Kedrallah Ahmed

Kedrallah Ahmed Future will be brightened with PROSPERITY PARTY. Choose PROSPERITY PARTY .

ከአንድ የፌስቡክ ጋደኛዬ ገጽ  ያገኘኋትን የተቋጠረች  ጽሁፍ እነሆ አጋራኋችሁ!የሴኔጋል ተጫዋቾች ተበድለናል ..."ሜዳውን ለቀን እንወጣለን" .. ብለው ፎከሩ። ፕሮፌሽናልነታቸው አውልቀው ጥ...
19/01/2026

ከአንድ የፌስቡክ ጋደኛዬ ገጽ ያገኘኋትን የተቋጠረች ጽሁፍ እነሆ አጋራኋችሁ!

የሴኔጋል ተጫዋቾች ተበድለናል ..."ሜዳውን ለቀን እንወጣለን" .. ብለው ፎከሩ። ፕሮፌሽናልነታቸው አውልቀው ጥለው እንደ ሰፈር ጎረምሳ በብሶት ተውጠው ወደ መልበሻ ቤት ማምራት ጀመሩ። እርግጥ ነው የተሰጠባቸው ፔናሊቲ አጨቃጫቂ ከመሆኑም ሌላ ለአዘጋጇ ሀገር የተሰራ ፌበር ይመስል ነበር።

በዚህ ሁሉ ግርግር ውስጥ ግን የአንድ ተጫዋች ትግስት ፣ ፕሮፌሽናሊዝም ፣ እርጋታና ፣ ምክር የሴኔጋል ተጫዋቾችን ስሜት አረገበ። ሜዳውን ለቀው መውጣታቸው ዋንጫውን ለሞሮኮ ፎርፌ እንዲሰጥ ከማድረግ በተጨማሪ ሴኔጋልን ለከፍተኛ ቅጣት እንደሚያበቃት የተረጋገጠ ነበር።

ይህ እንዳይሆን ተጫዋቾችን አረጋግቶ ወደ ሜዳው መለሳቸው። ፔናሊቲው እንዲመታ አሳመናቸው። የስፖርታዊ ጨዋነት መርህ ፣ የእግር ኳስ ተመልካቾች ክብር ፣ የአፍሪካ እግር ኳስ መድረክ ዝና ፣ የሴኔጋላዊያን ጨዋነት እንዳይጣስ አደረገ።

በእሱ ውሳኔ እየሆነ የነበረው በቅፅበት ተቀየር። ሞሮኮ የተሰጣትን ፔናሊቲ ሳተችው። በተስፋ መቁረጥ ውስጥ ገብተው የነበሩ የሴኔጋል ተጫዋቾች ተነቃቁ .... በተጨማሪ 30 ደቂቃ ጎል አስቆጥረው ከእጃቸው ያፈተለከውን ዋንጫ ዳግመኛ በማሳካት የሴኔጋልን ክብር አረጋገጡ ...

በአፍሪካ ዋንጫ ታሪክ እጅግ አጨቃጫቂው ፣ በድራማ የተሞላው ክስተት ፣ ምንአልባት የሴኔጋል ተጫዋቾች ሜዳውን ለቀው ቢወጡ ኖሮ በፎርፌ ለሞሮኮ ሊወሰን የነበረውን ጥቁር ታሪክ ሻረው።

ሳዲዮ ማኔ በሜዳ ላይ ለሀገሩ ክብር ሁሉንም ነገር ሳይሰሰት ሰጠ ... ከሜዳው ባሻገር ደግሞ በስፖርታዊ ጨዋነት ተግባሩ ዳግመኛ ነገሰ። ጥቁር ዳመና አጥልቶበት የነበረውን ጨዋታ በወጋገን የፀሀይ ነፀብራቅ ለወጠ ...

በእርግጥም እንደ ሳዲዮ ማኔ ያሉ በስነምግባራቸው የላቁ ፣ በስለው የረጉ ፣ የፕሮፌሽናልነት መለኪያ የሆኑ ፣ ከስሜት ይልቅ አስተዋይነት የታደሉ ፣ በክብር የደመቁ ፣ መልካም አርአያነት የተላበሱ ተጫዋቾች ባይኖሩ ኖሮ የእግር ኳስ መድረክ በዚህ ልክ ፈፅሞ አይደምቅም ነበር !!

14/01/2026
29/12/2025
የ G20 ጉባኤ፡ ለኢትዮጵያ ዲፕሎማሲያዊ አቅም መገለጫ።ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ በጆሃንስበርግ እየተካሄደ ባለው የG20 የመሪዎች ጉባኤ ላይ መገኘታቸው ለኢትዮጵያ ታሪካዊ ስኬት ...
24/11/2025

የ G20 ጉባኤ፡ ለኢትዮጵያ ዲፕሎማሲያዊ አቅም መገለጫ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ በጆሃንስበርግ እየተካሄደ ባለው የG20 የመሪዎች ጉባኤ ላይ መገኘታቸው ለኢትዮጵያ ታሪካዊ ስኬት ነው!
ይህ ተሳትፎ ለሀገራችን ብልጽግና እና ዲፕሎማሲያዊ አቅም ከፍተኛ ፋይዳ አለው።
የፖለቲካዊ እና ኢኮኖሚያዊ ተሰሚነት በዓለም ኢኮኖሚ እጣ ፈንታ በሚወሰንበት በዚህ መድረክ ላይ እንደ መሪ መሳተፍ የኢትዮጵያን ተሰሚነት በከፍተኛ ደረጃ ከፍ ያደርጋል።
ጉባኤው የውጭ ኢንቨስትመንትን ለመሳብ እና በዓለም አቀፍ የፋይናንስና የንግድ ሥርዓት ውስጥ ኢትዮጵያ ተጠቃሚ እንድትሆን ወሳኝ ዕድል ይከፍታል።
የሀገራችንን የልማት አጀንዳዎች ከዓለም አቀፍ ተዋናዮች ፍላጎት ጋር በማስተሳሰር ውጤታማ ትብብር ለመፍጠር ያስችላል።
በ G20 መገኘቱ ጠቅላይ ሚኒስትሩ የሀገሪቱን ጥቅም በከፍተኛ ደረጃ እንዲያስጠብቁ እና ኢትዮጵያን ወደ ዓለም አቀፍ የብልጽግና አውታር እንድትቀላቀል መንገድ ይከፍታል።
የኢትዮጵያ አጀንዳዎች ከዓለም አቀፍ ተዋናዮች ጋር የሚያያዙበት ወሳኝ ጊዜ አሁን ነው!

አንጋፋው የታሪክ ተመራማሪ ፕሮፌሰር ላዺሶ ጌ. ዴሌቦ በሕክምና ሲረዱ ቆይተው ዛሬ ህይወታቸው ማለፉን በታላቅ ሀዘን ሰማሁ። ለቤተ-ሰቦቻቸው፣ ለወዳጅ ዘመዶቻቸው መጽናናትን እንዲሰጥልን እመኛለ...
09/11/2025

አንጋፋው የታሪክ ተመራማሪ

ፕሮፌሰር ላዺሶ ጌ. ዴሌቦ

በሕክምና ሲረዱ ቆይተው ዛሬ ህይወታቸው ማለፉን በታላቅ ሀዘን ሰማሁ። ለቤተ-ሰቦቻቸው፣ ለወዳጅ ዘመዶቻቸው መጽናናትን እንዲሰጥልን እመኛለሁ።

Address

Werabele

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Kedrallah Ahmed posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share