Kedrallah Ahmed

Kedrallah Ahmed Future will be brightened with PROSPERITY PARTY. Choose PROSPERITY PARTY .

25/08/2026

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ባለፉት ሦስት አመታት ከ5.1 ቢሊዮን ብር በላይ ዕዳ መመለሱ ተገለጸ።

(ሆሳዕና፣ ነሐሴ 12/2018)፣ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ባለፉት ሦስት ዓመታት ከነበረበት 6.021 ቢሊዮን ብር ዕዳ ውስጥ ከ5 ነጥብ 1 ቢሊዮን ብር በላይ መመለስ መቻሉን የክልሉ ፋይናንስ ቢሮ ገለጸ።

የቢሮ ኃላፊዋ ወ/ሮ ዘይቱና ኢብራሂም ባለፉት ሦስት ዓመታት የክልሉን የዕዳ ቅነሳ ሂደት አስመልክተው በሰጡት ማብራሪያ፣ ክልሉ ሲመሠረት ከፍተኛ የዕዳ ጫና ውስጥ እንደነበር አስታውሰዋል።

በወቅቱም የደመወዝና የማኅበራዊ ዋስትና ክፍያዎችን ጨምሮ መደበኛ ወጪዎችን በወቅቱ መፈጸም አለመቻሉንና የካፒታል ፕሮጀክቶችም በክፍያ ችግር ምክንያት መስተጓጎላቸውን ገልጸዋል።

የዕዳ ጫናውን ካባባሱ ምክንያቶች መካከል ከቀድሞው ክልል የተላለፈ የጥሬ ገንዘብ ብድር፣ የማኅበራዊ ዋስትና ውዝፍ ክፍያዎች፣ በተጠናቀቁና በሂደት ላይ ባሉ ፕሮጀክቶች ላይ የቀረቡ የክፍያ ሰርተፊኬቶች በወቅቱ አለመከፈላቸው እና ከአፈር ማዳበሪያ ግዢ ጋር የተያያዙ የብድር ዕዳዎች እንደሚገኙበት አብራርተዋል።

የዕዳውን ችግር በዘላቂነት ለመፍታት የችግሩን መንስኤና መፍትሔ በጥናት በመለየት “ከዕዳ ነፃ የሆነ ክልል መፍጠር” የሚል ራዕይ ተይዞ ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር ቅንጅታዊ ሥራ መሠራቱን ወይዘሮ ዘይቱና ገልጸዋል።

በዚህም የአገልግሎት አሰጣጥን ማዘመን፣ አስተዳደራዊ ወጪዎችን መቀነስ፣ የማዳበሪያ ግዢና የዕዳ አመላለስ ሥርዓትን ማዘመን እንዲሁም የወጪ ቅነሳ ስትራቴጂና መመሪያዎችን ማዘጋጀት ተችሏል።

በተጨማሪም የበጀትና የጥሬ ገንዘብ አስተዳደር መመሪያዎችን በማዘጋጀትና በመተግበር፣ የተቀናጀ ድጋፍና ክትትል በማድረግ እና የውስጥ ቁጥጥር ሥርዓትን በማጠናከር የዕዳ ቅነሳ ሥራው እንዲጠናከር መደረጉን ጠቁመዋል።

ኃላፊዋ እንዳሉት፣ ቀሪ ዕዳውንም ለማጠናቀቅ በትኩረት በመሥራት ላይ ሲሆን፣ ወደፊት አዲስ ዕዳ እንዳይከማች ግልጽ አቅጣጫ ተቀምጦ እየተሠራ ነው።

በጁሲ ጥላሁን
ለተጨማሪ መረጃ ‼️

📌 በዌብሳይት https://www.cergcab.et/

📌በቴሌግራም https://t.me/CERGCAB

📌 በፌስቡክ https://www.facebook.com/profile.php?id=100070605291100&mibextid=ZbWKwL

📌 በቲውተር https://twitter.com/CabCerg2678

📌 በቲክቶክ tiktok.com/

📌 በዩቲዩብ https://youtube.com/?si=Ipdg3R3A3hpPQEUV

📌 በኢንስታግራም https://www.instagram.com/cergcab/profilecard/?igsh=MWNseXBlaW05dnM3MA==

ምርጫችሁ ስላደረጋችሁን እናመሰግናለን !!

25/08/2026

ባለፉት ሶስት አመታት የክልሉ ገቢ የመሰብሰብ አቅም እያደገ መምጣቱን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ገቢዎች ቢሮ አስታወቀ

(ሆሳዕና፣ነሐሴ 14/2018) በክልሉ ኢኮኖሚው የሚያመነጨውን ገቢ ወደ ላቀ ደረጃ ለማሳደግ በልዩ ትኩረት እንደሚሰራም ተመላክቷል

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ገቢዎች ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ቀመሪያ ረሻድ እንደገለጹት ባለፉት ሶስት አመታት የክልሉ ገቢ የመሰብሰብ አቅም እያደገ መምጣቱን ተናግረዋል።

እንደ ኃላፊዋ ገለጻ በ2016 በጀት ዓመት በክልሉ 10 ቢሊየን 883 ሚሊየን 846 ሺ 092 ብር ገቢ የተሰበሰበ ሲሆን በ2017 በጀት ዓመት ደግሞ 16 ቢሊየን 980 ሚሊየን 834 ሺ 702 ብር ገቢ ተሰብስቧል።

በ2018 በጀት ዓመት 26 ቢሊየን 636 ሚሊየን 151 ሺ 946 ብር መሰብሰቡን የተናገሩት ኃላፊዋ በ2019 በጀት ዓመት ደግሞ ብር 35 ቢሊየን 251 ሚሊየን 830 ሺህ ብር ገቢ ለመሰብሰብ ስለመታቀዱም አስረድተዋል።

የክልሉ ገቢ በየአመቱ እድገት እንዲያሳይ የክቡር ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)የቅርብ ክትትል እና ድጋፍ የጎላ አበርክቶ እንደነበረውም ኃላፊዋ በአብነት ጠቅሰዋል።

በክልሉ የተከናወኑ የህግ ማስከበር፣ የግብር ከፋዩን ንቃተ-ህሊና የማሳደግ እና አሰራርን የመዘመን ስራዎች ለገቢው እድገት አዎንታዊ አስተዋፅኦ አድርገዋል።

ግብር ከፋዩ ማህበረሰብ ግብር የመክፈል ባህሉ እንዲዳብር ሰፊ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራዎች ስለመከናወናቸውም ኃላፊዋ አብራርተዋል።

ባለፉት ዓመታት በተደረገ የተቀናጀ ጥረት የክልሉ ገቢ በሚፈለገው ደረጃ እንዲሰበሰብ አስችሏል ያሉት ኃላፊዋ በዘርፉ የላቀ ውጤት ለማስመዝገብ በህግ ማስከበር ረገድ የተጀመረው ጥረት ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም ጠቁመዋል።

በሴክተሩ የተመዘገበው ውጤት ክልሉ በራስ አቅም ለመልማት የሚያደርገውን ጉዞ የሚያፋጥን መሆኑን የገለጹት ወ/ሮ ቀመሪያ በቀጣይም ዘርፉን ወደ ላቀ ደረጃ ማሳደግ የሚያስችሉ ስትራቴጂዎች ተቀርጸው እየተሰራ ነው።

ኢኮኖሚው የሚያመነጨውን ገቢ በአግባቡ መሰብሰቡ የክልሉን የልማት እና የመልካም አስተዳደር ፍላጎቶች በራስ አቅም ለመሸፈን ያስችላል ብለዋል።

የሚሰበሰበው ገቢ መንገድ፣ ትምህርት ፣ ጤና ተቋማት ፣ የንጹህ መጠጥ ውሃ እና ሌሎች በርካታ የልማት ፕሮጀክቶችን ለመገንባት እና ለማስፋፋት የላቀ ጠቀሜታ እንዳለውም ኃላፊዋ ተናግረዋል።

መንግስት በሚያካሂዳቸው የተለያዩ የልማት ፕሮጀክቶች እና ለግል ዘርፉ በሚያደርገው የድጋፍ ስራዎች ለዜጎች ሰፊ የስራ እድል እንደሚፈጥርም አብራርተዋል።

ከኢኮኖሚ እንቅስቃሴው የሚሰበሰበው ገቢ ዝቅተኛ ገቢ ያላቸውን የህብረተሰብ ክፍሎች የሚደግፉ የማህበራዊ ዋስትና ስራዎች ላይ የሚኖረውን አበርክቶ ወ/ሮ ቀመሪያ አስረድተዋል።

በተስፋዬ መኮንን

ከአንድ የፌስቡክ ጋደኛዬ ገጽ  ያገኘኋትን የተቋጠረች  ጽሁፍ እነሆ አጋራኋችሁ!የሴኔጋል ተጫዋቾች ተበድለናል ..."ሜዳውን ለቀን እንወጣለን" .. ብለው ፎከሩ። ፕሮፌሽናልነታቸው አውልቀው ጥ...
19/01/2026

ከአንድ የፌስቡክ ጋደኛዬ ገጽ ያገኘኋትን የተቋጠረች ጽሁፍ እነሆ አጋራኋችሁ!

የሴኔጋል ተጫዋቾች ተበድለናል ..."ሜዳውን ለቀን እንወጣለን" .. ብለው ፎከሩ። ፕሮፌሽናልነታቸው አውልቀው ጥለው እንደ ሰፈር ጎረምሳ በብሶት ተውጠው ወደ መልበሻ ቤት ማምራት ጀመሩ። እርግጥ ነው የተሰጠባቸው ፔናሊቲ አጨቃጫቂ ከመሆኑም ሌላ ለአዘጋጇ ሀገር የተሰራ ፌበር ይመስል ነበር።

በዚህ ሁሉ ግርግር ውስጥ ግን የአንድ ተጫዋች ትግስት ፣ ፕሮፌሽናሊዝም ፣ እርጋታና ፣ ምክር የሴኔጋል ተጫዋቾችን ስሜት አረገበ። ሜዳውን ለቀው መውጣታቸው ዋንጫውን ለሞሮኮ ፎርፌ እንዲሰጥ ከማድረግ በተጨማሪ ሴኔጋልን ለከፍተኛ ቅጣት እንደሚያበቃት የተረጋገጠ ነበር።

ይህ እንዳይሆን ተጫዋቾችን አረጋግቶ ወደ ሜዳው መለሳቸው። ፔናሊቲው እንዲመታ አሳመናቸው። የስፖርታዊ ጨዋነት መርህ ፣ የእግር ኳስ ተመልካቾች ክብር ፣ የአፍሪካ እግር ኳስ መድረክ ዝና ፣ የሴኔጋላዊያን ጨዋነት እንዳይጣስ አደረገ።

በእሱ ውሳኔ እየሆነ የነበረው በቅፅበት ተቀየር። ሞሮኮ የተሰጣትን ፔናሊቲ ሳተችው። በተስፋ መቁረጥ ውስጥ ገብተው የነበሩ የሴኔጋል ተጫዋቾች ተነቃቁ .... በተጨማሪ 30 ደቂቃ ጎል አስቆጥረው ከእጃቸው ያፈተለከውን ዋንጫ ዳግመኛ በማሳካት የሴኔጋልን ክብር አረጋገጡ ...

በአፍሪካ ዋንጫ ታሪክ እጅግ አጨቃጫቂው ፣ በድራማ የተሞላው ክስተት ፣ ምንአልባት የሴኔጋል ተጫዋቾች ሜዳውን ለቀው ቢወጡ ኖሮ በፎርፌ ለሞሮኮ ሊወሰን የነበረውን ጥቁር ታሪክ ሻረው።

ሳዲዮ ማኔ በሜዳ ላይ ለሀገሩ ክብር ሁሉንም ነገር ሳይሰሰት ሰጠ ... ከሜዳው ባሻገር ደግሞ በስፖርታዊ ጨዋነት ተግባሩ ዳግመኛ ነገሰ። ጥቁር ዳመና አጥልቶበት የነበረውን ጨዋታ በወጋገን የፀሀይ ነፀብራቅ ለወጠ ...

በእርግጥም እንደ ሳዲዮ ማኔ ያሉ በስነምግባራቸው የላቁ ፣ በስለው የረጉ ፣ የፕሮፌሽናልነት መለኪያ የሆኑ ፣ ከስሜት ይልቅ አስተዋይነት የታደሉ ፣ በክብር የደመቁ ፣ መልካም አርአያነት የተላበሱ ተጫዋቾች ባይኖሩ ኖሮ የእግር ኳስ መድረክ በዚህ ልክ ፈፅሞ አይደምቅም ነበር !!

አንጋፋው የታሪክ ተመራማሪ ፕሮፌሰር ላዺሶ ጌ. ዴሌቦ በሕክምና ሲረዱ ቆይተው ዛሬ ህይወታቸው ማለፉን በታላቅ ሀዘን ሰማሁ። ለቤተ-ሰቦቻቸው፣ ለወዳጅ ዘመዶቻቸው መጽናናትን እንዲሰጥልን እመኛለ...
09/11/2025

አንጋፋው የታሪክ ተመራማሪ

ፕሮፌሰር ላዺሶ ጌ. ዴሌቦ

በሕክምና ሲረዱ ቆይተው ዛሬ ህይወታቸው ማለፉን በታላቅ ሀዘን ሰማሁ። ለቤተ-ሰቦቻቸው፣ ለወዳጅ ዘመዶቻቸው መጽናናትን እንዲሰጥልን እመኛለሁ።

Address

Werabele

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Kedrallah Ahmed posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share