የዓለም ከተማ ከተማ አስተዳደር ኮሙዩኒኬሽን ጸ/ቤት

የዓለም ከተማ ከተማ አስተዳደር  ኮሙዩኒኬሽን ጸ/ቤት ይህ ገጽ በዓለም ከተማ ከተማ አስ/ የመንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ፅ/ቤት ገፅ ነው
(1)

በዓለም ከተማ 03 ቀበሌ በክረምት በጎፍቃድ የተማሪዎች የፋይዳ መታወቂያ ምዝገባና አሻራ አሰጣጥ ተካሄደ።ነሀሴ 7/2018 ዓ/ምበዓለም ከተማ ከተማ አስተዳደር 03 ቀበሌ በሚገኘው ኢትዮ ሚሊኒ...
13/08/2026

በዓለም ከተማ 03 ቀበሌ በክረምት በጎፍቃድ የተማሪዎች የፋይዳ መታወቂያ ምዝገባና አሻራ አሰጣጥ ተካሄደ።

ነሀሴ 7/2018 ዓ/ም

በዓለም ከተማ ከተማ አስተዳደር 03 ቀበሌ በሚገኘው ኢትዮ ሚሊኒየም ትምህርት ቤት የተማሪዎች የፋይዳ መታወቂያ ምዝገባ ሥራ ተካሄደ።

የምዝገባና የአሻራ አሰጣጥ ሥራው በዓለም ከተማ ከተማ አስተዳደር ሴቶች፣ ሕፃናትና ማህበራዊ ጉዳይ ጽ/ቤት አስተባባሪነት ተከናውኗል።

በመርሃ ግብሩም የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ዓለም ከተማ ቅርንጫፍ ሲኒየር ቢዝነስ ባንኪንግ ኦፊሰር አቶ ኤፍሬም ንጉሴ እና የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ቢዝነስ ባንኪንግ ኦፊሰር ወ/ሮ ፋሲካ አንበርብር ተማሪዎችን የፋይዳ መታወቂያ ምዝገባና አሻራ አሰጣጥ ሥራ አከናውነዋል።

ይህም ተማሪዎች የፋይዳ መታወቂያቸውን በቀላሉ እንዲያገኙና ዲጂታል መረጃቸው በተገቢው መንገድ እንዲመዘገብ የሚያግዝ ነው።

በአለም  ከተማ ከተማ አስተዳደር "ተስፋን እንትከል" በሚል መሪ ቃል እየለሙ ባሉ የኢንቨስትመንት ቦታዎች የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ተካሄደ።‎‎   የአለም ከተማ አስተዳደር ...
13/08/2026

በአለም ከተማ ከተማ አስተዳደር "ተስፋን እንትከል" በሚል መሪ ቃል እየለሙ ባሉ የኢንቨስትመንት ቦታዎች የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ተካሄደ።

‎ የአለም ከተማ አስተዳደር ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ጽ/ቤት "ተስፋን እንትከል" በሚል መሪ ቃል እየለሙ ባሉ የኢንቨስትመንት ቦታዎች የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ መርሀ ግብር ነሀሴ 7/2018ዓ/ም አካሂዷል።

‎ በችግኝ ተከላ መርሀ ግብሩ የአለም ከተማ አስተዳደር ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ጽ/ቤት ኃላፊና ባለሙያዎች እንዲሁም የፕሮጀክቱ ተወካዮች ተሳትፈውበታል።

‎ ችግኞችን መትከል አፈርን በንፋስም ሆነ በጎርፍ እንዳይሸረሸር ከመከላከሉም በላይ የአየር ጠባይ ሚዛንን ለመጠበቅ ከፍተኛ ሚና አለው።

በአለም ከተማ የተቀናጀና የማህበረሰብ አቀፍ አሳታፊ እቅድ አስተቃቀድ ላይ ስልጠና ተሰጠ።ነሐሴ 6/2018 ዓ.ምበአለም ከተማ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ጽ/ቤት ሥር የሚገኘው የፕላንና ልማት ቡ...
12/08/2026

በአለም ከተማ የተቀናጀና የማህበረሰብ አቀፍ አሳታፊ እቅድ አስተቃቀድ ላይ ስልጠና ተሰጠ።

ነሐሴ 6/2018 ዓ.ም

በአለም ከተማ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ጽ/ቤት ሥር የሚገኘው የፕላንና ልማት ቡድን፣ የተቀናጀ የማህበረሰብ አቀፍ አሳታፊ እቅድ አስተቃቀድን በተመለከተ በየደረጃው የሚዘጋጁ እቅዶችን አስመልክቶ ለአብይና ቴክኒክ ኮሚቴ አባላት ስልጠና ሰጠ።

በስልጠናው የተቀናጀና የማህበረሰብ አቀፍ አሳታፊ እቅድ አስተቃቀድ ሂደት፣ በየደረጃው የሚዘጋጁ እቅዶች እንዲሁም የከተማዋን የመፃኢ እድገትና ልማት ሊያረጋግጥ የሚችል ውጤታማ እቅድ በማቀድ ረገድ ሊወሰዱ ስለሚገባቸው አቅጣጫዎች ሰፊ ገለጻ ተደርጓል።

ስልጠናውን የሰጡት የአለም ከተማ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ጽ/ቤት ሥር የሚገኘው የፕላንና ልማት ቡድን መሪ አቶ ጌታወይ ዘለለው እና የዘርፉ ባለሙያ አቶ ሀይለመስቀል በነበሩ ናቸው።

በመድረኩ የአለም ከተማ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ጌታው ጋሻው በማጠቃለያ ንግግራቸው፣ ስልጠናው የከተማዋን የመፃኢ እድገትና ልማት በተቀናጀ፣ በማህበረሰብ ተሳትፎ ላይ የተመሰረተ እና ከማህበረሰቡ ፍላጎትና ጋር በተጣጣመ መንገድ ለማስኬድ ውጤታማ እቅድ ለማዘጋጀት ጠቃሚ ግብዓት መሆኑን ገልጸዋል።

በቀጣይም በስልጠናው የተገኙ ግብዓቶችን በመጠቀም የከተማዋን የልማት እቅድ በተሳትፎና በተቀናጀ አካሄድ በማዘጋጀት የከተማዋን የመፃኢ እድገት ለማረጋገጥ የጋራ ተግባር እንደሚያስፈልግ ተጠቁሟል።

📢 ማስታወቂያበኪነ-ጥበብና ስፖርት ዘርፍ ለመመዝገብ ለምትፈልጉ ሁሉ!ነሀሴ 6/2018ዓ/ምየአለም ከተማ ከተማ አስተዳደር ባህል፣ ቱሪዝምና ስፖርት ጽ/ቤት በከተማችን የሚገኙ ወጣቶችና ባለሙያዎ...
12/08/2026

📢 ማስታወቂያ

በኪነ-ጥበብና ስፖርት ዘርፍ ለመመዝገብ ለምትፈልጉ ሁሉ!

ነሀሴ 6/2018ዓ/ም

የአለም ከተማ ከተማ አስተዳደር ባህል፣ ቱሪዝምና ስፖርት ጽ/ቤት በከተማችን የሚገኙ ወጣቶችና ባለሙያዎች ያላቸውን ተፈጥሯዊ ችሎታ፣ ክህሎትና ፍላጎት መነሻ በማድረግ በባህል፣ ኪነ-ጥበብና ስፖርት ዘርፎች ተሳትፎ እንዲያደርጉና ችሎታቸውን እንዲያሳድጉ ሰፊ ዕድል አመቻችቷል።

ስለሆነም፣ በኪነ-ጥበብና ስፖርት ዘርፍ ችሎታ፣ ፍላጎትና ተሰጥኦ ያላችሁ ወጣቶችና ባለሙያዎች በመመዝገብ ይህንን ዕድል እንድትጠቀሙ ጽ/ቤቱ በደስታ ይጋብዛችኋል።

🌟 ተሰጥኦዎን ያሳዩ፣ ክህሎትዎን ያሳድጉ፣ ለከተማችን ያበርክቱ!

📌 የምዝገባ ቦታ፦
በከተማዋ ውስጥ በሚገኙት 3ቱም ቀበሌዎች እና በአለም ከተማ ከተማ አስተዳደር ባህል፣ ቱሪዝምና ስፖርት ጽ/ቤት መመዝገብ ይቻላል።

📅 የምዝገባ ጊዜ፦
ከነሐሴ 7 ቀን 2018 ዓ.ም. ጀምሮ በየሥራ ቀኑ በመደበኛ የሥራ ሰዓት።

📞 ለበለጠ መረጃ፦
በአለም ከተማ ከተማ አስተዳደር ባህል፣ ቱሪዝምና ስፖርት ጽ/ቤት ቢሮ ቁጥር 45 እና 46 በመገኘት መረጃ ማግኘት ትችላላችሁ።

በዓለም ከተማ የሳምንታዊ ሥራዎች አፈጻጸም ተገመገመ።🗓 ነሐሴ 5/2018 ዓ.ምበዓለም ከተማ ከተማ አስተዳደር የሳምንቱን የመንግሥትና የፓርቲ ሥራዎች አፈጻጸም ለመፈተሽና ቀጣይ አቅጣጫዎችን ለ...
11/08/2026

በዓለም ከተማ የሳምንታዊ ሥራዎች አፈጻጸም ተገመገመ።

🗓 ነሐሴ 5/2018 ዓ.ም

በዓለም ከተማ ከተማ አስተዳደር የሳምንቱን የመንግሥትና የፓርቲ ሥራዎች አፈጻጸም ለመፈተሽና ቀጣይ አቅጣጫዎችን ለማስቀመጥ የሥራ ግምገማ መድረክ ተካሂዷል።

በመድረኩ የከተማውና የሦስቱ ቀበሌዎች አመራሮች የተሳተፉ ሲሆን የዓለም ከተማ ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ከንቲባ አቶ አበበ ተሰማ እና የከተማ ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ገለታው መኮንን የሳምንቱን አ አድርገዋል።

በውይይቱም በሦስቱም ቀበሌዎች በሰላምና ፀጥታ፣ በማኅበራዊ፣ በኢኮኖሚ እና በፖለቲካዊ ዘርፎች የተከናወኑ ተግባራት፣ የታዩ ጠንካራ ጎኖችና በቀጣይ መሻሻል የሚገባቸው ጉዳዮች በጥልቀት ተመልክተዋል።

ከግምገማው በኋላም በቀጣይ ትኩረት ሊሰጣቸው በሚገቡ ቁልፍ ተግባራት ላይ አቅጣጫ ተቀምጧል። በተለይም የክረምት በጎ ፍቃድ ሥራዎችን በተቀናጀ መልኩ ማከናወን፣ በየቀበሌው የተሻለ አፈጻጸም ማስመዝገብ እና በቀጣይ የሚፈጸሙ የሥራ ተግባራትን በተጠናከረ አመራር ማስፈጸም ላይ የጋራ ግንዛቤ ተፈጥሯል።

ግምገማው ያለፈውን ለማረም፣ የተሻለውን ለማጠናከርና ቀጣዩን ሥራ በተሻለ አቅም ለመፈጸም የቀጣይ አቅጣጫ በማስቀመጥ ግምገማዉ ተጠናቋል።

በአለም ከተማ ተቋርጦ የነበረው የማካን ሲልካ ሳንድ ፕሮሰሲንግ ሥራ እንደገና ጀመረ።ነሀሴ 05/2018 ዓ.ምበአለም ከተማ 02 ቀበሌ በገበያ ትስስር ችግር ምክንያት ተቋርጦ የነበረው የማካን ...
11/08/2026

በአለም ከተማ ተቋርጦ የነበረው የማካን ሲልካ ሳንድ ፕሮሰሲንግ ሥራ እንደገና ጀመረ።

ነሀሴ 05/2018 ዓ.ም

በአለም ከተማ 02 ቀበሌ በገበያ ትስስር ችግር ምክንያት ተቋርጦ የነበረው የማካን ሲልካ ሳንድ ፕሮሰሲንግ ድርጅት የገበያ ትስስር በመፈጠሩ ሥራውን እንደገና ጀምሯል።

የአለም ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ገለታው መኮንን፣ የከተማው ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ጽ/ቤት ሀላፊና ባለሙያዎች በተገኙበት በድርጅቱ የመስክ ምልከታ ተካሂዷል።

የአለም ከተማ ከተማ አስተዳደር ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ጽ/ቤት ሀላፊ ወ/ሮ ከነአን ታደሰ እንደገለጹት፣ የማካን ሲልካ ሳንድ ፕሮሰሲንግ ድርጅት በገበያ ትስስር ችግር ምክንያት ሥራው ተቋርጦ የቆየ ቢሆንም በአሁን ሰአት ድርጅቱ ሥራውን በድጋሚ መጀመሩን በመግለፅ ጭምር የኢንቨስትመንት ኮሚቴው እና ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ጽ/ቤት ሀላፊ እንዲሁም ባለሙያዎች ባደረጉት የመስክ ምልከታ ላይ በቀን እስከ 70 ቶን ምርት ማምረት እንደሚችል ማየት ተችሏል።

የድርጅቱ ሥራ እንደገና መጀመሩ ከምርት አቅም በተጨማሪ ለአካባቢው የሥራ ዕድል ፈጠራም አስተዋፅኦ እያደረገ ሲሆን፣ በድርጅቱ 32 ሰዎች የሥራ ዕድል ተፈጥሮላቸው እየሰሩ ይገኛሉ። ከእነዚህም 25 ወንዶች እና 7 ሴቶች ናቸው።

የድርጅቱ ሥራ እንደገና መጀመሩ በአለም ከተማ የኢንዱስትሪ ሥራዎችን ለማስፋፋት፣ የገበያ ትስስርን ለማጠናከርና የሥራ ዕድልን ለመፍጠር ያለውን ሚና ያሳያል።

የአለም ከተማ ኮሙኒኬሽን

‎''በጎነትና አብሮነት ለኢትዮጵያ ከፍታ!''በሚል መሪ ቃል የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ተጠናክሮ ቀጥሏል።‎‎  የአለም ከተማ ኮሙኒኬሽን ነሀሴ 05/2018 ዓ.ም ‎‎   በአለም ከተማ ከ...
11/08/2026

‎''በጎነትና አብሮነት ለኢትዮጵያ ከፍታ!''በሚል መሪ ቃል የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ተጠናክሮ ቀጥሏል።

‎ የአለም ከተማ ኮሙኒኬሽን ነሀሴ 05/2018 ዓ.ም

‎ በአለም ከተማ ከተማ አስተዳደር የክረምት በጎ ፍቃድ አገልግሎት አካል የሆነው የአቅመ ደካሞች የቤት ጥገና በሶስቱም ቀበሌ ተካሂዷል።

‎ በቤት ጥገና ፕሮግራሙ ላይ የአለም ከተማ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ አበበ ተሰማ ፣ የአለም ከተማ ብልጽግና ፖርቲ ቅ/ፅ/ቤት ሀላፊ አቶ ገለታው መኮንን፣የሴቶችና ወጣቶች ማህበራዊ ጉዳይ ጽ/ ቤት ኃላፊ ወ/ሮ ወይንሸት ገስጥ ጨምሮ የከተማና የቀበሌ አመራሮች እንዲሁም በጎ ፈቃደኛ ወጣቶች ተገኝተዋል።

‎ የአለም ከተማ ከተማ አስተዳደሩ ከንቲባ እንደገለፁት በ2018/2019 የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎትም በርካታ የአቅመ ደካማ ቤቶችን በመጠገንና በመገንባት አረጋውያን፣ አቅመ ደካሞችን ፣ አካል ጉዳተኞችን እና ዝቅተኛ ገቢ ያላቸውን የህብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ ለማድረግ በርካታ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ገልፀዋል።

‎ በጎነት ለራስ ነዉና በክረምት በጎ ፈቃድ ተግባራት የአቅመ ደካማ ቤት ጥገናና አዲስ ግንባታዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ ሌሎች ግለሰቦችና ተቋማት ተሳትፏቸዉን ማሳየት እንዳለባቸው ተገልፃል ።

🏃‍♀️ በጎነትና አብሮነት ለኢትዮጵያ ከፍታ! 🇪🇹ነሀሴ 3/2018 ዓ/ም«በጎነት እና አብሮነት ለኢትዮጵያ ከፍታ» በሚል መሪ ቃል ታላቅ የማስ ስፖርት እንቅስቃሴ በዓለም ከተማ ተካሄደ።በዓለም...
09/08/2026

🏃‍♀️ በጎነትና አብሮነት ለኢትዮጵያ ከፍታ! 🇪🇹

ነሀሴ 3/2018 ዓ/ም

«በጎነት እና አብሮነት ለኢትዮጵያ ከፍታ» በሚል መሪ ቃል ታላቅ የማስ ስፖርት እንቅስቃሴ በዓለም ከተማ ተካሄደ።

በዓለም ከተማ ከተማ አስተዳደር ባህል፣ ቱሪዝምና ስፖርት ጽሕፈት ቤት አስተባባሪነት የተዘጋጀው ይህ የማስ ስፖርት መርሃ ግብር፣ በከፍተኛ የሕዝብ ተሳትፎና በደመቀ ሁኔታ ተካሂዷል።

በመርሃ ግብሩ ላይ የከተማ አስተዳደሩ ከንቲባ አቶ አበበ ተሰማ፣ የብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ገለታው መኮንን፣ የባህል፣ ቱሪዝምና ስፖርት ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ መርከብ አከበረኝ፣ የየደረጃው አመራሮች፣ የመንግሥት ሠራተኞች፣ ወጣቶችና የተለያዩ የሕብረተሰብ ክፍሎች በመሳተፍ የአካል ብቃት ስፖርት አድርገዋል።

በመርሃ ግብሩ ላይ አመራሮች እንደገለጹት፣ ስፖርት የአካልና የአእምሮ ጤናን ከማሻሻል ባሻገር ማኅበራዊ ትስስርን ለማጠናከር፣ የሰላምና የአንድነት እሴቶችን ለማጎልበት የላቀ ሚና አለው ብለዋል።

የከተማ አስተዳደሩ ከንቲባ አቶ አበበ ተሰማ፣ የስፖርት ባህልን ማዳበር ንቁ፣ ጤናማና አምራች ዜጋን ለመፍጠር ወሳኝ መሆኑን ጠቁመው፣ በጎነትና አብሮነትን የተላበሰ ማኅበረሰብ ለመገንባት የጋራ ስፖርታዊ እንቅስቃሴዎች የላቀ ሚና እንዳላቸው ገልጸዋል።

የብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ገለታው መኮንን በበኩላቸው፣ የማስ ስፖርት መርሃ ግብሩ ሕዝባዊ ወንድማማችነትንና አብሮነትን ለማጠናከር፣ የጋራ ራዕይን ለማሳካት እንዲሁም ለሀገር ከፍታ የሚደረገውን የጋራ ጥረት ለማፋጠን ያለውን ፋይዳ አጉልተው ገልጸዋል።

የባህል፣ ቱሪዝምና ስፖርት ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ መርከብ አከበረኝ የማስ ስፖርት እንቅስቃሴዎች በቀጣይም በተጠናከረ መልኩ እንደሚቀጥሉ ጠቁመው፣ የወጣቶችንና የመላውን ማኅበረሰብ ጤና ከመጠበቅ ባሻገር የስፖርት ባህልን በስፋት ለማስረጽ ጽሕፈት ቤቱ በትኩረት እንደሚሠራ አረጋግጠዋል።

በመጨረሻም የተካሄደው የማስ ስፖርት እንቅስቃሴ የከተማውን ሕዝብ አንድነት፣ የአብሮነት መንፈስና የስፖርት ፍቅር በማንጸባረቅ በስኬት ተጠናቋል። ተመሳሳይ የማኅበረሰብ ተሳትፎ ያላቸው የስፖርት መርሃ ግብሮችም በቀጣይ በተጠናከረ መልኩ እንደሚቀጥሉ ተገልጿል።

በጎነትና አብሮነት፣ ለጤናማ ማኅበረሰብ፤ ለኢትዮጵያ ከፍታ! 🇪🇹🏃‍♂️🏃‍♀️
#በጎነትናአብሮነት
#ለኢትዮጵያከፍታ
#ማስስፖርት
#አለምከተማ
#የስፖርትባህል

ነሀሴ 2/2018ዓ/ም‎   በአለም ከተማ ከተማ አስተዳደር የአንድ ወር የፓርቲና የመንግስት ስራዎች ግምገማ የከተማና የቀበሌ አመራሮች በተገኙበት ከሰሜን ሸዋ ዞን የዞን ከፍተኛ አመራሮች ጋር...
08/08/2026

ነሀሴ 2/2018ዓ/ም
‎ በአለም ከተማ ከተማ አስተዳደር የአንድ ወር የፓርቲና የመንግስት ስራዎች ግምገማ የከተማና የቀበሌ አመራሮች በተገኙበት ከሰሜን ሸዋ ዞን የዞን ከፍተኛ አመራሮች ጋር ቨርችዋል ሚቲንግ(ዙም) ተደረገ።

‎ ቨርችዋል ሚቲንጉን የሰሜን ሸዋ ዞን ከፍተኛ አመራሮች የመሩት ሲሆን በቨርችዋል ሚቲንጉ የሁሉም ወረዳና ከተማ አስተዳደር የአንድ ወር የፓርቲና የመንግስት ስራዎች የጋራ ግምገማ አድርገዋል።

‎ቀን 2/12/2018ዓ.ም‎"በጎነትና አብሬነት  ለኢትዮጰያ ከፍታ"‎   የአለም ከተማ አጠቃላይ ሆስፒታል ከአለም ከተማ ጤና ጣቢያ  ጋር በመተባበር በክረምት በጎ ፈቃድ ነፃ የምርመራና ህክም...
08/08/2026

‎ቀን 2/12/2018ዓ.ም
‎"በጎነትና አብሬነት ለኢትዮጰያ ከፍታ"
‎ የአለም ከተማ አጠቃላይ ሆስፒታል ከአለም ከተማ ጤና ጣቢያ ጋር በመተባበር በክረምት በጎ ፈቃድ ነፃ የምርመራና ህክምና አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል።

‎ በአለም ከተማ ከተማ አስተዳደር በክረምት በጎ ፈቃድ አገልሎት እናት ጠቅላላ ሆስፒታል ከአለም ከተማ ጤና ጣቢያ ጋር በመተባበር የነፃ ምርመራና ህክምና ለማንኛውም የማህበረሰብ ክፍል አስፈላጊውን ምርመራ ማለትም የደም ግፊት ምርመራ ፤የስኳር ምርመራ ፤የሙቀት እና አተነፋፈስ እና የመጀመሪያ ህክምና እርዳታ አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል።

‎ በክረምት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት መርሃ- ግብር የጤናውን ዘርፍ ለማሻሻልና ተደራሽነቱን ለማስፋት ከግንዛቤ ፈጠራ ጀምሮ በርካታ ስራዎችን እየተሰራ ሲሆን ነፃ የምርመራና የህክምና አገልግሎት አንዱ ተግባር ነው።

‎ የአለም ከተማ እናት ጠቅላላ ሆስፒታል ጠቅላላ ሀኪም ዶክተር ሰለሞን ብርቅነህ እንዳሉት የዜጎች ጤና ቅድሚያ የሚሰጠው ሲሆን ማህበረሰቡን በክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት የነፃ ህክምና ተጠቃሚ በማድረግ ረገድ ሰፋፊ ስራዎች እየተሰሩ መሆኑን ገልፀው የነፃ ህክምና አገልግሎቱ ቀጣይነት ያለው መሆኑን አስታውቀዋል።

Address

`Alem Ketema

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የዓለም ከተማ ከተማ አስተዳደር ኮሙዩኒኬሽን ጸ/ቤት posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share