Ethiopian Embassy - UAE / AbuDhabi

Ethiopian Embassy - UAE / AbuDhabi Embassy of the Federal Democratic Republic of Ethiopia in Abu Dhabi.
(2)

ማስታወቂያ!በ “Young Future Energy Leaders” ሥልጠና ፕሮግራም ዕድል መሳተፍ ለምትፈልጉ በሙሉበተባበሩት ዐረብ ኤምሬቶች ታዋቂ የሆነው የካሊፋ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ...
26/08/2026

ማስታወቂያ!

በ “Young Future Energy Leaders” ሥልጠና ፕሮግራም ዕድል መሳተፍ ለምትፈልጉ በሙሉ

በተባበሩት ዐረብ ኤምሬቶች ታዋቂ የሆነው የካሊፋ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ በታዳሽ ኃይል፣ በአካባቢ ጥበቃ እና በዘላቂ ልማት ዘርፍ ላይ ትኩረት የሚያደርገውን የ2027 Young Future Energy Leaders የአንድ ዓመት ሥልጠና ፕሮግራም አዘጋጅቷል። ዩኒቨርሲቲ በዚህ ፕሮግራም ላይ የሚሳተፉ ኢትዮጵያውያንን በመመልመል ሂደት ድጋፍ እንድናደርግ ጥያቄ አቅርቦልናል፡፡

የፕሮግራሙ ዋና ዋና ጥቅሞች
• የአንድ ዓመት ሙሉ ሥልጠና፦ የምርምር ፕሮጀክቶች፣ የአመራርነት ሥልጠናዎች እና ከዘርፉ ባለሙያዎች ጋር የሚደረጉ የልምድ ልውውጦች።
• ልዩ የሥራ ዕድል፦ ከጥር 12 እስከ 14 ቀን 2027 (እ.ኤ.አ) በአቡዳቢ በሚካሄደው World Future Energy Summit (WFES) ላይ በመገኘት ከዓለም አቀፍ መሪዎች ጋር የመገናኘት ዕድል።
• ዋና ዋና የትኩረት አቅጣጫዎች፦ የታዳሽ ኃይል፣ የውኃ ደህንነት፣ የቆሻሻ አወጋገድ፣ ዘላቂ ከተሞች እና የአካባቢ አየር ለውጥ እርምጃዎች።

የአመልካቾች መስፈርት
• ዕድሜ፦ ከ20 እስከ 25 ዓመት
• የትምህርት ውጤት (GPA)፦ 3.50 እና ከዚያ በላይ
• የትምህርት ደረጃ፦ የመጀመሪያ ዲግሪ/ማስተርስ በመከታተል ላይ ያለ፣ በቅርቡ የተመረቀ ወይም በዘርፉ የመጀመሪያ ደረጃ የሥራ ልምድ ያለው
• ሌሎች፦ በታዳሽ ኃይል እና ዘላቂ ልማት ላይ ከፍተኛ ፍላጎት ያለው እና እንግሊዝኛ ቋንቋ መናገር/መፃፍ የሚችል።

የማመልከቻ ሂደት

ሙሉ መረጃችሁን ማለትም (ሙሉ ስም፣ የትምህርት ማስረጃ እና ሰርቴፊኬቶች ካሉ፣ ስልክ ቁጥር) ከዛሬ ጀምሮ እስከ ኦገስት 29 ቀን 2026 ድረስ በኤምባሲው ኦፊሴላዊ ኢሜይል አድራሻ [email protected] ይላኩ።

ማስታወሻ፦ ኤምባሲው በተቀመጠው መስፈርት መሰረት ብቁ የሆነ ዕጩዎችን ዝርዝር ለዩኒቨርሲቲው የሚያስተላልፍ ሲሆን የመጨረሻ ተሳታፊዎችን የሚመረጥው ዩኒቨርሲቲው እንደሆነ ለማሳወቅ እንወዳለን፡፡

የጋብቻ ማስታወቂያ
24/08/2026

የጋብቻ ማስታወቂያ

ማስታወቂያ!
19/08/2026

ማስታወቂያ!

AUCTION NOTICE
18/08/2026

AUCTION NOTICE

ማስታወቂያ
16/08/2026

ማስታወቂያ

ጋዜጣዊ መግለጫበሕገ-ወጥ የሰዎች እና የገንዘብ ዝውውር ዙሪያ የተያዘውን አገራዊ አቋምና የሕግ ማስከበር እርምጃዎችን አስመልክቶ ከተባበሩት ዐረብ ኤምሬቶች የኢፌዲሪ ኤምባሲ የተሰጠ መግለጫነሐ...
14/08/2026

ጋዜጣዊ መግለጫ

በሕገ-ወጥ የሰዎች እና የገንዘብ ዝውውር ዙሪያ የተያዘውን አገራዊ አቋምና የሕግ ማስከበር እርምጃዎችን አስመልክቶ ከተባበሩት ዐረብ ኤምሬቶች የኢፌዲሪ ኤምባሲ የተሰጠ መግለጫ

ነሐሴ 8 ቀን 2018 ዓ.ም.

———
በተባበሩት ዐረብ ኤምሬቶች የምትኖሩ ውድ ኢትዮጵያውያን፣ ትውልደ ኢትዮጵያውያን እና የኢትዮጵያ ወዳጆች በሙሉ፦

የኢፌዲሪ መንግሥት በአገራችን የኢኮኖሚ ደህንነት ላይ ከባድ ጉዳት እያደረሱ ያሉ ሕገወጥ ተግባራትንና ሙስናን ለመግታት፣ በተለይም በሕገወጥ የሐዋላ አገልግሎት እና የሰዎች ዝውውር ወንጀሎች ላይ ጥብቅ እርምጃዎችን እየወሰደ ይገኛል። በቅርቡ በመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት በይፋ እንደተገለጸው በእነዚህ ወንጀሎች ላይ በተካሄዱ አገራዊ ምርመራዎች በርካታ ጥፋተኞች ተለይተው ለሕግ እንዲቀርቡ ተደርጓል።

በተባበሩት ዐረብ ኤምሬቶች የሚገኘው የኢፌዲሪ ኤምባሲ ይህንን አገራዊ ጥረት ሙሉ በሙሉ የሚደግፍ ሲሆን እዚህ ኤምሬቶች ውስጥ የሚኖሩ ወገኖቻችንን በማታለል በሕገ-ወጥ የገንዘብ ዝውውር እና በደላሎች አማካይነት በሰዎች ዝውውር ወንጀል ላይ የተሰማሩ አካላትን እንቅስቃሴ በቅርበት በመከታተል ላይ ይገኛል።

በቅርቡ በኢፌዲሪ ፌደራል ፖሊስ እና በዱባይ ፖሊስ አጋርነት በተካሄደ የተቀናጀ ኦፕሬሽን በእነዚህ ከባድ ወንጀሎች የተጠረጠሩ ዋነኛ ግለሰቦች በተባበሩት ዐረብ ኤምሬቶች ተይዘው ለሕግ እንዲቀርቡ መደረጉ ይታወቃል። ይህ ስኬት ወንጀል ፈጽሞ ከሕግ ማምለጥ እንደማይቻል ማረጋገጫ ነው። ሁለቱ አገራት ወንጀለኞችን አሳልፎ የመስጠት እና የሕግ ትብብር ስምምነት (Agreement on Extradition and Mutual Legal Assistance Agreement) ያላቸው በመሆኑ በኢትዮጵያም ሆነ በኤምሬቶች ወንጀል ፈጽሞ ድንበር ተሻግሮ ማምለጥ አይቻልም።

በኢትዮጵያ እና በተባበሩት ዐረብ ኤምሬቶች መካከል በተፈረመው የሁለትዮሽ የሠራተኛ ስምምነት መሠረት የኤምሬቶች የሥራ ገበያ በሕጋዊ መንገድ ለሚመጡ ኢትዮጵያውያን ክፍት መሆኑ ይታወቃል፡፡ ሆኖም ሕገ-ወጥ ደላሎችና በህጋዊ ሽፋን የሚንቀሳቀሱ ኤጀንቶች የሐሰት የሥራ እድል በመስጠትና ያልተገባ ክፍያ በመቀበል ወገኖቻችንን ለአደጋ ዳርገዋል። በመሆኑም ማንኛውም ዜጋም ሆነ አገር ቤት የሚገኙ ቤተሰቦቻቸው ማንኛውንም የጉዞና የሥራ ቅጥር እንቅስቃሴ ከማድረጋቸው በፊት የሕጋዊነቱን ሁኔታ ማረጋገጥ እንዳለባቸው ኤምባሲው ያሳስባል።

በመሆኑም ኤምባሲው የሚከተሉትን ጥሪዎች ያስተላልፋል፦

1. ለተሳታፊዎች የተሰጠ የመጨረሻ ማጠንቀቂያ፦ በሕገ-ወጥ የሐዋላ ንግድ እና የሰዎች ዝውውር ላይ የተሰማሩ ግለሰቦችና ቡድኖች ቅርብ ክትትል እየተደረገባቸው መሆኑን አውቀው ከእነዚህ ሕገ-ወጥ ተግባራት በአስቸኳይ እንዲቆጠቡ፤ ባይቆጠቡ ግን ከኢትዮጵያ እና ከኤምሬቶች የሕግ ማስከበር አካላት ጋር ያለው ቅንጅት ተጠናክሮ እርምጃው እንደሚቀጥል እናሳውቃለን።

2. ሕጋዊ አሠራርን መጠቀም፦ እያንዳንዱ ወገን ወደ አገር ቤት ገንዘብ ሲልክ ሕጋዊ የባንክ እና ፈቃድ ያላቸው የሐዋላ ተቋማትን ብቻ እንዲጠቀም፣ እንዲሁም ስራ ፈላጊዎችን ሲያመጣ በሕጋዊ የሥራ መስመር ብቻ እንዲጠቀም ጥሪ እናቀርባለን።

3. ጥቆማ መስጠት፦ ኤምባሲው የሕገ-ወጥ ደላሎችን እንቅስቃሴ በቅርበት እየተከታተለ ሲሆን፣ ኅብረተሰቡ ስለ እነዚህ ሕገ-ወጥ አካላት የታመነ መረጃ ሲኖረው በኤምባሲው የስልክ መስመር +971500001522 በቀጥታ በመደወል ወይም በዋትስአፕ በጽሑፍና በድምፅ መልዕክት በምስጢር ጥቆማ እንዲሰጥ እንጠይቃለን።

በመጨረሻም መላው የኢትዮጵያ ማህበረሰብ አባላት የኢትዮጵያን እና የኤምሬቶችን ሕግ አክብረው በመንቀሳቀስ ራሳቸውንም ሆነ ወገኖቻቸውን ከጉዳት እንዲጠብቁ ኤምባሲው ጥሪውን በድጋሚ ያቀርባል።

የኢፌዲሪ ኤምባሲ — አቡዳቢ

13/08/2026

የኢትዮጵያ የታሪክ፣ የእድገት እና የነገ ተስፋ ጉዞ በ"መደመር መንግሥት" ዕይታ! 🇪🇹
————-
በአቡዳቢ በተካሄደው ታሪካዊው የመደመር መንግሥት መጽሐፍ የዓረብኛ ትርጉም ይፋዊ የምርቃት ሥነ-ሥርዓት ላይ የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ የለውጥ፣ የዕድገትና የታሪክ ጉዞ የሚያሳይ ልዩ ዶክመንተሪ ለታዳሚ ከፍተኛ የአገሪቱ ባለሥልጣናትና የዲፕሎማቲክ ማህበረሰብ አባላት ቀርቦ ነበር።

ይህ ልዩ ዶክመንተሪ፡

🔹 የመደመር እሴቶች፡ ሀገራችን ኢትዮጵያ በብዝሃነት ላይ የተመሠረተ አንድነቷን በማጠናከር ያከናወነቻቸውን ሁለንተናዊ የልማትና የዕድገት ሥራዎች፣

🔹 የተስፋና የዕድገት ጉዞ፡ በኢኮኖሚ፣ በዲፕሎማሲ እንዲሁም በቀጠናዊ ትስስር እውን እየሆኑ ያሉ ታላላቅ ሀገራዊ እቅዶችን እና ስኬቶችን፣

🔹 የሁለትዮሽ ወዳጅነት፡ በኢትዮጵያ እና በተባበሩት ዓረብ ኤምሬቶች መካከል ያለውን ጠንካራ ስትራቴጂካዊና ባህላዊ አጋርነት በጉልህ የሚያሳይ ነው።

ኢትዮጵያ በጥረቶቿና በጽናቷ ወደ ተሻለ የዕድገትና የብልፅግና ማዕዘን የምታደርገውን ጉዞ የሚያስቃኘው ይህ አጭር ዶክመንተሪ፣ የ"መደመር" ፍልስፍና የጋራ ጥረትንና ትስስርን መሠረት አድርጎ ያመጣውን አገራዊ ለውጥ በግልጽ ያሳያል።

መልካም ቆይታ! 🎬👇
Ethiopian News Agency
Ethiopian Press Agency /የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት/
FBC (Fana Broadcasting Corporate S.C.)
Ethiopian Broadcasting Corporation
Office of the Prime Minister-Ethiopia
The Ministry of Foreign Affairs of Ethiopia

የኤምባሲው ስታፍ አባላት አገልግሎት አሰጣጥንና ሙያዊ ብቃትን ለማሳደግ ያለመ ሥልጠና ወሰዱ————-በተባበሩት ዐረብ ኤምሬቶች የኢፌዲሪ ልዩ መልዕክተኛና ባለሙሉ ሥልጣን አምባሳደር ክቡር ዶ/ር...
12/08/2026

የኤምባሲው ስታፍ አባላት አገልግሎት አሰጣጥንና ሙያዊ ብቃትን ለማሳደግ ያለመ ሥልጠና ወሰዱ
————-
በተባበሩት ዐረብ ኤምሬቶች የኢፌዲሪ ልዩ መልዕክተኛና ባለሙሉ ሥልጣን አምባሳደር ክቡር ዶ/ር ጀማል በከር ከኤምባሲው ዲፕሎማቶችና የሥራ ባልደረቦች ጋር በሥራ ቦታ ስነ-ስርዓት፣ በዲፕሎማሲያዊ ፕሮቶኮልና በአገልግሎት አሰጣጥ ዙሪያ ሰፊ ውይይትና ሥልጠና አካሂደዋል።

በመድረኩ ላይ የተገኙት ክቡር አምባሳደር ዶ/ር ጀማል በከር ባደረጉት ንግግር፤ የኢትዮጵያ የውጭ ግንኙነት ፖሊሲ ዜጋ-ተኮር ዲፕሎማሲ ላይ ትኩረት የሚያደርግ መሆኑን አውስው፣ ለዜጎች የሚሰጠው የቆንስላና የዲፕሎማሲ አገልግሎት ብቁ፣ ቀልጣፋ፣ ፍትሐዊና ውጤታማ እንዲሆን የስታፍ አባላት የነቃ ተሳትፎና ከፍተኛ የሥራ ተነሳሽነት ወሳኝ መሆኑን አጽንኦት ሰጥተው አብራርተዋል።

ክቡር አምባሳደሩ አክለውም የዲፕሎማሲያዊ ፕሮቶኮል ደንቦችንና የሥራ ቦታ ዲስፕሊንን አክብሮ መንቀሳቀስ አገራዊ ገጽታን ከመገንባት ባለፈ የሚሲዮኑን የዘወትር የሥራ ውጤታማነት ከፍ እንደሚያደርገው ገልጸው፣ እያንዳንዱ ስታፍ ተገልጋይ ዜጎችን በቅንነትና በከፍተኛ ሙያዊ ሥነ-ምግባር ማስተናገድ እንዳለበት መመሪያ ሰጥተዋል።

በዕለቱ በተሰጠው የሥልጠና መርሃ-ግብር ላይ የዲፕሎማሲያዊ ፕሮቶኮል አፈጻጸም፣ የቢሮ ውሎና የሥራ ቦታ ዲስፕሊን ሕጎች እንዲሁም የተቀላጠፈ አገልግሎት አሰጣጥ ሥርዓቶች ላይ ተሰጥቷል፡፡

የኤምባሲው ስታፍ አባላት በበኩላቸው የተሰጣቸውን መመሪያ መሠረት በማድረግ ለዜጎች የሚሰጠውን አገልግሎት ጥራት ይበልጥ ለማሳደግና የተቀመጡ አገራዊ ግቦችን ለማሳካት በቁርጠኝነት እንደሚሠሩ አረጋግጠዋል።

ክቡር አምባሳደር ዶ/ር ጀማል በከር ከሞሪታንያ አቻቸው ጋር ውይይት አካሄዱ————-በተባበሩት ዐረብ ኤምሬቶች የኢፌዲሪ ልዩ መልዕክተኛና ባለሙሉ ሥልጣን አምባሳደር ክቡር ዶ/ር ጀማል በከር ከ...
11/08/2026

ክቡር አምባሳደር ዶ/ር ጀማል በከር ከሞሪታንያ አቻቸው ጋር ውይይት አካሄዱ
————-
በተባበሩት ዐረብ ኤምሬቶች የኢፌዲሪ ልዩ መልዕክተኛና ባለሙሉ ሥልጣን አምባሳደር ክቡር ዶ/ር ጀማል በከር ከሞሪታንያ አቻቸው H.E. Abdallahi Bah Nagi Kebd ጋር በሁለቱ አገራት የሁለትዮሽ ግንኙነትና ቀጠናዊ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት አካሂደዋል።

በውይይቱ ወቅት ክቡር አምባሰደር ዶ/ር ጀማል ኢትዮጵያ ከአፍሪካ አገራት ጋር ያላትን ወንድማማችነታዊ ግንኙነት ለማጠናከር እና በቀጣናዊ ሰላም፣ ደህንነት እንዲሁም ኢኮኖሚያዊ ትስስር ላይ በትብብር ለመሥራት ያላትን ቁርጠኝነት ገልጸዋል።

በተለይም ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት እያካሄደች ያለችውን አጠቃላይ የማክሮ ኢኮኖሚ እና የንግድ ሥርዓት ሪፎርም፣ በመካሄድ ላይ ስላለው አገራዊ ምክክር እና የተጀመሩ ግዙፍ አገራዊ የልማት ፕሮጀክቶችን በተመለከተ ለአቻቸው ሰፊ ገለጻ ሰጥተዋል።

የሞሪታንያ አምባሳደር በበኩላቸው ኢትዮጵያ በምሥራቅ አፍሪካና በአጠቃላይ በአፍሪካ አህጉር ያላትን ስትራቴጂካዊ፣ ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ተፅዕኖ ፈጣሪነት እንደሚያደንቁ ገልጸዋል።

ሁለቱ ሚሲዮኖች በአፍሪካ ህብረት ማዕቀፍ እንዲሁም በታዳሽ ኃይል ዙሪያ በትብብር እንዲሰሩም ጥሪ አቅርበዋል።

Address

Villa19 Ahl Alma'rifa St/Al Nahyan/Abu Dhabi
Abu Dhabi

Opening Hours

Monday 08:30 - 15:30
Tuesday 08:30 - 15:30
Wednesday 08:30 - 15:30
Thursday 08:30 - 15:30
Friday 08:30 - 12:30

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethiopian Embassy - UAE / AbuDhabi posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Ethiopian Embassy - UAE / AbuDhabi:

Share