Tocha Communications

Tocha Communications This is an official page of Tocha Woreda Government Communication Affairs Office posting any social, economic, cultural and political events of this woreda.

‎የቶጫ ወረዳ ማህበረሰብ ክፍሎች በሁሉም ምርጫ ጣቢያ ማልደዉ ወጥተዉ እየመረጡ ይገኛሉ‎*****************‎‎ዛሬ ግንቦት 24 ቀን በመላው የሀገሪቱ ክፍሎች የሚገኙ ዜጎች የወደ ፊት ...
01/06/2026

‎የቶጫ ወረዳ ማህበረሰብ ክፍሎች በሁሉም ምርጫ ጣቢያ ማልደዉ ወጥተዉ እየመረጡ ይገኛሉ
‎*****************

‎ዛሬ ግንቦት 24 ቀን በመላው የሀገሪቱ ክፍሎች የሚገኙ ዜጎች የወደ ፊት እጣ ፈንታቸውን ለመወሰን ይህንን ታሪካዊ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ለማካሄድና የዲሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታቸውን ለማፅናት በነቂስ ወጥተው እየመረጡ ይገኛሉ።

‎በዳዉሮ ዞን ቶጫ ወረዳ ነዋሪዎች በማለዳው ቅዝቃዜ ሳይበግራቸው በዬ ምርጫ ጣቢያ ቀድመው በመገኘት ታሪካዊ አሻራቸውን ለማሳረፍና ለመምረጥ ካርዳቸዉን ይዘዉ እየመረጡና ለመምረጥ ሰልፍ ላይ ይገኛሉ።

‎በዚህ የምርጫ ጣቢዎች ሂደቱ ስኬታማና ምቹ እንዲሆን ሰፊ ዝግጅት ተደርጓ። መራጮች ወደ ምርጫ ጣቢያው ሲያቀኑ ያለምንም እንግልት ድምጻቸውን መስጠት እንዲችሉ የድምፅ መስጫ ቦታ እና ሳጥኖችን ጨምሮ ሌሎች አስፈላጊ የቁሳቁስ ዝግጅቶች በሚገባ ተሟልተው ድምፅ የመስጠት ስራ በስከት ቀጥሏል።

‎ቶጫ ኮሙዩኒኬሽን !

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) ድምፃቸውን ሰጡየደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)...
01/06/2026

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) ድምፃቸውን ሰጡ

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) በሚወዳደሩበት የምርጫ ክልል በመገኘት ድምፃቸውን ሰጥተዋል።

ርዕሰ መስተዳድሩ የገዥውን የብልፅግና ፓርቲን ወክለው ለክልሉ ምክር ቤት አባልነት እየተወዳደሩ እንደሚገኙ የታወቀ ሲሆን፣ ዛሬ ማለዳ ላይ በተመረጡበት የምርጫ ክልል በመገኘት ነው የመምረጥ መብታቸውን የተጠቀሙት።

ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) ድምፃቸውን ከሰጡ በኋላ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ፤ የክልሉ ህዝቦች በነቂስ ወጥተው በያዙት የመራጭነት ካርድ ለቀጣይ የዕድገትና የተሻለች አገር የሚበጃቸውንና የሚወክላቸውን ፓርቲ እንዲመርጡ ጥሪ አቅርበዋል።

በክልሉ እየተካሄደ ባለው በዚህ ምርጫ ህዝቡ በከፍተኛ መነሳሳት ድምፅ እየሰጠ እንደሚገኝና ሂደቱም በሰላማዊ ሁኔታ እየተከናወነ መሆኑ ተገልጿል ሲል የዘገበው SWMN ነው።

‎በቶጫ ወረዳ የ10 ወራት የገቢ አሰባሰብ አፈጻጸም ግምገማ እና በቀሪ ቀናት በሚከናወኑ ተግባራት ዙሪያ የጋራ ውይይት ተካሄደ።‎‎የቶጫ ወረዳ ገቢዎች ጽህፈት ቤት የ10 ወራት የገቢ አሰባሰብ...
28/05/2026

‎በቶጫ ወረዳ የ10 ወራት የገቢ አሰባሰብ አፈጻጸም ግምገማ እና በቀሪ ቀናት በሚከናወኑ ተግባራት ዙሪያ የጋራ ውይይት ተካሄደ።

‎የቶጫ ወረዳ ገቢዎች ጽህፈት ቤት የ10 ወራት የገቢ አሰባሰብ አፈጻጸም ግምገማ እና በቀሪው የበጀት ዓመት 40 ቀናት ውስጥ በሚሰበሰቡ የገቢ ትኩረት አቅጣጫዎች ዙሪያ ከባለድርሻ አካላት ጋር የጋራ የምክክር መድረክ አካሂዷል።

‎የዉይይት መድረኩን የመሩት የቶጫ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ታምራት ታደሰ እንደጠቆሙት፦የራስን ገቢ በራስ አቅም ማሳደግ ለወረዳው ልማትና መልካም አስተዳደር መረጋገጥ ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል።

‎ባለፉት 10 ወራት የተከናወነው የገቢ አሰባሰብ ስራ የሚበረታታ ቢሆንም፣ ወረዳችን ካለው የገቢ አቅም አንጻር ገና ብዙ መስራት እንደምጠበቅ በማንሳት በቀሪዎቹ 40 ቀናት ውስጥ የተጣለብንን እቅድ ሙሉ በሙሉ ለማሳካት እያንዳንዱ አመራርና ባለሙያ በቁርጠኝነትና ባልተቆጠበ እምቅ አቅሙ መንቀሳቀስ እንዳለበት አሳስበዋል።

‎የቶ/ወ/ብ/ፓ/ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አንድነት ቡንጉዶ በበኩላቸው፣ የገቢ አሰባሰብ ስራን ውጤታማ ለማድረግ የህግ የበላይነትን ማስከበርና የባለድርሻ አካላትን ቅንጅት ማጠናከር እንደሚገባ ጠቁመዉ ፓርቲው የገቢ አቅምን ለማሳደግ የሚደረገውን የተደራጀ እንቅስቃሴ በቅርበት እንደሚከታተልና እንደሚደግፍ ገልጸው፣ የግብር ከፋዩን ማህበረሰብ ግንዛቤ በማሳደግ ረገድ የፖለቲካ አመራሩ ሚና ከፍተኛ መሆን እንዳለበት አጽንኦት ሰጥተዋል።

‎የዳዉሮ ዞን ገቢዎች መምሪያ ከፍተኛ ባለሙያ አቶ በጋሻው ግርማ በበኩላቸው፦በቶጫ ወረዳ የታዩ ጥንካሬዎችንና የታዩ ክፍተቶችን በዝርዝር አቅርበዉ በቀሪዎቹ ቀናት ውስጥ ያሉትን የገቢ አማራጮች አሟጦ ለመጠቀምና የታክስ ስወራን ለመከላከል የሚያስችሉ ስልታዊ አቅጣጫዎችንና የቴክኒክ ድጋፎችን ለተሳታፊዎቹ አብራርተዋል።

‎በመጨረሻም የመድረኩ ተሳታፊዎችና የጽህፈት ቤቱ ባለሙያዎች በቀረበው ሪፖርትና በቀጣይ አቅጣጫዎች ላይ ሰፊ ውይይት ካደረጉ በኋላ፣ የተሰጣቸውን ግብረ-መልስ መሰረት በማድረግ በቀሪዎቹ 40 ቀናት ውስጥ የገቢ እቅዱን 100 በመቶ ለማሳካትና የበጀት ዓመቱን በስኬት ለማጠናቀቅ ቃል በመግባት መድረኩ ተጠናቋል።

‎ዘገባዉ፦የቶጫ ወረዳ የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳች ጽ/ቤት ነዉ።

በቶጫ ወረዳ "ኢትዮጵያ ወደ ተምሳሌት ሀገር" በሚል መሪ ቃል በ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ዙሪያ ከቶጫ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት መምህራን እና ከቶጫ 1ኛና መካከለኛ ደረጃ ብልጽግና ፓርት አባል መምህራ...
27/05/2026

በቶጫ ወረዳ "ኢትዮጵያ ወደ ተምሳሌት ሀገር" በሚል መሪ ቃል በ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ዙሪያ ከቶጫ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት መምህራን እና ከቶጫ 1ኛና መካከለኛ ደረጃ ብልጽግና ፓርት አባል መምህራን ጋር ውይይት ተካሄደ።

‎በቶጫ ወረዳ "ኢትዮጵያ ወደ ተምሳሌት ሀገር" በሚል መሪ ቃል በ7ኛው ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫ ዝግጅት ዙሪያ፣ ከብልጽግና ፓርቲ አባል የቶጫ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት እና ከቶጫ 1ኛና መካከለኛ ደረጃ ት/ቤት መምህራን ጋር ሰፊ የማክሮ-ፖለቲካና የጋራ ግንባታ ውይይት ተካሄደ።

‎በመድረኩ ላይ የተገኙት የደ/ም/ኢ/ህ/ክ/መ/ፐ/ሰ/የሰ/ሀ/ል/ብሮ ም/ኃላፊ እጩ ዶ/ር ገዛኸኝ ገበየሁ እንደጠቆሙት፦መምህራን የነገዋን ተምሳሌት ሀገር የሚገነቡ ትውልዶችን በማፍራት ረገድ ግንባር ቀደም ሚና እንዳላቸው በመጠቆም "ሀገራችን የጀመረችውን የብልጽግና ጉዞ ከግብ ለማድረስና የዴሞክራሲ ስርዓታችንን ለማጠናከር መምህራን የነቃ የፖለቲካ ተሳትፎ ሊኖራቸው እንደሚገባ አሳስበዋል።

‎በተለይም በ7ኛው ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊ፣ ዴሞክራሲያዊና ተዓማኒ ሆኖ እንዲጠናቀቅ መምህራን ማህበረሰቡን በማንቃትና ምሁራዊ ኃላፊነታቸውን በመወጣት ረገድ የበኩላቸውን አስተዋጽኦ ማበርከት እንዳለባቸውም አብራርተዋል።

‎የቶጫ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ታምራት ታደሴ በበኩላቸው፣ በትምህርት ተቋማት ውስጥ የሚሰሩ የፓርቲው አባላት የወረዳውን ልማትና መልካም አስተዳደር ለማረጋገጥ የመሪነት ሚና መጫወት እንዳለባቸው ጠቁመዋል።

‎አክለዉ፦ ዋና አስተዳዳሪዉ በወረዳችን የተጀመሩ የልማት ስራዎችን ለማገዝ፣ የአካባቢውን ሰላም ዘላቂ ለማድረግ እና መጪውን ሀገራዊ ምርጫ በስኬት ለመወጣት ከመምህራን የሚጠበቀውን የነቃ ተሳትፎ መንግስት ሙሉ በሙሉ እንደምደግፍ አሳስበዋል።

‎የቶጫ ወረዳ ትምህርት ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ አፈወርቅ ዮሐንስ ባደረጉት ንግግር፣ በትምህርት ጥራት ዙሪያና በፓርቲው አባላት መተካካት ላይ ሰፊ ማብራሪያ የሰጡ ሲሆን፣ መምህራን በትምህርት ገበታቸው ላይ ውጤታማ ስራ ከመስራት ባለፈ ለሀገራዊና ቀጠናዊ ጥያቄዎች ምላሽ በመስጠት ረገድ ንቁ ተሳታፊ መሆን እንዳለባቸው አጽንኦት ሰጥተዋል።

‎በመጨረሻም በውይይቱ የተሳተፉት የቶጫ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት እና የቶጫ 1ኛና መካከለኛ ደረጃ ት/ቤት መምህራን በሰጡት አስተያየት፣ የቀረቡትን ሰነዶችና የወቅቱን ሀገራዊ ሁኔታ በሚገባ መገንዘባቸውን ገልጸው፣ ለ7ኛው ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫ መሳካትና "ኢትዮጵያን ተምሳሌት ሀገር የማድረግ" ራዕይ እንዲሰምር በትምህርት ክፍላቸውም ሆነ በማህበረሰቡ ውስጥ የበኩላቸውን ኃላፊነት ለመወጣት ዝግጁ መሆናቸውን አረጋግጠዋል።

‎ዘገባዉ፦የቶጫ ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ነዉ።

በቶጫ ወረዳ ቦብ ቀበሌ የሰላም ምልክት የሆነው ነጭ ባንዲራ የማሰቀል ስነ-ስርዓት ተካሄደ‎‎በዳዉሮ ዞን ቶጫ ወረዳ ቦብ ቀበሌ የዘላቂ ሰላምን አስፈላጊነት ለማብሰር እና የህብረተሰቡን አንድነ...
26/05/2026

በቶጫ ወረዳ ቦብ ቀበሌ የሰላም ምልክት የሆነው ነጭ ባንዲራ የማሰቀል ስነ-ስርዓት ተካሄደ

‎በዳዉሮ ዞን ቶጫ ወረዳ ቦብ ቀበሌ የዘላቂ ሰላምን አስፈላጊነት ለማብሰር እና የህብረተሰቡን አንድነት ለማጠናከር ያለመ የሰላም ምልክት ነጭ ባንዲራ የመስቀል ስነ-ስርዓት በድምቀት ተካሂዷል።

‎በስነ-ስርዓቱ ላይ የተገኙት የቶጫ ወረዳ ፖሊስ አዛዥ ም/ኮን/ር ታሪኩ ከበደ ባስተላለፉት መልዕክት፣ ሰላም ለማንኛውም ልማትና እድገት መሰረት መሆኑን አንስተዋል

‎አክለዉም፦ዛሬ የሰቀልነው ነጭ ባንዲራ ተራ ጨርቅ ሳይሆን የወረዳችንን ህዝብ የሰላም ጥማት፣ አብሮነትና እርቅን የሚያሳይ ትልቅ ምልክት መሆኑን በማንሳት ፖሊስ ከህዝቡ ጋር በመቀናጀት ይሄንን ሰላም የማስከበርና የማስቀጠል ስራውን አጠናክሮ እንደምቀጥል አብራርተዋል።

‎የወረዳው ፖሊስ ጽህፈት ቤት የወንጀል መከላከል ዘርፍ ኃላፊ ም/ኢንስፔክተር መብራቱ አደለ ፦ በበኩላቸው፣ ወንጀልን ቀድሞ ለመከላከልና አስተማማኝ ፀጥታ ለመፍጠር የህብረተሰቡ ተሳትፎ ወሳኝ መሆኑን ጠቁመዉ ይህ የሰላም ባንዲራ መውለብለብም እያንዳንዱ የህብረተሰብ ክፍል ለቀበሌው ሰላም የበኩሉን ጠባቂ እንዲሆን ትልቅ የቤት ስራ የሚጥል መሆኑን አብራርተዋል።

‎የወረዳ ፋይናንስ ኢኮኖሚ ል/ጽ/ቤት ም/ኃ አቶ ታሪኩ አለማየሁ እንደጠቆሙት ፦የአካባቢው መረጋጋት ለህዝቡ እለታዊ የልማትና የንግድ እንቅስቃሴዎች መሳካት ቁልፍ ሚና እንዳለው በማንሳት መንግስት ከአካባቢው ማህበረሰብ ጋር በመሆን የጀመራቸውን የሰላም አማራጮች አጠናክሮ እንደሚቀጥልም አረጋግጠዋል።

‎በመጨረሻም የቦብ ቀበሌ ፖሊስ አስተባባሪ ም/ሳጅን ዳንኤል ደሱላ እንደጠቆሙት ፦በቀበሌው ደረጃ ህዝባዊ የፀጥታ መዋቅሩን በማጠናከር ከህዝቡ ጎን በመቆም የተገኘውን ሰላም ዘላቂ ለማድረግ ሌሊትና ቀን እንደሚሰሩ ቃል ገብተዋል።

‎በእለቱ የነጭ ባንዲራ ማውለብለብ ስነ-ስርዓቱ ሲከናወን የአካባቢው ነዋሪዎች፣ የሃገር ሽማግሌዎችና ወጣቶች የተገኙ ሲሆን፣ የተፈጠረውን ሰላም በጋራ ለመጠበቅና ለመንከባከብ ያላቸውን ዝግጁነት በመግለጽ በቀበሌዉ የሠላም አምባሳደር ለሆኑት ለአቶ መለሰ መኩሪ ህዝቡ እዉቅና በመስጠት መድረኩ ተጠናቅቋል።

‎ዘገባዉ የቶጫ ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ነዉ።

"የአካባቢው ፀጥታ አስተማማኝ የሚሆነው በታማኝና በተደራጀ የሰው ኃይል ነው" አቶ ታምራት ታደሰ የቶጫ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ ።‎‎በቶጫ ወረዳ በሕዝብ ተሳትፎ ተመልምለው አገልግሎት በመስጠት ...
26/05/2026

"የአካባቢው ፀጥታ አስተማማኝ የሚሆነው በታማኝና በተደራጀ የሰው ኃይል ነው" አቶ ታምራት ታደሰ የቶጫ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ ።

‎በቶጫ ወረዳ በሕዝብ ተሳትፎ ተመልምለው አገልግሎት በመስጠት ላይ ለሚገኙ 104 የሚሊሻ አባላት ሲሰጥ የቆየው የማጥራት፣ መልሶ ማደራጀትና የደንብ ልብስ ማልበስ ሥነ-ሥርዓት በዛሬው ዕለት በስኬት መጠናቀቁ ተገለጠ።

‎የቶጫ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ታምራት ታደሰ እንደጠቆሙት የአካባቢው ፀጥታ አስተማማኝ የሚሆነው በታማኝና በተደራጀ የሰው ኃይል መሆኑን በማንሳት፣ የአካባቢን ሰላምና ደህንነት በዘላቂነት ለማረጋገጥ የሕዝብ ተሳትፎና የታማኝ ሚሊሻ ሚና ከፍተኛ መሆኑን ገልጸዋል።

‎ዋና አስተዳዳሪው አክለውም፦"ይህ የማጥራትና መልሶ የማደራጀት ሥራ የተከናወነው ሕዝባዊ አመኔታን ይበልጥ ለማጠናከርና የአካባቢያችንን ሰላም አስተማማኝ ለማድረግ ያለመ መሆኑን አብራርተዋል።

‎አዲስ የደንብ ልብስ የለበሳችሁ የሚሊሻ አባላት፣ የተሰጣችሁን የመንግሥትና የሕዝብ አደራ በታማኝነትና በቁርጠኝነት ልትወጡ ይገባል" ሲሉ አሳስበዋል።

‎የቶጫ ወረዳ ሰላምና ፀጥታ ሚሊሻ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ደስታ ደዋና በበኩላቸዉ፣ የደህንነት ስጋቶችን ቀድሞ ለመከላከልና ለሕዝቡ ቀልጣፋ ጥበቃ ለመስጠት የአባላቱ ዝግጁነት በከፍተኛ ደረጃ ላይ እንደሚገኝ ጠቁመዋል።

‎የቶጫ ወረዳ ፖሊስ አዛዥ ምክትል ኮማንደር ታሪኩ ከበደ እንደጠቆሙት፦ሚሊሻው ከፖሊስ ኃይል ጋር በቅርበትና በቅንጅት በመሥራት ረገድ ያለውን ሚና አድንቀው፣ ይሄኛው መልሶ የማደራጀት ሂደት የወንጀል መከላከል ሥራውን ይበልጥ ውጤታማ እንደሚያደርገው ያላቸውን እምነት ገልጸዋል ።

‎የቶጫ ወረዳ ሰላም ፀጥታ ሚልሻ ጽ/ቤት ምልመላና የስልጠና ስራ ሂደት አስተባባሪ መ/አለቃ ግርማ ቡንጉዶ እንደጠቆሙት፦በሰባዊ መብት አጠባበቅ፣በህግ-መንግስት ጽንስ ሀሳብና የጦር መሳሪያ አያያዝና አጠቃቀም ዙሪያ መሰጠቱን አብራርተዉ አደረጃጀቱን ይበልጥ በማጠናከር የሕግ የበላይነትን ለማስከበር በትኩረት እንደሚሠራ ገልጸዋል።

‎በመጨረሻም ሥነ-ሥርዓቱ ለተተኪና ነባር አባላቱ የደንብ ልብስ በማልበስና የወደፊት የሥራ መመሪያ በመስጠት በስከት ተጠናቋል ።

‎ዘገባዉ የቶጫ ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ነዉ።

‎በወረዳዉ የሚገኙ የሕብረተሰብ ክፍሎች ሰላምና ደህንነት ይበልጥ ለማረጋገጥ ይቻል ዘንድ፣ የቶጫ ወረዳ ሰላምና ፀጥታ ሚሊሻ ጽሕፈት ቤት ከተለያዩ 15 ቀበሌዎች ለተውጣጡ 104 የቀበሌ ሚሊሻ ...
25/05/2026

‎በወረዳዉ የሚገኙ የሕብረተሰብ ክፍሎች ሰላምና ደህንነት ይበልጥ ለማረጋገጥ ይቻል ዘንድ፣ የቶጫ ወረዳ ሰላምና ፀጥታ ሚሊሻ ጽሕፈት ቤት ከተለያዩ 15 ቀበሌዎች ለተውጣጡ 104 የቀበሌ ሚሊሻ አባላት የአቅም መገንቢያ ስልጠና መስጠት ጀምሯል።

‎በቶጫ ወረዳ ለ104 የቀበሌ ሚሊሻ አባላት የአቅም መገንቢያ ስልጠና እየተሰጠ ይገኛል።

‎ለሁለት ቀናት በሚቆየው በዚህ ስልጠና ላይ አባላቱ በማኅበራዊ፣ በፖለቲካዊ እና በወታደራዊ ዘርፎች ዙሪያ ሰፊ ግንዛቤ እንደሚያገኙ ተገልጿል

‎በመርሃ-ግብር ላይ ተገኝተዉ ስልጠናዉን ያስጀመሩት የቶጫ ወረዳ ሰላምና ፀጥታ ሚሊሻ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ደስታ ደዋና እንደገለጹት፤ የዚህ ስልጠና ዋና ዓላማ በሚሊሻ አባላቱ ዘንድ ያለውን የአገልግሎት ዝግጁነት ማሳደግና የአካባቢውን ሰላምና ፀጥታ በበሰለ መልኩ ለማስጠበቅ ያለመ መሆኑን አብራርተዋል።

‎አክለዉ ኃላፊ፦ ሚሊሻው ከሕብረተሰቡ ጋር ያለውን ማኅበራዊ ትስስር በማጠናከርና ወቅታዊ የፖለቲካ ሁኔታዎችን በሚገባ በመረዳት ረገድ ስልጠናው ጉልህ ሚና እንደሚኖረውም ገልጸዋል።

‎ሰልጣኞቹም የቀሰሙትን እውቀትና ክህሎት ወደ ተግባር በመቀየር የአካባቢያቸውን ሰላም በንቃት እንዲጠብቁ ተጠቁሟል ።

‎ይህ ስልጠና በሚሊሻ አባላቱ መካከል ያለውን ዝግጁነትና ቅንጅት በማሳደግ የወረዳዉን ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥ ትልቅ አስተዋጽኦ እንዳለዉ ተጠቁሟል ።

‎የቶጫ ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ነዉ።

‎ሻምፒዮኑ አርሰናል ክሪስታል ፓላስን 2ለ1 አሸነፈ‎*****************‎‎ከሁለት አስርት ዓመታት በላይ የዘለቀው የመድፈኞቹ የዋንጫ ጥማት ዛሬ በደመቀ ሁኔታ ተቋጭቷል።‎‎አርሰናል በ...
24/05/2026

‎ሻምፒዮኑ አርሰናል ክሪስታል ፓላስን 2ለ1 አሸነፈ
‎*****************

‎ከሁለት አስርት ዓመታት በላይ የዘለቀው የመድፈኞቹ የዋንጫ ጥማት ዛሬ በደመቀ ሁኔታ ተቋጭቷል።

‎አርሰናል በ38ኛው ሳምንት የመጨረሻ ጨዋታው ክሪስታል ፓላስን 2 ለ 1 በሆነ ውጤት በማሸነፍ የሊጉን የክብር አክሊል ይረከባል።

‎ለአርሰናል በመጀመሪያው የጨዋታ ክፍለ ጊዜ ገብርኤል ጀሱስ የመጀመሪያዋን ግብ አስቆጥሯል፡፡ በሁለተኛው የጨዋታ ክፍለ ጊዜ ማዱኬ ሁለተኛዋን ግብ ከመረብ ላይ አሳርፏል፡፡ ለክሪስታል ፓላስ ብቸኛዋን ግብ ማቴታ ማስቆጠር ችሏል፡፡

‎ቡድኑ እስከ ጨዋታው ፍጻሜ ድረስ ብቃቱን በማስመስከር 2ለ1 ማሸነፉን ተከትሎ የለንደን ጎዳናዎችን በደስታ እና በእልልታ እንዲሞሉ አድርጓል።

‎በሌሎች የዛሬው የመጨረሻ ሳምንት መርሃ ግብሮች ማንቸስተር ሲቲ በአስቶን ቪላ 2 ለ 1 በሆነ ውጤት ሲሸነፍ ፣ ማንቸስተር ዩናይትድ ብራይተንን 3 ለ 0 በሆነ ሰፊ ውጤት ሲረታ፣ ፉልሃም ኒውካስትልን 2 ለ 0 ሲያሸንፍ እንዲሁም ዌስትሃም ሊድስን በ 3 ለ 0 በሆነ ውጤት ቢያሸንፍም ወደታችኛው ሊግ ወርዷል።

‎በሌላ በኩል ሊቨርፑል ከብሬንትፎርድ ጋር 1 ለ 1 ሲለያይ፣ ሰንደርላንድ ቼልሲን 2 ለ 1 በማሸነፍ ያልተጠበቀ ውጤት አስመዝግቧል።

‎ቶተንሃም ኤቨርተንን 1 ለ 0 አሸንፎ በሊጉ ሲቆይ ፣ በርንሌይ ከዎልቭስ እንዲሁም ኖቲንግሃም ፎረስት ከቦርንማውዝ ጋር 1 ለ 1 በሆነ አቻ ውጤት የውድድር ዘመኑን አጠናቀዋል።

‎የቶጫ ወረዳ ትምህርት ጽሕፈት ቤት የ9 ወራት የሥራ አፈጻጸም ግምገማ መድረክ አካሂዷል ።‎‎የቶጫ ወረዳ ትምህርት ጽሕፈት ቤት በ2018 በጀት ዓመት የዘጠኝ ወራት የሥራ አፈጻጸሙን ባለድርሻ...
23/05/2026

‎የቶጫ ወረዳ ትምህርት ጽሕፈት ቤት የ9 ወራት የሥራ አፈጻጸም ግምገማ መድረክ አካሂዷል ።

‎የቶጫ ወረዳ ትምህርት ጽሕፈት ቤት በ2018 በጀት ዓመት የዘጠኝ ወራት የሥራ አፈጻጸሙን ባለድርሻ አካላት በተገኙበት ገምግሟል።

‎በመድረኩ ላይ ባለፉት ዘጠኝ ወራት በትምህርት ተደራሽነት፣በጥራት ማሻሻል፣ በግብዓት አቅርቦትና በትምህርት ቤት መሠረተ ልማት ግንባታ ዙሪያ የተከናወኑ ዋና ዋና ተግባራት የቀረቡ ሲሆን፥ የተመዘገቡ ስኬቶችና ያጋጠሙ ማነቆዎችን በመለየት ሰፊ ውይይት ተደርጎባቸዋል።

‎በሌላ በኩል፦በትምህርት ዘርፉ የተጀመሩ አዎንታዊ ለውጦችን አጠናክሮ ማስቀጠልና የቀሩትን የቤት ሥራዎች በቀሪው የበጀት ዓመት ጊዜ ውስጥ ለማጠናቀቅ መላው የትምህርት ማኅበረሰብ በቁርጠኝነት መንቀሳቀስ እንዳለበት ተጠቁሟል ።

‎በግምገማ መድረኩ ላይ የደ/ም/ኢ/ህ/ክ/መ/ፐ/ሰ/የሰ/ሀ/ል/ብሮ ም/ኃላፊ እጩ ዶ/ር ገዛኸኝ ገበየሁ ቶጫ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ታምራት ታደሰ፣የወረዳው ብ/ፓ/ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አንድነት ቡንጉዶ እና የዳዉሮ ዞን ትምህርት መምሪያ ከፍተኛ ባለሙያ አቶ ቴዎድሮስ ተክለ የቶጫ ወረዳ ትምህርት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አፈወርቅ ዮሐንስን ጨምሮ የወረዳዉ ትምህርት ጽ/ቤት ባለሙያዎች፣ የግልና የመንግስት ትምህርት ቤት ርዕሳነ መምህራንና ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።

‎ዘገባዉ፦የቶጫ ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ነዉ።

‎የቶጫ ወረዳ ፖሊስ ጽ/ቤት ከባለ ሁለት እግር ሞተር አሽከርካሪዎች እና ከባጃጅ ሾፈሮች ጋር በወቅታዊ ነባራዊ ሁኔታዎች ላይ ያቶከረ ዉይይት ማካሄዱ ተገለጸ።‎‎ግንቦት 15/9/2018 ዓ/ም ...
23/05/2026

‎የቶጫ ወረዳ ፖሊስ ጽ/ቤት ከባለ ሁለት እግር ሞተር አሽከርካሪዎች እና ከባጃጅ ሾፈሮች ጋር በወቅታዊ ነባራዊ ሁኔታዎች ላይ ያቶከረ ዉይይት ማካሄዱ ተገለጸ።

‎ግንቦት 15/9/2018 ዓ/ም ቶጫ ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት።

‎የቶጫ ወረዳ ፖሊስ ጽ/ቤት ከባለ ሁለት እግር ሞተር አሽከርካሪዎች እና ከባጃጅ ሾፈሮች ጋር በወቅታዊ ነባራዊ ሁኔታዎች ላይ ያቶከረ ዉይይት አካሂዷል ።

‎በዉይይቱ ላይ የተለያዩ ትራፍክ አደጋ መከላከያ ግንዛቤ ተሰጥቶ ከታርፍ በላይ ማስከፈልና ትርፍ መጫን ፣ሰዓት ዕላፍ ማሽከርከር ዙሪያ ላይ ሰፋ ያለ ዉይይት ተደርጎበታል ።

‎በዉይይት መድረክ ላይ የዳዉሮ ዞን ፖሊስ መምሪያ ከፍተኛ ባሙያን ጨምሮ የወረዳዉ ፖሊስ ማኔጅመንት አካላት ተሳትፈዋል።

‎ቶጫ ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት።

Address

Tocha
Toamasina

Telephone

+251911418197

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Tocha Communications posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Tocha Communications:

Share