21/03/2025
መንግስት ሰላምን ያስቀደመ መሆን አለበት"
የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር)
መጋቢት 11/2017 ዓ.ም (ሰላም ሚኒስቴር) የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) ፓርላማ በመገኘት በፌዴራል መንግስት የ2017 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ግማሽ ዓመት አፈፃፀምን መነሻ በማድረግ ከምክር ቤት አባላት ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች ማብራሪያ በሰጡበት ወቅት እንደተናገሩት መንግስት ሰላምን ያስቀደመ፣ ሰላምን በይፋ የሚናገርና ለሰላም የሚተጋ መሆን እንዳለበት ተናግረዋል፡፡
"ሰላምን የሚያደፈርስ ነገር ሲኖር ግልጽ መመዘኛዎች ያስፈልጉታል ያሉ ሲሆን መንግስት በብቸኝነት ሀይል የመጠቀም ስልጣን ያለው በመሆኑ ዘላቂ ሰላምንና ፍትሀዊነትን ለማረጋገጥ ወደ ግጭት ሊገባ ይችላል" ብለዋል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ "በኢትዮጵያ የመጣው ችግር ፍረጃ ነው። የጠላትና የወዳጅ ፍረጃ ማለት ነው። ይህ ደግሞ ለሰላማዊ ድርድር ቦታ አይሰጥም። ስለሆነም በኃይል ስልጣን የመያዝ አባዜን አምጥቷል። በምርጫ የተመረጠን መንግስት በኃይል ለመጣል የሚሞክሩ ኃይሎች አሉ። እነዚህ አካላት የሚያሰቃዩት እንታገልልሃለን የሚሉትን ህዝብ ነው” ብለዋል፡፡
መንግስት ለሰላም እጁ የተዘረጋ ነው፡፡ በድርድር እና በሰለጠነ መንገድ የሚነሱ ችግሮችን ለመፍታት ሁሌም ቢሆን ዝግጁ መሆኑንም ተናግረዋል፡፡