Argoba Communication-አርጎባ ኮሙኒኬሽን

Argoba Communication-አርጎባ ኮሙኒኬሽን Ensure smooth flow of information between the woreda Government and the public and facilitate the process of building a society enriched with information

Argoba communication

ለወባ ተጋላጭ ነፍሰ ጡር እናቶችና ሕፃናት የአጎበር ድጋፍ ተደረገመዲና – ጳጉሜ 3/2018 ዓ.ም (አርጎባ ኮሙኒኬሽን)በአርጎባ ብሔረሰብ ልዩ ወረዳ ለወባ ተጋላጭ ለሆኑ ነፍሰ ጡር እናቶችና ...
08/09/2026

ለወባ ተጋላጭ ነፍሰ ጡር እናቶችና ሕፃናት የአጎበር ድጋፍ ተደረገ

መዲና – ጳጉሜ 3/2018 ዓ.ም (አርጎባ ኮሙኒኬሽን)

በአርጎባ ብሔረሰብ ልዩ ወረዳ ለወባ ተጋላጭ ለሆኑ ነፍሰ ጡር እናቶችና ሕፃናት 1,200 አጎበሮች ድጋፍ ተደረገ።

አጎበሮቹ ከአንድ ሚሊዮን ብር በላይ ግምት ያላቸው ሲሆን፣ ድጋፉን ያደረገው የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር ደሴ ቅርንጫፍ ከደቡብ ወሎ ዞን ጤና መምሪያ ጋር በመተባበር ነው።

በዕለቱ የወባን ስርጭት በተገቢው መከላከል ላይ ያተኮረ ግንዛቤ ለማስጨበጥ ትምህርት ተሰጥቷል።

በተለይም አጎበርን በአግባቡ የመጠቀም፣ የመንከባከብና የወባ ትንኝ ንክሻን በመከላከል የሚኖረው ሚና ላይ ትምህርት ተሰጥቷል።

የድጋፍ ሥራው በተለይም ለወባ ተጋላጭ የሆኑ ነፍሰ ጡር እናቶችና ሕፃናትን ከወባ በሽታ ለመከላከል እንዲሁም በማኅበረሰቡ ዘንድ የወባ መከላከያ ግንዛቤን ለማሳደግ ጠቃሚ መሆኑ ተገልጿል።

ተጠቃሚዎችም ለተደረገላቸው ድጋፍ ምስጋና አቅርበው፣ በቀጣይም ተመሳሳይ የጤናና የሰብዓዊ ድጋፍ ሥራዎች እንዲጠናከሩ ጠይቀዋል

ጳጉሜን 3 የጽናት ቀን በአርጎባ ብሔረሰብ ልዩ ወረዳ እየተከበረ ነውመዲና- ጳጉሜን 3/2018 ዓ.ም (አርጎባ ኮሙኒኬሽን)በደቡብ ወሎ ዞን በአርጎባ ብሔረሰብ ልዩ ወረዳ ጳጉሜን 3 "የጽናት ...
08/09/2026

ጳጉሜን 3 የጽናት ቀን በአርጎባ ብሔረሰብ ልዩ ወረዳ እየተከበረ ነው

መዲና- ጳጉሜን 3/2018 ዓ.ም (አርጎባ ኮሙኒኬሽን)

በደቡብ ወሎ ዞን በአርጎባ ብሔረሰብ ልዩ ወረዳ ጳጉሜን 3 "የጽናት ቀን" በተለያዩ መርሐ ግብሮች እየተከበረ ይገኛል።

ዕለቱ የኢትዮጵያውያንን ጽናት፣ ተስፋና በችግር ወቅት አብሮ የመቆም እሴት በሚያሳዩ የተለያዩ መርሐ ግብሮች በድምቀት እየተከበረ ነው።

ጳጉሜን 2 የመንሰራራት ቀን በመስክ ምልከታ ተከበረመዲና – ጳጉሜን 2/2018 ዓ.ም (አርጎባ ኮሙኒኬሽን)በደቡብ ወሎ ዞን በአርጎባ ብሔረሰብ ልዩ ወረዳ ጳጉሜን 2 “የመንሰራራት ቀን” በህዝ...
07/09/2026

ጳጉሜን 2 የመንሰራራት ቀን በመስክ ምልከታ ተከበረ

መዲና – ጳጉሜን 2/2018 ዓ.ም (አርጎባ ኮሙኒኬሽን)

በደቡብ ወሎ ዞን በአርጎባ ብሔረሰብ ልዩ ወረዳ ጳጉሜን 2 “የመንሰራራት ቀን” በህዝብን ተጠቃሚ ካደረጉ የልማት ፕሮጀክቶች መካከል የኮልደር ልማት ሥራ እና የመዲና ከተማ ንፁህ የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክትን በመጎብኘት ተከብሯል።

“ለኢትዮጵያ መንሰራራት” በሚል መሪ ቃል በተከበረው በዚህ ዕለት፣ በመዲና መሪ ማዘጋጃ ቤት እና በመዲና ውሃና ፍሳሽ አገልግሎት ድርጅት የተከናወኑ የልማት ሥራዎች በመስክ ተጎብኝተዋል።

በመስክ ምልከታው የኮልደር ልማት ሥራና የመዲና ከተማ ንፁህ የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ያለበት ደረጃ ተጎብኝቶ በመስክ በመመልከት ተገምግሟል። ፕሮጀክቶቹ ለከተማውና ለአካባቢው ህብረተሰብ የሚያበረክቱት አስተዋፅዖም በመስክ ምልከታው ተመልክቷል።

በዚህም ጳጉሜን 2 “የመንሰራራት ቀን” የልማት ሥራዎችን በመጎብኘትና በመገምገም ተከብሯል።

በአርጎባ ብሔረሰብ ልዩ ወረዳ ጳጉሜ 1 “የእመርታ ቀን” ተከበረመዲና - ጳጉሜ 1/2018 ዓ.ም (አርጎባ ኮሙኒኬሽን)በአርጎባ ብሔረሰብ ልዩ ወረዳ ጳጉሜ 1 “የእመርታ ቀን” “የኢትዮጵያ መን...
06/09/2026

በአርጎባ ብሔረሰብ ልዩ ወረዳ ጳጉሜ 1 “የእመርታ ቀን” ተከበረ

መዲና - ጳጉሜ 1/2018 ዓ.ም (አርጎባ ኮሙኒኬሽን)

በአርጎባ ብሔረሰብ ልዩ ወረዳ ጳጉሜ 1 “የእመርታ ቀን” “የኢትዮጵያ መንሰራራት” በሚል መሪ ሃሳብ በልዩ ልዩ መርሃግብር ተከብሯል።

ዕለቱን አስመልክቶ በወረዳው በ01 መዲና ቀበሌ ደለመኔ ሞዴል ተፋሰስ የፍራፍሬ ልማት የሥራ እንቅስቃሴን የመስክ ጉብኝትና የፓናል ውይይት ተካሂዷል።

የመስክ ጉብኝቱ በአካባቢው በፍራፍሬ ልማት ዘርፍ እየተከናወኑ ያሉ ተግባራትን በተግባር ለመመልከትና በቀጣይ ሊሰፋ የሚገባውን የልማት ሥራ ለመለየት ዕድል ሰጥቷል።

በዕለቱ የተካሄደው የፓናል ውይይትም ምርታማነትን ለማሳደግና የልማት ሥራዎችን ይበልጥ ውጤታማ ለማድረግ የሚያስችሉ ገንቢ ሃሳቦች ተነስተዋል።

በውይይቱ እየተከናወኑ ያሉ ሥራዎችን ክፍተቶች በመሙላት ማጠናከር፣ ፍሬያማ የሆኑ ሥራዎችን ደግሞ በበለጠ ማስፋትና በዘላቂነት ማስቀጠል እንደሚገባ በመገምገም መግባባት ላይ ተደርሷል።

የእመርታ ቀኑ የተጀመሩ የልማት ሥራዎችን በመገምገም፣ በስኬታማ ተሞክሮዎች ላይ በመወያየትና ቀጣይ የልማት አቅጣጫዎችን በማስቀመጥ የአካባቢውን እመርታ ለማፋጠን ያለመ መሆኑ ተገልጿል።

ሀገር በቀል የግጭት አፈታት፣ የእርቅ እና የሰላም ማስፈኛ ልምዶችን ለዘላቂ ሰላም ማዋል ይገባል።‎የሰላም ሚኒስቴር በደብረ ማርቆስ ከተማ ከሀገሪቱ ከተውጣጡ ከሀገር ሽመግሌዎች፣ ከሃይማኖት አ...
05/09/2026

ሀገር በቀል የግጭት አፈታት፣ የእርቅ እና የሰላም ማስፈኛ ልምዶችን ለዘላቂ ሰላም ማዋል ይገባል።

‎የሰላም ሚኒስቴር በደብረ ማርቆስ ከተማ ከሀገሪቱ ከተውጣጡ ከሀገር ሽመግሌዎች፣ ከሃይማኖት አባቶች እና ከሰላም እና ከጸጥታ አካላት ጋር የውይይት መድረክ አካሂዷል፡፡

‎የውይይት መድረኩ የሀገሪቱን ባሕላዊ ሀብቶች እና ከትውልድ ወደ ትውልድ ሲተላለፉ የመጡ ሀገር በቀል የግጭት አፈታት፣ የእርቅ እና የሰላም ማስፈኛ ልምዶችን በመለየት ብሎም በማጠናከር ለዘላቂ ሰላም እና ለሀገር ግንባታ የበለጠ እንዲውሉ ለማድረግ ያለመ ነው፡፡

‎የደብረ ማርቆስ ከተማ አሥተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ተሾመ ዋለ የከተማዋ ሕዝብ በኢትዮጵያዊ ወንድማማችነት የሚያምን፣ ሰላምን እና ልማትን የሚያስቀድም ነው ብለዋል፡፡

‎ከተማዋ በልማት ሥራዎች፣ በኢንዱስትሪ እና ኢንቨስትመንት ዘርፎች ተመራጭ መኾኗን ገልጸው አሁን ላይ ከተማዋ እና አካባቢው ወደ ሰላማዊ እንቅስቃሴ መግባታቸውን ተናግረዋል፡፡

‎አሁን ለተገኘው ሰላም እና መረጋጋት የሀገር መከላከያ ሠራዊት እና የክልል ጸጥታ አካላት ሚናም የሚያሥመሠግን እና ከፍ ያለ ስለመኾኑ ጠቁመዋል፡፡

‎የአማራ ክልል ሰላም እና ጸጥታ ቢሮ ምክትል ኀላፊ ኮሚሽነር ደጀኔ ልመንህ በበኩላቸው፣ ዘላቂ ሰላም መገንባት የማኅበረሰብን ተሳትፎ እንደሚጠይቅ ገልጸው የሀገር ሽማግሌዎች ጥበብ፣ የሃይማኖት አባቶች ምክር እና የሰላም አስተምህሮ ወሳኝ መኾናቸውን ጠቁመዋል።

‎የሰላም ሚኒስቴር የጽሕፈት ቤት ኀላፊ መብራቱ ካሳ የሰላም እጦት እና አለመረጋጋት የሁሉንም አካላት የጋራ ጥረት የሚጠይቅ ችግር መኾኑን ገልጸዋል።

‎አለመረጋጋት ከማኅበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ኪሳራ ባለፈ የሰው ሕይወትን እየጎዳ በመኾኑ ሰላምን ለማስፈን የሁሉም ዜጎች እና ተቋማት ተሳትፎ ወሳኝ መኾኑን አቶ መብራቱ አመላክተዋል።

‎ከዘመናዊ የግጭት አፈታት ዘዴዎች በተጨማሪ ማኅበረሰብን ለዘመናት ሲያስተሳስሩ የቆዩ የማስታረቅ ባሕላዊ ሥርዓቶች እና የሀገር በቀል የሰላም ዕውቀቶች እንዲጠናከሩ እና እንዲተገበሩ አስፈላጊ መኾኑን ጠቁመዋል።

‎የሀገር ሽማግሌዎች እና የሃይማኖት አባቶች በበኩላቸው ለሰላም የሚያበረክቱትን ሚና በማጠናከር ለሀገራዊ እና ክልላዊ ሰላም የበለጠ እንደሚሠሩ ተናግረዋል።

‎በውይይቱ ባሕላዊ እሴቶችን እና ሀገር በቀል የሰላም ዕውቀቶችን ከዘመናዊ የሰላም ግንባታ ሥርዓቶች ጋር በማጣመር፣ ግጭቶችን በሰላማዊ ውይይት፣ በሽምግልና እና በእርቅ ለመፍታት የሚያስችሉ አቅጣጫዎች ተመላክተዋል።

#አሚኮ

የአርጎባ ብሔረሰብ ልዩ ወረዳ የ2018 ዓ.ም የጳጉሜን ቀናትን በልዩ ልዩ ሁነቶች ለማክበር ውይይት አደረገመዲና – ነሐሴ 29/2018 ዓ.ም (አርጎባ ኮሙኒኬሽን)የአርጎባ ብሔረሰብ ልዩ ወረዳ...
04/09/2026

የአርጎባ ብሔረሰብ ልዩ ወረዳ የ2018 ዓ.ም የጳጉሜን ቀናትን በልዩ ልዩ ሁነቶች ለማክበር ውይይት አደረገ

መዲና – ነሐሴ 29/2018 ዓ.ም (አርጎባ ኮሙኒኬሽን)

የአርጎባ ብሔረሰብ ልዩ ወረዳ የ2018 ዓ.ም የጳጉሜን ቀናትን በልዩ ልዩ ሁነቶችና መርሃ ግብሮች ለማክበር ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት አደረገ።

የውይይቱ ዓላማ የጳጉሜን ቀናት “የኢትዮጵያ ማንሰራራት” በሚል መሪ ቃል በተለያዩ ሁነቶች በማክበር ያለፈውን ዓመት ለመገምገም፣ የተገኙ ውጤቶችን ለማጠናከርና አዲሱን ዓመት በተስፋና በከፍታ ለመቀበል የሚያስችሉ ተግባራትን በጋራ ለማከናወን ነው።

በውይይቱ የጳጉሜን አምስቱ ቀናት በተለያዩ ስያሜዎችና መልዕክቶች እንደሚከበሩ ተገልጿል።

ጳጉሜን 1 – የእመርታ ቀን

ጳጉሜን 2 – የማንሰራራት ቀን

ጳጉሜን 3 – የጽናት ቀን

ጳጉሜን 4 – የኅብር ቀን

ጳጉሜን 5 – የነገ ቀን

በዚህም መሠረት የጳጉሜን ቀናትን በተለያዩ ሁነቶችና መርሃ ግብሮች በደማቅ ሁኔታ ለማክበር ከባለድርሻ አካላት ሚናና ኃላፊነት ጋር በተያያዘ ሰፊ ውይይት ተደርጓል።

በተጨማሪም የተዘጋጁትን መርሃ ግብሮች በተቀናጀና በተሳካ ሁኔታ ለማስፈጸም አብይ ኮሚቴዎችን በማቋቋም የተለያዩ የሥራ ኃላፊነቶችን ለማከፋፈል ውይይት ተካሄዷል።

የጳጉሜን ቀናት አከባበሩ የወረዳውን ማኅበረሰብ በማሳተፍ የአንድነት፣ የእመርታና የተስፋ መንፈስን ለማጠናከር እንደሚያግዝ ተገልጿል።

ከ150 ኩንታል በላይ ጤፍና 40 ኩንታል ስኳር በተመጣጣኝ ዋጋ ለህብረተሰቡ እየቀረበ ነውመዲና – ነሐሴ 29/ 2018 ዓ.ም (አርጎባ ኮሙኒኬሽን) በአርጎባ ብሔረሰብ ልዩ ወረዳ የኑሮ ውድነት...
04/09/2026

ከ150 ኩንታል በላይ ጤፍና 40 ኩንታል ስኳር በተመጣጣኝ ዋጋ ለህብረተሰቡ እየቀረበ ነው

መዲና – ነሐሴ 29/ 2018 ዓ.ም (አርጎባ ኮሙኒኬሽን)

በአርጎባ ብሔረሰብ ልዩ ወረዳ የኑሮ ውድነት የሚያስከትለውን የኢኮኖሚ ጫና ለማቃለል ከ150 ኩንታል በላይ ጤፍና 40 ኩንታል ስኳር ለህብረተሰቡ ማቅረብ መቻሉ ተገለጸ።

በወረዳው ህብረት ሥራ ማህበራት ማስፋፊያ ጽሕፈት ቤት ሥር የሚገኘው የመዲና ሸማቾች ህብረት ሥራ ማህበር፣ የአካባቢውን ህብረተሰብ ከኑሮ ውድነት ጫና ለማቃለል የግብርናና የኢንዱስትሪ ምርቶችን በማቅረብ ላይ ይገኛል።

የወረዳው ህብረት ሥራ ማህበራት ማስፋፊያ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሁሴን መሐመድ እንደገለጹት፣ ማህበሩ ከ150 ኩንታል በላይ ጤፍና 40 ኩንታል ስኳር በማቅረብ መሠረታዊ የፍጆታ ምርቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ ለህብረተሰቡ እያቀረበ ይገኛል።

አቶ ሁሴን እንዳሉት፣ የሸማቾች ህብረት ሥራ ማህበሩ ምርቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ ለህብረተሰቡ በማቅረብ የገበያ ጫናን ለማቃለልና የኑሮ ውድነትን ለማረጋጋት አስፈላጊ ሚና እየተወጣ ነው።

በተለይም አላስፈላጊ የዋጋ ጭማሪ በመከላከል ለሸማቾች ተመጣጣኝ ዋጋ ያላቸውን መሠረታዊ ምርቶች ማቅረቡ በአካባቢው ገበያ መረጋጋት ላይ ያለው ፋይዳ የጎላ መሆኑንም ገልጸዋል።

የማህበሩ አገልግሎት ተጠቃሚዎችም ምርቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ ማግኘታቸው የኑሮ ውድነት ጫናን ከማቃለል ባለፈ በአካባቢው ገበያ የዋጋ መረጋጋት እንዲኖር ጠቃሚ መሆኑን ገልጸዋል።

በመሆኑም ማህበሩ ጀምሮ ያለውን የመሠረታዊ ምርቶች አቅርቦት በቀጣይነት እንዲያስቀጥልና የህብረተሰቡን የገበያ ፍላጎት በተሻለ ሁኔታ እንዲያሟላ ተጠቃሚዎች ጠይቀዋል።

በዳዋ ጨፋ ወረዳ አዘጋጅነት  አርጎባን ጨምሮ 7 /ሰባት/ አጎራባች ወረዳዎችን የፓርቲ ስራ አመራር ኮሚቴ የፓለቲካና ህዝብ ግንኙነት  የጋራ እቅድ ኦረንቴሽን መድረክ በከሚሴ ከተማ ተካሄደ።
03/09/2026

በዳዋ ጨፋ ወረዳ አዘጋጅነት አርጎባን ጨምሮ 7 /ሰባት/ አጎራባች ወረዳዎችን የፓርቲ ስራ አመራር ኮሚቴ የፓለቲካና ህዝብ ግንኙነት የጋራ እቅድ ኦረንቴሽን መድረክ በከሚሴ ከተማ ተካሄደ።

Adresse

Dessel

Site Web

Notifications

Soyez le premier à savoir et laissez-nous vous envoyer un courriel lorsque Argoba Communication-አርጎባ ኮሙኒኬሽን publie des nouvelles et des promotions. Votre adresse e-mail ne sera pas utilisée à d'autres fins, et vous pouvez vous désabonner à tout moment.

Contacter L’organisation

Envoyer un message à Argoba Communication-አርጎባ ኮሙኒኬሽን:

Raccourcis

Partager