13/02/2026
የታች አርማጭሆ ወረዳ ምክር ቤት የ5ኛ ዙር 13ኛ ዓመት 2ኛ መደበኛ ጉባዔ አካሄደ።
በጉባዔው ላይም የምክር ቤቱ አባላት፣ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶችና የየዘርፉ አመራሮች ተገኝተዋል።
በዚህ መደበኛ ጉባዔ ላይም ባለፉት ስድስት ወራት የተከናወኑ የልማት፣ የመልካም አስተዳደርና የሰላም ስራዎች በዝርዝር ቀርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል።
በሌላ በኩልም በየደረጃው ከህዝብ የሚነሱ የመሰረተ ልማት፣ የፍትህና የፀጥታ ጥያቄዎች ምላሽ እንዲያገኙ አቅጣጫዎች ተቀምጠዋል።
በመጨረሻም ምክር ቤቱ የቀረቡለትን ሪፖርቶች በጥልቀት በመገምገም የተለያዩ ውሳኔዎችንና ሹመቶችን አፅድቀዋል።
"ጠንካራ ምክር ቤት ለህዝብ ተጠቃሚነት"