01/06/2026
የቶጫ ወረዳ ማህበረሰብ ክፍሎች በሁሉም ምርጫ ጣቢያ ማልደዉ ወጥተዉ እየመረጡ ይገኛሉ
*****************
ዛሬ ግንቦት 24 ቀን በመላው የሀገሪቱ ክፍሎች የሚገኙ ዜጎች የወደ ፊት እጣ ፈንታቸውን ለመወሰን ይህንን ታሪካዊ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ለማካሄድና የዲሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታቸውን ለማፅናት በነቂስ ወጥተው እየመረጡ ይገኛሉ።
በዳዉሮ ዞን ቶጫ ወረዳ ነዋሪዎች በማለዳው ቅዝቃዜ ሳይበግራቸው በዬ ምርጫ ጣቢያ ቀድመው በመገኘት ታሪካዊ አሻራቸውን ለማሳረፍና ለመምረጥ ካርዳቸዉን ይዘዉ እየመረጡና ለመምረጥ ሰልፍ ላይ ይገኛሉ።
በዚህ የምርጫ ጣቢዎች ሂደቱ ስኬታማና ምቹ እንዲሆን ሰፊ ዝግጅት ተደርጓ። መራጮች ወደ ምርጫ ጣቢያው ሲያቀኑ ያለምንም እንግልት ድምጻቸውን መስጠት እንዲችሉ የድምፅ መስጫ ቦታ እና ሳጥኖችን ጨምሮ ሌሎች አስፈላጊ የቁሳቁስ ዝግጅቶች በሚገባ ተሟልተው ድምፅ የመስጠት ስራ በስከት ቀጥሏል።
ቶጫ ኮሙዩኒኬሽን !