንጋ መናሀሪያ ህጋዊ የታሪፍ ማሳወቂያ!!

የቦንጋ ከተማ አስተዳደር ትራንስፖርት ጽሕፈት ቤት ከ ትራፊክ ፖሊስ ማስተባበሪያ ጋር በመቀናጀት ህገ-ወጥ የዋጋ ጭማሪን ለመከላከልና ተሳፋሪዎችን ከብዝበዛ ለመታደግ የጉዞ ታሪፍ ማሳወቂያ ባነር በመናሀሪያው መውጫ መቁረጫ ቢሮ ግድግዳ ላይ በግልጽ እንዲለጠፍ አድርጓል።

:-

#ግልጽነት:-ተሳፋሪዎች ከመሳፈራቸው በፊት ህጋዊውን ታሪፍ ማወቅ እንዲችሉ ማድረግ።
:- ከአሽከርካሪዎችና ደላሎች የሚደርሰውን ህገ-ወጥ የዋጋ ጭማሪ በዘላቂነት መግታት።

:- የትራፊክ ፖሊሶችና ተቆጣጣሪዎች ጥብቅ ቁጥጥር እንዲያደርጉ ምቹ ሁኔታ መፍጠር።

#የተላለፈ-ጥሪ:-
#ለተሳፋሪዎች-በመናሀሪያው የተለጠፈውን ባነር በማየት ትክክለኛውን ህጋዊ ክፍያ ብቻ ይክፈሉ፤ ከተቀመጠው ዋጋ በላይ የሚጠይቁ አካላት ሲያጋጥሙዎት ወዲያውኑ ለትራፊክ ፖሊስ ወይም ለመናሀሪያው አስተዳደር ጥቆማ ይስጡ።

#ለአሽከርካሪዎች:-ከህጋዊው ታሪፍ ውጪ ትርፍ ገንዘብ ማስከፈል በጥብቅ የተከለከለ ነው። መመሪያውን ጥሰው በሚገኙ አካላት ላይ ተሽከርካሪን እስከ ማገድና ከባድ የገንዘብ ቅጣት የሚጣል መሆኑን እንገልፃለን።

የሚመለከቷቸው ዋና ዋና መስመሮች: ጌሻ፣ አዲዮ፣ ጠሎ፣ ጨታ፣ ዴቻ፣ ጨና፣ ሺሺንዳ፣ ቢጣ፣ ቴፒ፣ ጂማ፣ ሚዛን እና ሌሎች አከባቢዎች መሆናቸውም ተጠቅሷል።

የካፊቾ ብሔር ዘመን መለወጫ በዓል "ማሽቃሮን" የአለም የማይዳሰስ ቅርስ ሆኖ እንዲመዘገብ እየተደረገ ባለው ጥረት ውስጥ የበኩላችንን እንወጣለን፦ የዋቻ ከተማ ነዋሪዎች።የካፊቾ ብሔር ዘመን መ...
30/08/2026

የካፊቾ ብሔር ዘመን መለወጫ በዓል "ማሽቃሮን" የአለም የማይዳሰስ ቅርስ ሆኖ እንዲመዘገብ እየተደረገ ባለው ጥረት ውስጥ የበኩላችንን እንወጣለን፦ የዋቻ ከተማ ነዋሪዎች።

የካፊቾ ብሔር ዘመን መለወጫ በዓል የሆነውን "ማሽቃሮን" የአለም የማይዳሰስ ቅርስ ሆኖ እንዲመዘገብ እየተደረገ ባለው ጥረት ውስጥ የበኩላቸውን እንደሚወጡ የዋቻ ከተማ አስተዳደር ነዋሪዎች ተናገሩ።

የካፋ ብሔረሰብ ጥንት የራሱ የሆነ ባህል፣ታሪክ፣የአስተዳደር ሥርዓት እና የዘመን አቆጣጠር ቀመር ያለው ማህበረሰብ መሆኑን የታሪክ ድርሳናትና የታሪክ አዋቂዎች ይናገራሉ።

ከዚህ ውስጥ የብሔሩ ዘመን መለወጫ ወይም የ"ማሽቃሮ በዓል" አንዱ ነው።

ማሽቃሮ በየዓመቱ በመስከረም ወራት ውስጥ የሚከበር ደማቅና ታሪካዊ በዓል ነው።

ይህን በዓል በየዓመቱ ከማክበር አልፎ በአሁን ወቅት በአለም አቀፍ የተባበሩት ዜጎች የትምህርት፣ሳይንስና ባህል ድርጅት ዩኒስኮ የአቀም የማይዳሰስ ቅርስ አካል ሆነው እንዲመዘገብ ዘርፍ ብዙ ተግባራት እየተከናወኑ ይገኛሉ።

በዚህ ላይ ለጣቢያችን አስተያየታቸው የሰጡት የብሔሩ ተወላጆች መከካል የዋቻ ከተማ ነዋሪ የሆኑት አቶ ንጋቱ ወ/ትንሳዔና አቶ ባህሪ አምቦ ካፌቾ የራሱ የሆነ ባህል፣ታሪክ እና ትውፊት ያለው ብሔር መሆኑን አስረዲተዋል።

የካፌቾ የጥንት የአስተዳደር እና የባህል እሴቶች ባለቤት መሆኑን ያስገነዘቡት እነዚህ የዋቻ ከተማ ነዋሪዎች የምክረቾ"ሥርዓትን ከኢትዮጵያ አልፎ ለአም ያበረከት የታላቅ ታሪክ ባለቤት መሆኑን ገልፀዋል።

የካፌቾ ብሔር የጀግንነትና የመቻቻል ተምሳሌት መሆኑን ያነሱት ነዋሪዎች 3 ዋና ዋና ብሔረሰቦች እና ሌሎች የኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰቦች ጋር ተከባብሮ የሚኖር መሆኑ ለዚህ ማሳያ ነው ብለዋል።

ካፌቾ የራሱ የሆነ የዘመን አቆጣጠር ቀመር (yemeenee shadeyoo) የተሰኘ የራሱ ካላንደር ያለው ቀደምት የስልጣኔ ባለቤት መሆኑን ያስረዱት ደግሞ ሌለኛው የዋቻ ከተማ ነዋሪዎች አቶ ሀብታሙ ከሮ እና አቶ ስጦታ ሽፈራ ናቸው።
ነዋሪዎቹ አክለው የካፊቾ ዘመን መለወጫ ማሽቃሮ በዓል በየዓመቱ መከበረ ከጀመረ ረጅም ዓመታትን ያስቆጠረ መሆኑን አመላክተዋል።

ይህ በዓል የካፊቾዎች እምቅ ታሪክና ባህልን አጣምሮ የያዘ ታላቅ ሁነት መሆኑን ገልዋል።

በዓሉ ከብዙ ውጣ ወረዶችን ተሻግሮ ከብሔሩ መገለጫነት አልፎ በአለም የሰው ልጆች ወካይ የማይዳሰስ ቅርስ ሆነው በዩኒሲኮ"UNESCO" መመዝገብ የሚያስችለውን መስፈርት እንዳሟላ የሚያመላክት የምስራች ዜና በመስማታቸው ደስተኞች እንደሆኑም ተናግረዋል።

በዓሉ አሁን ለደረሰበት ደረጃ የበኩላቸውን ለተወጡት አካላት ምስጋናቸውን ያቀረቡት ነዋሪዎች ለስኬታማነቱ ቀጣይ በሚኖሩ ተግባራት ላይ ሁሉ አቀፍ ድጋፋቸውን የሚያጠናክሩ መሆናቸውን አረጋግጠዋል ሲል የካፋ ማህ/ሬ/ቴሌ/ድርጅት ዘግቧል።

የጨና ወረዳ የክረምት በጎ ፈቃደኝነት አገልግሎት አቅመ ደካማ ወገኖችን በመደገፍ ላይ ትኩረቱን ቀጥሏል፤የክረምት በጎ ፈቃደኝነት አገልግሎት አቅመ ደካማ ወገኖችን በመደገፍ፣ የኑሮ ሁኔታቸውን ...
30/08/2026

የጨና ወረዳ የክረምት በጎ ፈቃደኝነት አገልግሎት አቅመ ደካማ ወገኖችን በመደገፍ ላይ ትኩረቱን ቀጥሏል፤

የክረምት በጎ ፈቃደኝነት አገልግሎት አቅመ ደካማ ወገኖችን በመደገፍ፣ የኑሮ ሁኔታቸውን በማሻሻልና ለቤተሰቦቻቸው የተሻለ ዕድል በመፍጠር ተግባራዊ ድጋፍ እያደረገ ይገኛል።

በዚህ መሠረት በቦባ ወዲቲ ቀበሌ ጎማ ሰፈር የሚኖሩትን የአቶ በላይ ባሮ ቤት የመገንባት ሥራ በበጎ ፈቃደኞች እየተከናወነ ነው።

አቶ በላይ ባሮ አይነ ስውር የሆኑ ዜጋ ሲሆኑ፣ በራሳቸው አቅም የተሻለ መኖሪያ ቤት መገንባት በማይችሉበት ሁኔታ የበጎ ፈቃደኞች ድጋፍ ተግባራዊ ሆኗል።

የቤት ግንባታው በተጨማሪ ለአቶ በላይ ባሮ ልጆች የመማሪያ ቁሳቁስ እና አልባሳቶች በወረዳው ሴቶች ህጻናትና ወጣቶች ማህበራዊ ጉዳይ ጽ/ቤት ድጋፍ አድርጓል።

ይህም በቤተሰቡ ላይ የተከሰተውን የኑሮ ችግር በቤት ግንባታ ብቻ ሳይወሰን፣ የልጆቹን የትምህርት ሂደት ለማጠናከር ጭምር በተቀናጀ መልኩ ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ያሳያል።

በወረዳው የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት እስካሁን 15 የአቅመ ደካማ ወገኖች ቤቶች እንዲገነቡ ድጋፍ የተደረገ ሲሆን፣ ተግባሩ በቀጣይም በማስፋት እንደሚቀጥል ተገልጿል።

የበጎ ፈቃድ አገልግሎቱ የመኖሪያ ቤት በመገንባት ብቻ ሳይገደብ፣ የተቸገሩ ወገኖችን በምግብ፣ በትምህርት ቁሳቁስና በሌሎች አስፈላጊ ድጋፎች በመደገፍ ቤተሰቦች ከችግር እንዲወጡ የሚያግዝ ሥራ እየተከናወነ ነው።

በጎ ፈቃደኝነት በዚህ መልኩ በማህበረሰቡ ውስጥ የመተጋገዝና የመረዳዳት ባህልን በማጠናከር፣ ችግረኛ ወገኖችን ከዕለት ተዕለት ችግር በማላቀቅና ልጆቻቸውም ትምህርታቸውን በአግባቡ እንዲቀጥሉ ዕድል በመፍጠር ትርጉም ያለው ማህበራዊ ኃላፊነት እየተወጣ ይገኛል።

በ2019 ዓ.ም በደማቅ ሥነ-ሥርዓት የሚከበረውን የካፊቾ ዘመን መለወጫ በዓል “ማሽ ቃሮ” ለማክበር የተደረገው የቅድመ ዝግጅት ሥራ መጠናቀቁ ተገለጸ።በዘንድሮ ዓመት የካፊቾ ሕዝብ የዘመን መለ...
30/08/2026

በ2019 ዓ.ም በደማቅ ሥነ-ሥርዓት የሚከበረውን የካፊቾ ዘመን መለወጫ በዓል “ማሽ ቃሮ” ለማክበር የተደረገው የቅድመ ዝግጅት ሥራ መጠናቀቁ ተገለጸ።

በዘንድሮ ዓመት የካፊቾ ሕዝብ የዘመን መለወጫ በዓልን ከወትሮ በተለየ መልኩ በደማቅና ሕዝባዊ ተሳትፎን በሚያረጋግጥ ሁኔታ ለማክበር በዞኑ ከፍተኛ ንቅናቄ እየተደረገ ይገኛል።

ይህም የካፋ ሕዝብን ታሪክ፣ ማንነት፣ ባህልና ባህላዊ እሴቶች በማጉላት በዓሉን በዩኔስኮ ለማስመዝገብ እየተደረገ ካለው ጥረት ጋር የተያያዘ መሆኑ ተመላክቷል።

በዚህ መነሻነት የጨና ወረዳና የዋቻ ከተማ አስተዳደር በመቀናጀት የበዓሉን ዝግጅት በመዋቅር ደረጃ እያጠናከሩ ሲሆን፣ ሕዝቡም የራሱን ባህልና እሴት በኩራት እንዲያሳይ ሰፊ የንቅናቄና የተሳትፎ ሥራ እየተከናወነ ነው።

በዛሬው ዕለት የበዓሉ ቅድመ ዝግጅት አካል የሆነውን የቦንጌ ሻምቤቶ የባህል ማዕከል ቤት ዕድሳትና የግቢ ጽዳት የደረሰበትን ደረጃ የጨና ወረዳ ተወካይ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ታምራት ካሳ እና የዋቻ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ተክሌ ታደሰ የመሩት የሁለቱ መዋቅር አስተባባሪ ኮሚቴ ጎብኝቷል።

በጉብኝቱም የባህል ማዕከሉ የቤት ዕድሳትና የግቢ ጽዳት ሥራዎች መጠናቀቃቸውን አረጋግጠው፥ የተከናወነው የዕድሳትና የጽዳት ሥራም በዓሉን ለማስተናገድ የሚያስችል የተሻለ ዝግጅት መፈጠሩን አመላካች ነው ብለዋል።

የባህል ማዕከሉ የካፊቾ ሕዝብ ታሪክና ባህላዊ እሴቶች የሚገለጹበት አንዱ ወሳኝ ስፍራ በመሆኑ፣ ማዕከሉን ማደስና በበዓሉ ዋዜማ በአግባቡ ማዘጋጀት የበዓሉን ታሪካዊና ባህላዊ ይዘት ከማጠናከር ባለፈ ለቀጣይ ትውልድ የሚተላለፈውን የባህል ቅርስ ለመጠበቅም የላቀ አስተዋጽኦ ይኖረዋል ብለዋል።

በመሆኑም የ“ማሽ ቃሮ” በዓል የካፊቾ ሕዝብ ማንነትና ባህላዊ እሴት መገለጫ ብቻ ሳይሆን፣ ባህልን ለመጠበቅ፣ ለማስተዋወቅና ለቀጣይ ትውልድ ለማስተላለፍ የሚያግዝ ሕዝባዊ የትብብር መድረክ እንዲሆን ተጠናክሮ እየተሠራ ይገኛል።

በቅድመ ዝግጅቱ የተገኘው ውጤት የተቀናጀ ሥራና የሁለቱ መዋቅሮች ትብብር ውጤት መሆኑ ተገልጿል።

29/08/2026
"የጤና መድህን አባል መሆናን ከድንገተኛ የህክምና ወጪ ታድጎናል"፦ በጨና ወረዳ የአገልግሎቱ ተጠቃሚዎች የማህበረሰብ አቀፍ ጤና መድህን አባል መሆናቸው ለህክምና የሚያወጡት ከፍተኛ ወጪ እንዲ...
29/08/2026

"የጤና መድህን አባል መሆናን ከድንገተኛ የህክምና ወጪ ታድጎናል"፦ በጨና ወረዳ የአገልግሎቱ ተጠቃሚዎች

የማህበረሰብ አቀፍ ጤና መድህን አባል መሆናቸው ለህክምና የሚያወጡት ከፍተኛ ወጪ እንዲቀንስ ማስቻሉን በካፋ ዞን የጨና ወረዳ የአገልግሎቱ ተጠቃሚዎች ተናገሩ።

በወረዳው ሻቻ ጤና ጣቢያ ተገኝተን ካነጋገሪናቸው ተገልጋዮች መካከል አቶ ወሰነ ገብሬ እና አቶ ከተማ አበበ የማህበረሰብ አቀፍ ጤና መድህን አባል መሆናቸው ለህክምና የሚያወጡት ከፍተኛ ወጪ እንዲቀንስ ማስቻሉን ገልፀዋል።

በጤና ጣቢያው ባለሙያዎች የሚሰጣቸው አገልግሎት መልካም መሆኑን የገለጹት አስተያየት ሰጭዎቹ መድኃኒት በተገብ ሁኔታ እያገኙ መሆኑንም አብራርተዋል።

የሻቻ ጤና ጣቢያ ኃላፊ አቶ አረጋኼኝ ክፍሌ በበኩላቸው 3ሺህ 251 ዜጎች የማህበረሰብ አቀፍ ጤና መድህን ተጠቃሚ መሆናቸውን ገልፀው በ4 ነጥብ 4 ሚልዮን ብር መድኃኒት መገዛቱን ተናግረዋል።

በተጠናቀቀው በጀት ዓመት 11 ሺህ 782 ዜጎች የማህበረሰብ አቀፍ ጤና መድህን ተጠቃሚ መሆናቸውን የተናገሩት ደግሞ የወረዳው ጤና ጽህፈት ቤት ኃላፊ ወይዘሮ አብነት ሲኣ ናቸው።

ማህበረሰቡ የጤና መድህን አባል የመሆን ፊላጎት ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ መምጣቱን ጠቁመዋል።

በወረዳው ባሉ ሁለት ጤና ጣቢያዎች የመድኃኒት እጥረት እንዳይኖር ከ11 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ መድኃኒት ግዥ መፈጸሙን ገልጸዋል።

የማህበረሰብ አቀፍ ጤና መድህን አገልግሎት የጤና እክል በሚገጥምበት ወቅት ዜጎች በድንገተኛ የህክምና ወጭ እንዳይቸገር ዋስትና የሚሰጥ አሰራር ነው ብለዋል።

#ቦንጋ ኤፍ ኤም 97.4

የተገልጋይ እርካታን ማሳደግ የሴክተር መ/ቤቶች ቀዳሚ ተግባር መሆኑ ተገለጸጨና፣ ነሐሴ 22/2018 ዓ.ም — የጨና ወረዳ ፐብሊክ ሰርቪስ የሰው ሀብት ልማት ጽ/ቤት የ2018 ዓ.ም የሴክተር ...
28/08/2026

የተገልጋይ እርካታን ማሳደግ የሴክተር መ/ቤቶች ቀዳሚ ተግባር መሆኑ ተገለጸ

ጨና፣ ነሐሴ 22/2018 ዓ.ም — የጨና ወረዳ ፐብሊክ ሰርቪስ የሰው ሀብት ልማት ጽ/ቤት የ2018 ዓ.ም የሴክተር መ/ቤቶችን የዕቅድ አፈጻጸም ውጤት መነሻ በማድረግ የዕውቅናና ሽልማት መድረክ አካሂዷል።

መድረኩ የተቋማትን የ2018 ዓ.ም የሥራ አፈጻጸም በመገምገም፣ የተሻለ ውጤት ያስመዘገቡ መ/ቤቶችን ለማበረታታት፣ በቀጣይ የሥራ ዘመን የተሻለ አፈጻጸም ለማስመዝገብ አቅጣጫ ለማስቀመጥ እንደሆነ ተገልጿል።

በመድረኩ የተሻለ አፈጻጸም ላስመዘገቡ መ/ቤቶች የዕውቅና ምሥክር ወረቀት የተሰጠ ሲሆን፥ በዚህም የጨና ወረዳ ፍርድ ቤት 1ኛ፣ የጤና ጥበቃ ጽ/ቤት 2ኛ እና የአስተዳደር ጽ/ቤት 3ኛ ደረጃ በመውጣት ዕውቅና ተሰጥቷቸዋል።

በመድረኩ ሴክተር መ/ቤቶች በመንግሥት የተሰጣቸውን ተልዕኮ በብቃት በመፈጸም የተገልጋይ እርካታን በየጊዜው ማሳደግ እንደሚገባቸው ተጠይቋል።

ባለሙያዎችም የሙያ ግዴታቸውን በታማኝነት በመወጣት፣ በሥነ-ምግባር የታነጹ በመሆን፣ ተገልጋዮችን በአክብሮትና በእኩልነት በማገልገል የህዝብን እምነት ማጠናከር እንዳለባቸው ተገልጿል።

የወረዳው ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊ ተወካይና የፖለቲካና የህዝብ ግንኙነት ዘርፍ ኃላፊ አቶ አግዘው ሁሴን፣ የመንግሥት ተቋማት ዋና ትኩረታቸው ህዝብን በተሻለ ሁኔታ ማገልገልና ተጨባጭ ውጤት ማምጣት መሆን እንዳለበት ገልጸዋል።

የሥራ አፈጻጸም ሲመዘን የተገልጋይ እርካታ፣ የአገልግሎት ጥራት፣ ተጠያቂነትና ሙያዊ ሥነ-ምግባር ዋና መለኪያዎች መሆን እንዳለባቸውም አስገንዝበዋል።

የጨና ወረዳ ፐብሊክ ሰርቪስ የሰው ሀብት ልማት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ታሪኩ ኃይሌ በበኩላቸው፣ ዕውቅናና ሽልማቱ ውጤታማ መ/ቤቶችን ለማበረታታትና ሌሎች ተቋማት ከተሻለ አፈጻጸም ተሞክሮ በመውሰድ እንዲሻሻሉ ለማነሳሳት ያለመ መሆኑን ገልጸዋል።

ባለሙያዎች የህዝብን እምነት የሚያጠናክር ሙያዊ ሥነ-ምግባር በመላበስ፣ ተገልጋይን በማክበርና የሙያ ግዴታቸውን በትጋት በመወጣት የአገልግሎት ጥራትን እንዲያሻሽሉ አሳስበዋል።

በመድረኩ የተሳተፉ የሴክተር መ/ቤት ተወካዮችና ባለሙያዎች፣ የዕቅድ አፈጻጸም በግልጽ መለኪያ መገምገሙ ተቋማት የሚያከናውኗቸውን ሥራዎች በማስረጃ እንዲመሩ እና የተጠያቂነት ባህልን እንዲያጠናክሩ እድል የሚፈጥር መሆኑን ገልጸዋል።

ተሳታፊዎቹ በተለይ የተገልጋይ እርካታ የተቋማት ውጤታማነት ቁልፍ መለኪያ በመሆኑ፣ በቀጣይ የሥራ ዘመን ተገልጋዮችን በአክብሮት ማስተናገድ፣ አገልግሎትን በጊዜው መስጠት፣ ቅሬታዎችን በፍጥነት መፍታትና የሙያ ሥነ-ምግባርን ማስጠበቅ ላይ ትኩረት ሊደረግ እንደሚገባ አስተያየታቸውን አካፍለዋል።

እንዲሁም የተሻለ ውጤት ያስመዘገቡ መ/ቤቶች የተገኙትን ውጤት ለማስቀጠል እና የበለጠ ለማሻሻል እንዲሁም ሌሎች መ/ቤቶች ከእነሱ ተሞክሮ በመውሰድ አፈጻጸማቸውን እንዲያሻሽሉ ያላቸውን ቁርጠኝነት ገልጸዋል።

በመድረኩ የወረዳው አስተባባሪ አካላት፣ የወረዳ አመራሮች፣ የሁሉም ሴክተር መ/ቤቶች የሰው ሀብት አስተዳደርና የልማት ዕቅድ ዳይሬክቶሬት ቡድን መሪዎች፣ ባለሙያዎችና ተወካዮች ተሳትፈዋል።

መድረኩ የሴክተር መ/ቤቶች የሥራ ውጤታማነትን በማጠናከር፣ የሙያ ሥነ-ምግባርንና ተጠያቂነትን በማሳደግ እና የተገልጋይ እርካታን በማሻሻል ለቀጣይ ሥራ ጠንካራ አቅጣጫ በማስቀመጥ ተጠናቋል።

የጨና ወረዳ ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ጽ/ቤት የተሻለ አፈጻጸምን ለማበረታታት ለውጤታማ መ/ቤቶች የዕውቅና ምስክር ወረቀት ሰጠ፤ጨና፣ ነሐሴ 22/2018 ዓ.ም — የጨና ወረዳ ፐብሊ...
28/08/2026

የጨና ወረዳ ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ጽ/ቤት የተሻለ አፈጻጸምን ለማበረታታት ለውጤታማ መ/ቤቶች የዕውቅና ምስክር ወረቀት ሰጠ፤

ጨና፣ ነሐሴ 22/2018 ዓ.ም — የጨና ወረዳ ፐብሊክ ሰርቪስ የሰው ሀብት ልማት ጽ/ቤት የ2018 ዓ.ም የሴክተር መስሪያ ቤቶች የዕቅድ አፈጻጸም ውጤትን መነሻ በማድረግ የዕውቅናና ሽልማት መድረክ አካሂዷል።

መድረኩ በ2018 ዓ.ም በዕቅድ አፈጻጸም የተሻለ ውጤት ያስመዘገቡ የወረዳው ሴክተር መ/ቤቶችን ለማበረታታት፣ የተሻሉ የሥራ ልምዶችን ለማስፋፋትና በቀጣይ የተሻለ አፈጻጸም እንዲመዘገብ ለማነሳሳት ያለመ እንደሆነ ተገልጿል።

በመድረኩ የተሻለ አፈጻጸም ያስመዘገቡ መ/ቤቶች በደረጃ ተለይተው የዕውቅና ምሥክር ወረቀት የተሰጣቸው ሲሆን፥ በዚህም 1ኛ ደረጃ - የጨና ወረዳ ፍርድ ቤት፤ 2ኛ ደረጃ — የጨና ወረዳ ጤና ጥበቃ ጽ/ቤት እና 3ኛ ደረጃ — የጨና ወረዳ አስተዳደር ጽ/ቤት በተቀመጠው መስፈርት መሠረት ደረጃ በመለየት ለመ/ቤቶቹ የዕውቅና ምሥክር ወረቀት መሰጠቱ ተገልጿል።

የጨና ወረዳ ፐብሊክ ሰርቪስ የሰው ሀብት ልማት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ታሪኩ ኃይሌ በበኩላቸው፣ ዕውቅናና ሽልማት ውጤታማ ሠራተኞችና ተቋማትን ለማበረታታት እንዲሁም የተሻለ የሥራ ባህልን ለመገንባት ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል።

አቶ ታሪኩ በተጨማሪም በ2018 ዓ.ም የተመዘገበው አፈጻጸም ለ2019 ዓ.ም የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ መነሻ በመሆኑ፣ ሁሉም መ/ቤቶች የተሰጣቸውን ዕቅድ በጥራትና በተጠያቂነት እንዲፈጽሙ ጠይቀዋል።

በተቀናጀ ዕቅድ፣ በጥራት አፈጻጸምና በተጠናከረ ክትትል የተሻለ የልማት ውጤት ማስመዝገብ እንደሚቻል ተገለጸ፤ጨና፣ ነሐሴ 22/2018 ዓ.ም — የካፋ ዞን ፕላንና ልማት መምሪያ የ2018 በጀት...
28/08/2026

በተቀናጀ ዕቅድ፣ በጥራት አፈጻጸምና በተጠናከረ ክትትል የተሻለ የልማት ውጤት ማስመዝገብ እንደሚቻል ተገለጸ፤

ጨና፣ ነሐሴ 22/2018 ዓ.ም — የካፋ ዞን ፕላንና ልማት መምሪያ የ2018 በጀት ዓመት የዕቅድ አፈጻጸም ግምገማና በ2019 በጀት ዓመት የሴክተሩን ዕቅድ በተመለከተ በቼክ ሊስት የተደገፈ ድጋፋዊ ክትትል በጨና ወረዳ አካሂዷል።

ድጋፋዊ ክትትሉ የወረዳው ፕላንና ልማት ጽ/ቤት የ2018 ዓ.ም የዕቅድ አፈጻጸምን ለመገምገም፣ በሥራ አፈጻጸም የታዩ ጠንካራ ጎኖችን ለማጠናከር፣ ክፍተቶችን ለመለየትና የ2019 ዓ.ም ዕቅድን በተሻለ መልኩ ለመፈጸም አቅጣጫ ለማስቀመጥ ያለመ እንደሆነ ተገልጿል።

በክትትሉ ወቅት ከታዩ ጠንካራ ጎኖች መካከል በወረዳው በሚገኙ ትምህርት ቤቶች የሥነ-ሕዝብ ክበባት ተቋቁመው ሥራ መጀመራቸው ተጠቅሷል። ይህም የሥነ-ሕዝብ ጉዳዮችን በትምህርት ተቋማት ማስረጽና በወጣቱ ትውልድ የሥነ-ሕዝብ ግንዛቤን ማሳደግ ረገድ አዎንታዊ ጅማሮ መኖሩን እንደሚያሳይ ተነግሯል።

በተጨማሪም የሶሺዮ-ኢኮኖሚ መረጃዎች በየሩብ ዓመቱ ከሁሉም ሴክተር መ/ቤቶች ተሰብስበው በወረዳ ካቢኔ ተገምግመውና ከጸደቁ በኋላ ለሚመለከተው ክፍል በወቅቱ የማድረስ ሥራ መከናወኑ እንደ ጠንካራ ጎን ተመልክቷል።

የ2018 ዓ.ም የሴክተር መ/ቤቶች የዕቅድ አፈጻጸምና የ2019 ዓ.ም የሥራ ዕቅድ በጽ/ቤቱ ማኔጅመንት ተገምግሞ ለሚመለከተው ክፍል መላኩም ሌላው አዎንታዊ አፈጻጸም መሆኑ ተገልጿል።

በወረዳው የካፒታል ፕሮጀክቶችን የመከታተልና የመደገፍ ሥራ ተጠናክሮ መቀጠሉን የገመገመው የክትትል ቡድኑ፣ የፕሮጀክቶች ፕሮፋይል በጥራት ተደራጅቶ ለግምገማና ለክትትል ምቹ በሆነ መልኩ መቀመጡንም አድንቋል።

በሌላ በኩል በአንዳንድ ሴክተር መ/ቤቶች የዕቅድና ሪፖርት አዘገጃጀት ጥራት ላይ ክፍተት መኖሩ፣ እንዲሁም ከ2018 እስከ 2022 ዓ.ም ያለው የሴክተር መካከለኛ ዕቅድ አለመኖሩ ለቀጣይ ሥራ መሻሻል ከሚገባቸው ጉዳዮች መካከል ተጠቅሰዋል።

ድጋፋዊ ክትትሉን የመሩት የካፋ ዞን ፕላንና ልማት መምሪያ የልማት ዕቅድና ካፒታል ፕሮጀክት አፈጻጸም፣ ክትትልና ግምገማ ቡድን መሪ አቶ አደም አባዲኮ እንደገለጹት፣ ድጋፋዊ ክትትሉ የታዩ ጠንካራ ጎኖችን በማጠናከርና የታዩ ክፍተቶችን በመፍታት የተሻለ የዕቅድ አፈጻጸም ለማስመዝገብ የሚያግዝ ነው ብለዋል።

የጨና ወረዳ ፕላንና ልማት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ወልደየስ ማለቶ በበኩላቸው፣ በክትትሉ የተለዩ ጠንካራ ጎኖችን በማስቀጠልና ክፍተቶችን በማረም የ2019 ዓ.ም ዕቅድ በተሻለ የሥራ አመራርና በተጠናከረ ክትትል ለመፈጸም ቁርጠኝነት እንዳለ ገልጸዋል።

በመድረኩ የጽ/ቤቱ ማኔጅመንት አካላት በመሳተፍ በዕቅድ አፈጻጸም፣ በሪፖርት አዘገጃጀት፣ በመረጃ አያያዝ፣ በካፒታል ፕሮጀክቶች ክትትልና በ2019 ዓ.ም ዕቅድ ዙሪያ የጋራ ግምገማና ውይይት አድርገዋል።

“አፈሳ አለ” በሚል በማህበራዊ ሚዲያ በሚሰራጩ የሐሰት መረጃዎች ህብረተሰቡ እንዳይረበሽ የጨና ወረዳ ሠላምና ጸጥታ ጽ/ቤት አሳሰበጨና፣ ነሐሴ 22/2018 ዓ.ም — “አፈሳ አለ” በሚል ርዕስ...
28/08/2026

“አፈሳ አለ” በሚል በማህበራዊ ሚዲያ በሚሰራጩ የሐሰት መረጃዎች ህብረተሰቡ እንዳይረበሽ የጨና ወረዳ ሠላምና ጸጥታ ጽ/ቤት አሳሰበ

ጨና፣ ነሐሴ 22/2018 ዓ.ም — “አፈሳ አለ” በሚል ርዕስ ሰሞኑን በማህበራዊ ሚዲያ እየተሰራጩ ያሉ የሐሰትና ያልተረጋገጡ መረጃዎች ህብረተሰቡን ሊያሳስቱና የሰላም ሁኔታን ሊያውኩ ስለሚችሉ፣ ይህን ዓይነት ወሬ የሚያሰራጩ አካላት ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ የጨና ወረዳ ሠላምና ጸጥታ ጽ/ቤት አሳሰበ።

በተለይም ሰሞኑን “አፈሳ አለ” በሚል መልዕክት በማህበራዊ ሚዲያ የሚሰራጩ ወሬዎች ህብረተሰቡ ውስጥ ስጋትና ያለመረጋጋት ሊፈጥሩ እንደሚችሉ ጽ/ቤቱ ገልጿል።

የጨና ወረዳ ሠላምና ጸጥታ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ መኮንን ኃይሌ እንደገለጹት፣ በማህበራዊ ሚዲያ እየተሰራጨ ያለው “አፈሳ አለ” የሚል ወሬ ፈጽሞ ውሸትና የተሳሳተ መረጃ ነው ብለዋል።

አቶ መኮንን አክለውም፣ ህብረተሰቡ ያልተረጋገጠ መረጃን በማመን ሳይሆን መረጃውን ከታማኝ ምንጮች በማረጋገጥ ብቻ እንዲጠቀም አሳስበዋል።

የማይታወቅ መረጃን ሳናጣራ ማሰራጨት በህብረተሰቡ ላይ ስጋት ሊፈጥር እና የሰላም ሁኔታን ሊያውክ ይችላል ያሉት ኃላፊው፣ ሁሉም ዜጋ የመረጃ ኃላፊነትን በመወጣት ያልተረጋገጠ ወሬ ከማሰራጨት እንዲቆጠብ ጠይቀዋል።

በተጨማሪም የሠላምና ጸጥታ ጽ/ቤቱ የህብረተሰቡን ሠላምና ጸጥታ ለማስጠበቅ በተቀናጀ መልኩ እየሠራ መሆኑን ገልጾ፣ ህብረተሰቡም ሰላሙን በመጠበቅ ለሚሰራጩ የሐሰት ወሬዎች ቦታ እንዳይሰጥ ጥሪ አቅርቧል።

Address

Chena
Wacha

Telephone

+251927220264

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የጨና ወረዳ ኮሙኒኬሽን Chena Woreda Communications posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share