Wolaita Zone Government Communication Affairs Department

Wolaita Zone Government Communication Affairs Department We inform the nation! We allow an information to flow from people to government and from government to the public.

We enhance communication between government and citizens.

የሀዋሳ ከተማ ምክትል ከንቲባና የንግድና ገበያ ልማት መምሪያ ኃላፊ አቶ አገና ኔቶ  የወላይታ  ብሔር ዘመን መለወጫ ጊፋታ በዓል ላይ ለመታደም ከወላይታ ዞን አስተዳደር የተላከላቸውን ጥሪ ተ...
02/09/2026

የሀዋሳ ከተማ ምክትል ከንቲባና የንግድና ገበያ ልማት መምሪያ ኃላፊ አቶ አገና ኔቶ የወላይታ ብሔር ዘመን መለወጫ ጊፋታ በዓል ላይ ለመታደም ከወላይታ ዞን አስተዳደር የተላከላቸውን ጥሪ ተቀብለዋል

​ወላይታ ሶዶ | ነሐሴ 27 ቀን 2018 ዓ.ም

​የወላይታ ብሔር ዘመን መለወጫ የጊፋታ በዓልን ምክንያት በማድረግ የወላይታ ሕዝብ ተወካዮች ከሀዋሳ ከተማ አስተዳደር የሥራ ኃላፊዎች ጋር በዓሉን በጋራ ለማክበር ጥሪ አቀረቡ።

​በመርሃ-ግብሩ የከተማዋ ምክር ቤት አባላት፣ ከፍተኛ የመንግሥት ሥራ ኃላፊዎች እና የሀገር ሽማግሌዎች ተገኝተዋል። የሲዳማና የወላይታ ሕዝቦች ከጥንት ጀምሮ የኖረ ጥልቅ ታሪካዊ ትስስር፣ አብሮነት እና የቆዩ እሴቶች ባለቤቶች መሆናቸው ተመላክቷል፤ ይህን ታሪክ ተሻጋሪ አብሮነት ይበልጥ ለማጠናከርም በዓሉን በጋራ ለማክበር ጥሪው ቀርቧል።

​ለልዑኩ አቀባበል ያደረጉት የሀዋሳ ከተማ ምክትል ከንቲባና የንግድና ገበያ ልማት መምሪያ ኃላፊ አቶ አገና ኔቶ፤ የወላይታና የሲዳማ ሕዝቦች በደስታም ሆነ በሐዘን ጊዜ አብረው የቆዩ መሆናቸውን ገልጸዋል። ይህንን የቆየ እሴት ለማስቀጠልም በሁለቱም ወገን የሚደረጉ ሕዝብ ለሕዝብ ትስስሮች ተጠናክረው መቀጠል እንዳባቸው አጽንኦት ሰጥተዋል።

​የከተማ አስተዳደሩ ከፍተኛ ኃላፊዎች ከወላይታ ዞን አስተዳደርና ሕዝብ ጋር በመሆን ቀኑን በደስታ ማክበራቸው ሕዝባዊ ትስስሩን ይበልጥ ለማጠናከር ሰፊ አስተዋጽኦ እንዳለውም አቶ አገና አክለው ገልጸዋል።

​በአጠቃላይ፣ ይህ ዝግጅት ሁለቱ ሕዝቦች ያላቸውን ጠንካራ ማኅበራዊ ትስስርና አንጸባራቂ እሴቶች በድምቀት የሚያሳይ ሆኖ፣ ወደፊትም የጋራ ሰላምና ልማት ሥራዎችን አጠናክሮ ለመቀጠል ትልቅ ድርሻ የሚኖረው መሆኑ ተገልጿል።
#ሀዋሳ ከተማ መንግሰት ኮሙኒኬሽን

‎ከተረጂነት ወደ ምርታማነት በምደረገው ጥረት የዝንጅብል ምርት ከፍተኛ አስተዋጽኦ የሚያበረክት ሀብት በመሆኑ ልዩ ትኩረት መስጠት እንደሚገባ ተመላከተ ‎‎ወላይታ ሶዶ፤ነሐሴ 27/2018 የወላ...
02/09/2026

‎ከተረጂነት ወደ ምርታማነት በምደረገው ጥረት የዝንጅብል ምርት ከፍተኛ አስተዋጽኦ የሚያበረክት ሀብት በመሆኑ ልዩ ትኩረት መስጠት እንደሚገባ ተመላከተ

‎ወላይታ ሶዶ፤ነሐሴ 27/2018 የወላይታ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት አመራሮች በቦምቤ ከተማ በማህበር በተደራጁ ወጣቶች በሶፋት እየተመረተ ያለውን የዝንጅብል ማሳን ጎብኝተዋል።

‎ዝንጅብል ለሀገራችን ብሎም አካባቢያችን የውጭ ምንዛሬ ከሚያስገኙ የቅመማ ቅመም ሰብሎች መካከል የሚጠቀስ ነው።

‎በሀገራችን ዝንጅብል በብዛት የሚመረትባቸው አካባቢዎች በወላይታ ዞን ቦሎሶ አከባቢው ግንባር ቀደም የሚጠቅስ መሆኑን ተገልጿል።

‎የአከባቢው ወጣቶች መንግስት ያመቻቸውን የስራ ዕድልን በመጠቀም በስፋት ዝንጅብል እያመረቱ መሆናቸውን አመራሮች ተመልክተዋል።

‎ይህም ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ለማሸጋገር በሚደረገው ጥረት ትልቅ ሀብት መሆኑን ተመላክቷል።

‎ወጣቶች የዞኑ አስተዳደር የውሃ ፓምፕ ባደረገው ድጋፍ ቀጣይ የተለያዩ ጓሮ አታክልት ለማምረት ፍላጎት እንዳለቸውም ገልጸዋል።

‎ከዝንጅበል ምርቱ ያልተጠቀመነው እምቅ አቅም ይበልጥ ለመጠቀምና ምርታማነትን ለማሳደግ የሚያሳድጉ ቴክኖሎጂዎችን እና በሽታን የሚቋቋሙ ዝርያዎች በአግባቡ መጠቀምና ማስፋፋት እንደሚገባም ተመላክቷል።

‎ባለፉት ዓመታት ዝንጅብል ምርት "የዝንጅብል ባክቴሪያል ዊልት" በተሰኘ በሽታ ምክንያት ከፍተኛ ጉዳት ደርሶበት የምርት መጠኑ እንዲቀንስ መደረጉንም ይታወሳል።

‎በጉብኝቱ የወላይታ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ ዶ/ር አማረ አቦታ፣ የዞኑ ፖለቲካና ህዝብ ግንኙነት ዘርፍ ኃላፊ አቶ መስፍን ቶማስ፣ የዞኑ አደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ ወ/ሮ ሰላማዊት ሳሙኤልን ጨምሮ የዘርፍ አመራሮች፣ የዞን ማዕከል ብልፅግና ህብረት ሰብሳቢዎች እና የወረዳና ከተማ ቅ/ጽ/ቤት አመራሮች ተገኝተዋል።

"የበጎ ፈቃድ ስራው የተቸገሩ ወገኖችን ህይወት በሚታደግ እና ህዝባዊ አጋርነትን በሚያጠናክር መልኩ ተጠናክሮ መቀጠል አለበት።"- አቶ ገብረመስቀል ጫላ
02/09/2026

"የበጎ ፈቃድ ስራው የተቸገሩ ወገኖችን ህይወት በሚታደግ እና ህዝባዊ አጋርነትን በሚያጠናክር መልኩ ተጠናክሮ መቀጠል አለበት።"- አቶ ገብረመስቀል ጫላ

‎የወላይታ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት አመራሮች አጆራ መንትያ ፏፏቴዎችን ጎበኙ‎‎ወላይታ ሶዶ፤ነሐሴ 27/2018 ዓ.ም የወላይታ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት አመራሮች አጆራ መንትያ ፏ...
02/09/2026

‎የወላይታ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት አመራሮች አጆራ መንትያ ፏፏቴዎችን ጎበኙ

‎ወላይታ ሶዶ፤ነሐሴ 27/2018 ዓ.ም የወላይታ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት አመራሮች አጆራ መንትያ ፏፏቴዎችን ጎብኝተዋል።

‎የወላይታ ዞን አስተዳደር "ከአቧራ ወደ አሻራ" በሚል ዕሳቤ በዞኑ የሚገኙ የቱሪዝም ቦታዎችን የማልማትና የማስተዋወቅ እንዲሁም ለጎብኚዎች ምቹ የማድረግ ስራ እየሰራ ይገኛል።

‎ከዚህም አጆራ መንትያ ፏፏቴዎች እንዱ ሲሆን በአጭር ጊዜ ውስጥ ለማጠናቀቅ ልዩ ትኩረት በመሰጠት እየተሰራ ይገኛል።

‎በወላይታ ዞን በቱሪስት መስህብነት ከሚታወቁ ቦታዎች መካከል አጆራ መንትያ ፏፏቴዎች በዋናነት የሚጠቀሱ ሲሆኑ እጅግ ውብና ማራኪ የሆኑና የአገር ውስጥና የውጭ አገር ቱሪስቶች ቀልብ የሚስቡ ናቸው።

‎የአጆራ መንትያ ፏፏቴዎች በወላይታ ዞን በቦምቤ ከተማ አስተዳደር አጆራ ቀበሌ የሚገኝ ተፈጥሮአዊ የቱሪስት መስህብ ነው።

‎ይህ ውብ የሆነው የተፈጥሮ መስህብ ከአዲስ አበባ በሆሳዕና 320 ኪ.ሜ በሻሸመኔ በኩል ደግሞ 436 ኪ.ሜ፣ ከወላይታ ሶዶ በ56 ኪ.ሜ ርቀት ላይ ይገኛል፡፡

‎አጆራ ፏፏቴዎች ከ170 ሜትር ቁልቁል በሚምዘገዘግ ሶኬ እና ከ210 ሜትር ቁልቁል በሚንደረደር አጃንቾ ከሚባሉ ትላልቅ ወንዞች የሚፈጠሩ መንትያ ፏፏቴዎች ናቸው፡፡

‎ፏፏቴዎቹ መሬት ላይ አርፈው ተዋሕደው ከ300 ሜትር ያህል አብሮነት ጉዞ በኋላ ቡቡቃ የሚባል ሌላ ፏፏቴ ፈጥረው ወደ ኦሞ ወንዝ ይቀላቀላሉ፡፡

‎የሁለቱም ወንዞች መነሻ ከወላይታ ዋላጫ ጫሪያ ከሚባል ሥፍራ ሲሆን በአጠቃላይ ሶኬ ወንዝ ከመነሻው ጀምሮ በወላይታና ካንባታ ዞን/ ማዕከላዊ ኢትዮጵያ መካከል እንደ ወሰን የሚያገለግል ወንዝ ነው።

‎ፏፏቴዎቹ ስያሜያቸውን ያገኙት ወንዞቹ ከሚወርዱበት ትልቅ ገደል ውስጥ ለረዥም ጊዜ ሲኖሩ ከነበረው አጆራ ተብሎ ከሚጠሩ ጎሣዎች ስያሜ እንደሆነ አፈ ታሪክ ያስረዳል፡፡

‎የተለያዩ የዱር እንስሳት በተለይም ጉሬዛ፣ ድኩላ፣ ከርከሮ፣ ዝንጆሮ፣ አነር፣ አጋዘን፣ ጦጣ እና ሌሎች የዱር እንስሳትን ጨምሮ የተለያዩ የአዕዋፋትና የተፈጥሮ የዕፅዋት ዝሪያዎች የሚገኙት ሲሆን ለምግብነት የሚያገለግሉ ስራስር ምግቦች ቦይና እና የሐረግ ቦዬ ተክሎች በብዛት ይገኙበታል።

‎በጉብኝቱ የወላይታ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ ዶ/ር አማረ አቦታ፣ የዞኑ ፖለቲካና ህዝብ ግንኙነት ዘርፍ ኃላፊ አቶ መስፍን ቶማስ፣ የዞኑ አደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ ወ/ሮ ሰላማዊት ሳሙኤል፣ የአረካ ከተማ ከንቲባ ኢ/ር ጥበቡ ሳሙኤልን ጨምሮ የዘርፍ አመራሮች፣ የዞን ማዕከል ብልፅግና ህብረት ሰብሳቢዎች እና የወረዳና ከተማ ቅ/ጽ/ቤት አመራሮች ተገኝተዋል።

የቡርጂ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ትንሳኤ ዮሐንስና የዞኑ መንግሥት ኮሚንኬሽን አገልግሎት ኃላፊ አቶ ካሳ አለማየሁ የወላይታ ብሔር ዘመን መለወጫ"ጊፋታ" በዓል ላይ እንዲታደሙ ለዞኑ የቀረበላቸ...
02/09/2026

የቡርጂ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ትንሳኤ ዮሐንስና የዞኑ መንግሥት ኮሚንኬሽን አገልግሎት ኃላፊ አቶ ካሳ አለማየሁ የወላይታ ብሔር ዘመን መለወጫ"ጊፋታ" በዓል ላይ እንዲታደሙ ለዞኑ የቀረበላቸውን ጥሪ ተቀብለዋል።

‎በወላይታ ዞን የኢኖቬሽንና ተክኖሎጂ መምሪያ ኃላፊ አቶ አበራ አሉላ የተመራ ልኡካን ቡድን ከወንድም ወላይታ ህዝብ "በጊፋታ " በዓል ላይ እንዲታደሙ የቀረበላቸውን ጥሪ የወንድም ቡርጂ ህዝብ በአክሮት መቀበሉን ተናግረዋል።

‎የጊፋታ በዓል በዩኔስኮ የማይዳሰስ ቅርስ ሆኖ የተመዘገበበት ማግስት መሆኑን የዘንድሮውን በዓል ልዩ እንደሚያደርግ በመጠቆም የበዓሉ አከባበር ባህላዊ እሴቶችን ከማስተዋወቅና ከማስጠበቅ ባለፈ ለቀጣዩ ትውልድ ለማስተላለፍ ያለው ሚና ከፍተኛ መሆኑ ተመላክቷል።

‎በዚህም መሠረት “የጊፋታ ብሔረሰባችን ረጅም ዘመን” በሚል መሪ ቃል የብሔረሰቡ ዘመን መለወጫ የጊፋታ በዓል በመጪው መስከረም 10/2019 ዓ.ም በወላይታ ሶዶ ከክልሉና ከሌሎች ክልሎች እንግዶች ጋር በጋራ በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል።

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ዋና ኦዲተር መ/ቤት ከወላይታ ዞን አስተዳደር የቀረበለትን የ "ጊፋታ " በዓል ጥሪ ተቀበለየደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ዋና ኦዲተር መ/ቤት ከወላይታ ዞን አስተዳደር የተላከ...
02/09/2026

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ዋና ኦዲተር መ/ቤት ከወላይታ ዞን አስተዳደር የቀረበለትን የ "ጊፋታ " በዓል ጥሪ ተቀበለ

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ዋና ኦዲተር መ/ቤት ከወላይታ ዞን አስተዳደር የተላከውን የወላይታ ብሔረሰብ የዘመን መለወጫ "ጊፋታ " ክብረ በዓል ጥሪ ደብዳቤ ተቀብሏል።

ከወላይታ ዞን አስተዳደር የተላከውን የጥሪ ደብዳቤ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ዋና ኦዲተር መ/ቤት ዋና ኦዲተር አቶ ኢዮብ ዋቴ ተቀብለዋል:: ኃላፊው ለተደረገላቸው ግብዣ በተቋሙ ስም ለወላይታ ዞን አስተዳደር ምስጋናቸውን አቅርበዋል::

የ​"ጊፋታ " በዓል መስከረም 10 /2019 ዓ.ም እሁድ ዕለት በወላይታ ዞን ሶዶ ከተማ በልዩ ልዩ ኩነቶች በድምቀት ይከበራል።

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ንግድና ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ  ኃላፊ ወ/ሮ ሰናይት ሰለሞን የወላይታ ዞን በ2019 ዓ.ም ለሚያከብረው የወላይታ ብሔር ዘመን መለወጫ ክብረ በዓል "ዮዮ ጊፋታ "  ያቀ...
02/09/2026

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ንግድና ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ሰናይት ሰለሞን የወላይታ ዞን በ2019 ዓ.ም ለሚያከብረው የወላይታ ብሔር ዘመን መለወጫ ክብረ በዓል "ዮዮ ጊፋታ " ያቀረበውን የተሳትፎ ጥሪ ተቀበሉ።

‎ነሀሴ 27/2018 ዓ.ም

‎የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ንግድና ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ሰናይት ሰለሞን የወላይታ ዞን "የጊፋታ ብስራቶች ፤ ለህዝባችን ከፍታ!!" በሚል መሪ ቃል በ2019 ዓ.ም ለሚያከብረው የወላይታ ብሔር ዘመን መለወጫ ክብረ በዓል "ዮዮ ጊፋታ " ጥሪን ተቀብለዋል።

‎በዓሉ መስከረም 10/2019 ዓ.ም በወላይታ ሶዶ ስታዲዬም በደማቅ ስነ-ስርዓት ይከበራል።

‎የወላይታ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት አመራሮች በግንባታ ላይ የሚገኘውን የወላይታ ሶዶ አለምአቀፍ አየር ማረፊያን ጎበኙ‎‎ወላይታ ሶዶ፤ነሐሴ 27/2018 የወላይታ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ቅ...
02/09/2026

‎የወላይታ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት አመራሮች በግንባታ ላይ የሚገኘውን የወላይታ ሶዶ አለምአቀፍ አየር ማረፊያን ጎበኙ

‎ወላይታ ሶዶ፤ነሐሴ 27/2018 የወላይታ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት አመራሮች በግንባታ ላይ የሚገኘውን የወላይታ ሶዶ አለምአቀፍ አየር ማረፊያን ጎብኝተዋል።

‎የወላይታ ሶዶ አለምአቀፍ አየር ማረፊያ በተቀመጠው ጊዜ ገደብ እንዲጠናቀቅ በልዩ ትኩረት እየተሰራ መሆኑንም አመራሮች ተመልክተዋል።

‎አየር ማረፊያው በህብረተሰቡ ዘንድ ለዘመናት ጥያቄ ሆኖ መቆየቱ የሚታወቅ ሲሆን ብልፅግና ፓርቲ የሚመራው መንግስት ምላሽ አግኝተው ግንባታው እየተፋጠነ ይገኛል።

‎አየር ማረፊያው ለአከባቢው እና ለአጎራባች ህብረተሰብ የሚሰጠው ፋይዳ የጎላ መሆኑንም ተመላክቷል።

‎በጉብኝቱ የወላይታ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ ዶ/ር አማረ አቦታ፣ የዞኑ ፖለቲካና ህዝብ ግንኙነት ዘርፍ ኃላፊ አቶ መስፍን ቶማስ፣ የዞኑ አደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ ወ/ሮ ሰላማዊት ሳሙኤል፣ የአረካ ከተማ ከንቲባ ኢ/ር ጥበቡ ሳሙኤልን ጨምሮ የዘርፍ አመራሮች፣ የዞን ማዕከል ብልፅግና ህብረት ሰብሳቢዎች እና የወረዳና ከተማ ቅ/ጽ/ቤት አመራሮች ተገኝተዋል።

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ባህልና ስፖርት ቢሮ በወላይታ ብሔር  የዘመን መለወጫ  በዓል ጊፋታ ላይ  እንዲቀርብ በዞኑ የቀረበለት የክብር ጥሪ ተቀበለ።ጊፋታ በዩኔስኮ( UNESCO) ተመዝግቦ የመ...
02/09/2026

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ባህልና ስፖርት ቢሮ በወላይታ ብሔር የዘመን መለወጫ በዓል ጊፋታ ላይ እንዲቀርብ በዞኑ የቀረበለት የክብር ጥሪ ተቀበለ።

ጊፋታ በዩኔስኮ( UNESCO) ተመዝግቦ የመጀመሪያውን በዓል በመስከረም 10/2019 ዓ.ም አደባባይ ላይ የሚከበር ሲሆን በዚህ በዓል የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ባህልና ስፖርት ቢሮ እንደምሳተፍ የቢሮው ኃላፊ አቶ ኦላዶ ኦሎ ገልፀዋል።

ቢሮው እንደ በዓሉ ባለበት የህዝቡን ቱባ ባህል ተጠብቆ እንዲከበር ተቋማዊ ድርሻውን እየተወጣ መሆኑንም ኃላፊው ገልፀዋል።

አቶ ኦላድ ኦሎና የቢሮው ሁለት ዋና ዘርፍ ኃላፊዎች ከወላይታ ዞን አስተዳደር የተላከላቸውን ጥሪ በደስታ ተቀብለዋል።

‎የወላይታ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ከዘርፎችና መዋቅሮች ጋር የግብ ስምምነት ተፈራረመ‎‎ወላይታ ሶዶ፤ነሐሴ 27/2018 የወላይታ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ቀጣይ በ2019 በጀት ...
02/09/2026

‎የወላይታ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ከዘርፎችና መዋቅሮች ጋር የግብ ስምምነት ተፈራረመ

‎ወላይታ ሶዶ፤ነሐሴ 27/2018 የወላይታ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ቀጣይ በ2019 በጀት ዓመቱ የሚሰሩ ተግባራት ዙሪያ ከዘርፎች እና ከወረዳና ከተማ አስተዳደር ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤቶች ጋር የግብ ስምምነት ተፈራርመዋል።

‎የወላይታ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ ዶ/ር አማረ አቦታን ጨምሮ የሁለቱም ዘርፍ አመራሮች ከወረዳና ከተማ አስተዳደር ቅ/ጽ/ቤት ቁልፍ አመራሮች ጋር የግብ ስምምነት ተፈራርመዋል።

‎የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ዋና ዋና ግቦችና ተግባራት ላይ ከመዋቅሮች ጋር የግብ ስምምነት በመፈራረም ቀጣይ አቅጣጫዎችን ተቀምጧል።

‎የግብ ስምምነቱ በ2019 በጀት ዓመት ህዝቡ በየደረጃው ለሚያነሳቸው ጥያቄዎች በሁሉም መስኮች ለመመለስና እንዲሁም የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችንም ለመፍታት ታስቦ የተዘጋጀ ነው።

‎የ2019 የበጀት ዓመት በፓርቲው መሪነት በእያንዳንዱ ዘርፍና በሁሉም ሥራ መስኮች የታቀዱ ተግባራት ለህዝቡ በገባነው ቃል መሰረት ለመመለስ ከፍተኛ ርብርብ የሚደረግበት መሆኑ በማጠቃለያው ተገልጿል።

‎ጠንካራ ፓርቲ ለጠንካራ መንግስትና ለጠንካራ ሀገረ-መንግስት ግንባታ ወሳኝ በመሆኑ የፓርቲውን ተቋማዊ ጥንካሬ ማረጋገጥ ቅድሚያ የሚሰጠው ተግባር እንደሚሆን ተመላክቷል።

‎በተዋረድ የወረዳ/ከተማ ፊት አመራሮች እስከ ቀበሌ ድረስ ለስራዉ አጋዥ ከሚሆኑ ኃይሎች ጋር የግብ ስምምነት በመፈራረም በተቀመጠው ጊዜ ሠሌዳ መሠረት ተግባራት በጥብቅ ዲሲፕሊን መመራት እንዳለባቸውም አጽንኦት ተሰጥቷል፡፡

‎የሕዝቡ የልማትና የመልካም አስተዳደር ጉዳዮችንም ለይቶ በፓርቲ መሪነትና በህዝቡ ተካትፎ ለመፈፀምና ለማስፈጸም መግባባት ላይም ተደርሷል።

Address

Wolaita Zone Administration Building 2nd Floor.
Wolaita Sodo
0465510548

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Wolaita Zone Government Communication Affairs Department posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Wolaita Zone Government Communication Affairs Department:

Shortcuts

Share