16/07/2026
የወልዲያ ከተማ ወረዳ ፍርድ ቤት ማኔጅመንት የ2018 ዓ/ም የ 1 ዓመት የስራ አፈፃፀም ግምገማ ተካሄደ።
ሀምሌ 09 ቀን 2018 ዓ/ም: ወልዲያ
==========================
➖ የወልዲያ ወረዳ ፍ/ቤት ማኔጅመንት በዛሬው ዕለት የ 2018 ዓ/ም የአንድ ዓመት የስራ አፈፃፀም ሪፖርት ግምገማ አድርጓል። ግምገማው በአመቱ ውስጥ የተሰሩ ዋና ዋና ተግባራት ላይ ትኩረት ያደረገ ሲሆን የአንድ ዓመት የስራ አፈፃፀም ሪፖርትም በዝርዝር ቀርቧል ።
✔️በመጀመርያ የተገመገመው የመዝገብ አፈፃፀም ሲሆን በአመቱ ውስጥ፣
👉በወንጀል -616 መዛግብት
👉 በፍትሐብሔር 5882 መዛግብት
በድምሩ #6498 መዛግብት የቀረበ ሲሆን
👉በወንጀል- 590
👉 በፍትሐብሔር- 5506
✅ድምር #ለ6096 መዛግብት ዉሳኔ ተሰጥቷል!!!
✅ አፈፃፀም ከአቅርቦት አንፃር 95% ለማድረስ ታቅዶ 93.81% ተፈፅሟል!!
🪴 ወደሚቀጥለው ዓመት የተላለፉት
🐢ወንጀል 26
🐢ፍትሐብሔር 376
🐢ድምር #402 መዛግብት ተላልፈዋል ።
✅ የባህል ፍ/ቤቶች ማቋቋም እና ስራ ማስጀመር በተመለከተ በከተማ አስተዳደሩ ባሉ 10 ቀበሌዎች የባህል ፍርድ ቤት ሽማግሌ በመምረጥ እና ፀሃፊ በመቀጠርየባህል ፍርድ ቤት ተቋቁሞ ወደ ስራ እዲገቡ የተደረገ ሲሆን ስልጠና በመስጠት ወደ ተሟላ አግልግሎት እዲገቡ ተደርጓል ።
✅ በጀትን አጣጥሞ ግዥ መገዛቱ፡ ለማህበረሰቡ የጧት ጧት ትምህርት ( ግንዛቤ) መስጠቱ: የሰራተኛ ስነምግባር ቁጥጥር ከማድረግ አንፃር፡ ከቴክኖሎጂ ተጠቃሚነት አንፃር ጥሩ ነዉ ወደፊት ተጠናክሮ እንድቀጥል ትኩረት እንድደረግ በማለት ማኔጅመንቱ ተወያይቷል!!!
✔️ማኔጅመንቱ በሌሎች ጉዳዮችም ሰፊ ውይይት በማድረግ በተነሱ ጥያቄዎችና አስተያየቶች በፍ/ቤቱ የእቅድ በጀት ዝግጅት: ክትትል እና ግምገማ ባለሙያ እና በፍ/ቤቱ ፕሬዝዳንት ማብራሪያ ተሰጥቶ ወደፊት ከመላዉ ሰራተኛ ጋር የሚገመገምበትን ጊዜ በመወሰን ተጠናቋል።