Somali regional state vital events registrations agency Dawaa Zone branch

  • Home
  • Kenya
  • Moyale
  • Somali regional state vital events registrations agency Dawaa Zone branch

Somali regional state vital events registrations agency Dawaa Zone branch Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Somali regional state vital events registrations agency Dawaa Zone branch, Dawa zone, Moyale.

ወ/ኩ/ም/መ/ኤጀንሲአዲስ አበባሰኔ 17 /2014 ዓ.ም“ህገ ወጥ ሰነዶችን ለመከላከል ከሚመለከታው ተቋማት ጋር በጋራ መስራት እንደሚገባ ተገለፀ”   የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የወሳኝ ኩ...
24/06/2022

ወ/ኩ/ም/መ/ኤጀንሲ
አዲስ አበባ
ሰኔ 17 /2014 ዓ.ም

“ህገ ወጥ ሰነዶችን ለመከላከል ከሚመለከታው ተቋማት ጋር በጋራ መስራት እንደሚገባ ተገለፀ”

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የወሳኝ ኩነት ምዝገባ እና መረጃ ኤጀንሲ ከሰነዶች ማረጋገጫ ምዝገባ ኤጀንሲ የሰነድ ማጭበርብርን እና ህገወጦችን ለመከላከል በጋራ እየሰሩ መሆኑን የገለፀው ኤጀንሲው ተቋማቱ አጠቃላይ የሚሰጡት አገልግሎቶች በጋራ መስራት አስፈላጊ ነው ተብሏል ፡፡

በዚህም መሰረት ዉጭ ላይ ለሚሰሩ የሰነድ ማጭበርብር ( የፎርጀሪ) ስራ በስፋት በኤጀንሲዎቹ ላይ ችግር እየፈጠረ ያለ በመሆኑ ይህንን ተግባር ለመከላከል በጋራ የአሰራር ስርዓቶችን በመንደፍ አጠቃላይ እየታዩ ያሉትን የፎርጀሪ ስራ የሚያስቀር አሰራርን ዘርግቶ ለመስራት እየተንቀሳቀሰ መሆኑን ገልፀዋል ፡፡
በዛሬዉ እለትም ከሰነዶች ማረጋገጫ ኤጀንሲ ኮሚቴዎች በተገኙበት ውይይት አድርገው በቀጣይ አሁን ባለዉ የቴክሎጂ ግብዓት ተጠቅሞና የሲስተም ስርዓት ዘርግቶ አብሮ ለመስራት ተግባብተዋል ፡፡

የተከበራችሁ የተቋማችን ተገልጋዮችና ባለድርሻ አካላት በሙሉ ከዚህን ቀደም የኢሚግሬሽን ዜግነትና ወሳኝ ኩነት ኤጀንሲ ይባል የነበረው የተቋማችን ስያሜ የፌዴራል መንግስት አስፈፃሚ አካላትን ሥ...
26/04/2022

የተከበራችሁ የተቋማችን ተገልጋዮችና ባለድርሻ አካላት በሙሉ ከዚህን ቀደም የኢሚግሬሽን ዜግነትና ወሳኝ ኩነት ኤጀንሲ ይባል የነበረው የተቋማችን ስያሜ የፌዴራል መንግስት አስፈፃሚ አካላትን ሥልጣንና ተግባር ለመወሰን በወጣው አዋጅ 1263/2014 ዓ.ም መሠረት የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት "Immigration and citizenship service" በሚል ስያሜ ተቀይሯል። ስለሆነም ነባሩ የተቋሙ ሎጎ በአዲሱ ስያሜ መሠረት ተሻሽሎ የተዘጋጀ መሆኑን እናሳውቃለን።

በአስደናቂ ደረጃ ላይ የሚገኙት የስራ ኃላፊዎች፣ አስተዳደሩ እና ሁሉም የምዝገባ ኤጀንሲ አባላት እንኳን ለረመዳን ፆም አደረሳችሁ በማለት በመላው አለም ለምትገኙ ሙስሊሞች በተለይም የሶማሌ ማ...
04/04/2022

በአስደናቂ ደረጃ ላይ የሚገኙት የስራ ኃላፊዎች፣ አስተዳደሩ እና ሁሉም የምዝገባ ኤጀንሲ አባላት እንኳን ለረመዳን ፆም አደረሳችሁ በማለት በመላው አለም ለምትገኙ ሙስሊሞች በተለይም የሶማሌ ማህበረሰብ እንኳን አደረሳችሁ።

ረመዳን ሙባረክ🎉🙏🌺

የዓለም ባንክ የወሳኝ ኩነት ምዝገባን ለማሻሻል ለድጋፍና ክትትል  የተለገሰ ድጋፎችን በማስመልከት የተዘጋጀ የርክክብና ዕውቅና የመስጠት ፕሮግራም መካሄዱ ተገለጸየኢሚግሬሽን ዜግነት አገልግሎት...
15/03/2022

የዓለም ባንክ የወሳኝ ኩነት ምዝገባን ለማሻሻል ለድጋፍና ክትትል የተለገሰ ድጋፎችን በማስመልከት የተዘጋጀ የርክክብና ዕውቅና የመስጠት ፕሮግራም መካሄዱ ተገለጸ
የኢሚግሬሽን ዜግነት አገልግሎት ለክልልና ከተማ መስተዳደሮች የወሳኝ ኩነት ምዝገባ ስራን ለመደገፍ የአለም ባንክ ፕሮጀክት የተለገሱ ተሸከርካሪዎችን ለክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች የርክክብና ዕውቅና የመስጠት ፕሮግራም በዛሬው ዕለት መጋቢት 5 ቀን 2014 ዓ.ም በኢንተርኮንትኔንታል ሆቴል ተካሂዷል፡፡
የዕለቱ የክብር እንግዳ የነበሩት የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ሹመቴ ግዛው የወሳኝ ኩነት ምዝገባ ከሌላው የመረጃ ምዝገባ ለየት የሚያደርገው ክቡር የሆነውን የሰው ልጅ መረጃ መያዙ መሆኑን ገልፀው አንድን መረጃ መረጃ የሚያሰኘው ምስጥራዊነቱ ሲጠበቅ፣ትስስር ሲኖረውና በወቅቱ ሲገኝ መሆኑን አሳውቀዋል።
በሌላ በኩል በዕለቱ ተገኝተው የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት ክቡር አቶ ብሩህተስፋ መሉጌታ የኢሚግሬሽን ዜግነት አገልግሎት ዋና ዳርሬክተር እንዳሉት የወሳኝ ኩነት ምዝባ አሁን ካለበት የማንዋል የምዝገባ ሂደት በመላቀቅ ዘመናዊ ቴክኖሎጂን በመጠቀም የምዝገባ ስረዓቱን ቀልጠፋና ውጤተማ በማድረግና የምዝገባ ጥረቱን ለማሻሻል ተስፋ የተጣለበት መሆኑን ገልፀዋል። ዳይሬክተሩ አክለውም በሀገር አቀፍ ደረጃ ከሚገኙ በ1380 ቀበሌዎች ላይ የሞባይል ኢትዮጵያ የወሳኝ ኩነት ምዝገባ ስታቲስቲክስ/ME-CRVS/የሙከራ ፕሮጀክት የሚጀመርበት መሆኑን አሳውቀዋል፡፡የME-CRVS የወሳኝ ኩነት ምዝገባ በዘመናዊ መልኩ የሚመዘግብበት ቴክኖሎጂ በዛሬው ዕለት በይፋ ስራ መጀመሩን በክብር አቶ ፍራኦል ጣፋ የኢሚግሬሽን ዜግነት አገልግሎት ም/ዋና ዳይሬክተር ተበስሯል፡፡
በመጨሻም ለክልል የወሳኝ ኩነት ምዝገባ ድጋፍና ክትትል የሚውሉ ተሸከርካሪዎች ቁልፍ የመረካከብ ስነስርዓት በአገልግሎቱ ዋና ዳይሬክተር ክቡር አቶ ብሩህተስፋ ሙሉጌታ አማካኝነት ተከናውኗል፡፡ 1000 የሚሆኑ ያማሐ ሞተር ሳይክሎችና ሌሎች የምዝገባ ግብዓት ቁሳቁሶች ከዚህ ቀደም ለወሳኝ ኩነት ምዝገባ ተግባር የሚውል ለክልሎች ድጋፍ መደረጉ ይታወሳል፡፡

👉ሁሉም ሰው የሚታወቅበት ኢትዮጵያ 💪

Ethiopia where everyone's recognized!!ሁሉም ሰው የሚታወቅበት ኢትዮጵያ
04/03/2022

Ethiopia where everyone's recognized!!
ሁሉም ሰው የሚታወቅበት ኢትዮጵያ

Well come
01/01/2022

Well come

Address

Dawa Zone
Moyale
5508

Telephone

+251915665080

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Somali regional state vital events registrations agency Dawaa Zone branch posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share