Adama Customs Branch Office የአዳማ ጉምሩክ ቅ/ጽ/ ቤት

  • Home
  • Ethiopia
  • Adama
  • Adama Customs Branch Office የአዳማ ጉምሩክ ቅ/ጽ/ ቤት

Adama Customs Branch Office የአዳማ ጉምሩክ ቅ/ጽ/ ቤት Adama Customs Branch Office
የአዳማ ጉምሩክ ቅ/ጽ/ ቤት
(1)

05/09/2026

አዋጅ ቁጥር 1425/2018 የጉምሩክ አዋጅን እንደገና ለማሻሻል የወጣ አዋጅ ስለ ኮንትሮባንድ ድረጊት ምን ይላል በሁለት ክፍል እናቀርባለን ተከታተሉን፡፡

ክፍል አንድ

16) የአዋጁ አንቀጽ 147 ኑዑስ አንቀጽ (3) ፊደል ተራ (ሀ) እና (ለ) ተሰርዘው በሚከተለዉ አዲስ ኑዑስ አንቀጽ (3) ፊደል ተራ (ሀ) እና (ለ) ተተክተዋል፡፡ እንዲሁም አዲስ ፊደል ተራ(ሐ) ተጨምሯል ፡፡

ሀ) ዕቃዎቹን ለመደበቅ እንዲያስችል ሆኖ የተሰራ፣የተለወጠ ወይም መደበቂያ አካል የተገጠመለት ከሆነ፤

ለ) በፊደል ተራ( ሀ) የተመለከተዉ እንደተጠበቀ ሆኖ ማጓጓዛዉ የኮንትሮባንድ ዕቃ ጭኖ የተገኘ ከሆነ ተሽከርካሪዉ ባለቤት የገንዘብ ሚኒስቴር የሚያወጣዉ መመሪያ በሚወሰነዉ መሰረት እንደነገሩ ክብደት እንዲሁም እንደጭነቱ መጠን በገንዘብ መቀጮ ወይም ማጓጓዣዉን እስከ መዉረሰ ሊያደርሰ በሚችል ቅጣት ሊቀጣ ይችላል፤

ሐ) ማጓጓዣዉ ከመወረሱ በፈት ማጓጓዣዉ ባለቤት ይህንኑ እንዲያዉቀዉ ሊደረግ እና ማጓጓዣዉ ጥቅም ላይ ስለዋለበት ሁኔታ ማስረጃ እንዲያቀርብ እድል ሊሰጠዉ ይገባል፡፡

17) የአዋጁ አንቀጽ 155 ኑዑስ አንቀጽ ( 2) ተሰርዞ በሚከተለዉ አዲስ ንዑስ አንቀጽ (2) ተተክቷል፤

2/ ይግባኝ የተባለበት ጉዳይ የቀረጥና ታክስ ክፍያ የሚመለከት ሲሆን የፌደራል ታክስ ይግባኝ ኮሚሽን 50% (ሃምሳ በመቶ) ክርክር ያስነሳዉ የቀረጥና ታክስ ክፍያ መፈጸሙን ሳያረጋግጥ ይግባኙን አይቀበልም፡፡

18) የአዋጁ አንቀጽ 157 ንዑስ አንቀጽ (3) ተሰርዟል የአንቀጽ 157 ቀሪ ድንጋጌዎች ተሸጋሽገዋል፡፡

19) የአዋጁ አንቀጽ 160 ተሰርዞ በሚከተለው አዲስ አንቀጽ ተተክቷል
160. ስለአጓጓዥ ግዴታዎች እና ኮንትሮባንድ በማጓጓዝ ዲርጊት ስለመሳተፍ

1/ማንኛዉም አጓጓዥ፡-

ሀ/ በተወሰነዉ የጊዜ ገደብ ዉስጥ የመንገደኞች ወይም የጭነት መገለጫ ካላቀረበ ፤

ለ/ ከተፈቀደለት ሰዉ በሰተቀር ሌላ ሰዉ ወደ ማጓጓዛዉ እንዲገባ ካደረገ ወይም

ሐ/ ማጓጓዛዉ ከጉምሩክ ወደብ እንዲወጣ ከተወሰነ በኋላ ምክንያቱን ለጉምሩክ ሹም ሳያስረዳና ፍቃድ ሳያገኝ እንዲቆይ ካደረገ ከብር 4,000 ባላነሰ እና ክብር 10,000 (አስር ሺ) በማይበልጥ መቀጮ ይቀጣል፡፡

------ ክፍል ሁለት ይቀጥላል

05/09/2026

አዋጅ ቁጥር 1425/2018 የጉምሩክ አዋጅን እንደገና ለማሻሻል የወጣ አዋጅ :-

------- ከለፈው የቀጠለ

2) አዋጁን አንቀጽ 25 ኑዑስ አንቀጽ(4) ተሰርዞ የሚከተለዉን ኑዑስ አንቀጽ(4) እንዲሁም ከኑዑስ አንቀጽ(4)ቀጥሎ አዲስ ኑዑስ አንቀጽ(5) ተጨምሯል፡፡

4/ በአንድ ዲክላራሲዮን ተመዝግበዉ ወደ አገር የገቡ ዕቃዎች ለነጻ ዝዉዉር መለቀቅ ያለባቸዉ በአንድ ላይ ነዉ::

5/ በዚህ አንቀጽ ኑዑስ አንቀጽ(4) ድንጋጌ ቢኖርም ዲክላራሲዮን አቅራቢዉ ወደ አገር ለገቡ ዕቃዎች ሊከፈል የሚገባዉን ቀረጥና ታክስ በአንድ ጊዜ መክፈል እንደማይቻል ገልፆ እቃዎችን በክፍልፋይ እንዲለቀቁ ጥያቄ ያቀረበ እንደሆነ ኮሚሽኑ በክፍልፋይ ለሚለቀቀዉ ዕቃ መጠን ሊከፈል የሚገባዉ ቀረጥና ታክስ መክፈሉ ሲያረጋግጥ ዕቃዎች በክፍልፋይ እንዲለቀቁ ሊፈቀድ ይችላል፡፡

3) አዋጁ አንቀጽ 51 ኑዑስ አንቀጽ (1). (2) (7) እና (8) ተሰርዞ በሚከተለዉ አዲስ ኑዑስ አንቀጽ (1)፤ (2)፤ (7) እና (8) ተተክቷል፤

1/ መዘግየቱ የተፈጠረዉ በጉምሩክ ቁጥጥር በአስተዳደርራዊ እርምጃ ወይም ከአቅም በላይ በሆነ ሁኔታ በመሆኑ ምክንያት ጊዜዉ ካልተራዘመ በስተቀር ማንኛዉም በባህር ወይም በየብስ ተጓጉዞ ወደ አገር የገባ ዕቃ ጊዜያዊ የጉምሩክ ዕቃ ማከማቻ ከገባበት ቀን ጀምሮ በአርባ አምስት ቀናት ዉስጥ አስፈላጊዉ የጉምሩክ ሥነሥርዓት ተከናዉኖበት ከማከማቻዉ መዉጣት አለበት፡፡

2/ በዚህ ኑዑስ አንቀጽ(1) በተገለጹት ተመሳሳይ ልዩ ሁኔታዎች ምክንያት ጊዜዉ ካልተራዘመ በስተቀር ማናቸዉም በአየር ተጓጉዞ ወደ አገር የገባ ዕቃ ማከማቻ ከገባበት ቀን ጀምሮ በሰላሳ ቀናት ዉስጥ አስፈላጊዉን የጉምሩክ ሥነሥርዓት ተከናዉኖበት ከማከማቻዉ መዉጣት አለበት፡፡

7/ ወደ ጊዜያዊ የጉምሩክ ዕቃ ማከማቻ ወይም ቦንድድ መጋዘን የገባ ዕቃ በዚህ አንቀጽ ኑዑስ አንቀጽ (1)፤(2)፤(3) እና (4) በተመለከተዉ ጊዜ ዉስጥ ካልወጣ ወደ መንግስት ጉምሩክ መጋዘን እንዲዛወር ይደረጋል፡፡

8/ በዚህ አንቀጽ ኑዑስ አንቀጽ(7) መሰረት ወደ መንግስት ጉምሩክ መጋዘን የገቡ እቃዎች ከመወገዳቸዉ በፊት የዕቃዉ ባለቤት ሊከፍል የሚገባዉን ቀረጥና ታክስ እንዲሁም ሌሎች ወጪዎችን በከፊል ዕቃዎችን የመረከብ መብት ይኖረዋል፡፡

------ ይቀጥላል

05/09/2026
04/09/2026

ቀን 29/12/2018 ዓ. ም

ማስታወቂያ

ለክብሯን ደንበኞቻችን በሙሉ

በቅርንጫፍ ጽ/ቤታችን የእየሰጠን የምንገኘው የጉምሩክ ስነስረዓት አገልግሎት በተፋጠነ መልኩ ለመከወንና በቅርንጫፍ ጽ/ቤታችን ጊቢ ውስጥ የሚገኙ እቃዎች የጉምሩክ ስነስርዓት ጨርሰው ለሚፈለገው አገልግሎት እንዲደርሱ ለማስቻል ያመች ዘንድ ከመደበኛ ስራ ሰዓት በተጨማሪ በእረፍት ቀናት አገልግሎት መስጠት አሰፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ ቅዳሜ ቀን 30/12/2018 ዓ.ም እና እሁድ ሙሉ ቀን በቀን 01/13/2018 ዓ.ም እንደማንኛውም መደበኛ የስራ ቀናት ሙሉ አገልግሎት ስለምንሰጥ ማሟላት ያለባችሁን አስፈላጊ ቅድመ ዝግጅት በማሟላት አገልግሎት ማግኘት የምትችሎ መሆኑን በአክብሮት እየገለጽን የቅ/ጽ/ቤታችን ሰራተኞችም በስራ ገበታ ለይ በመገኘት ለደንበኞቻችን ተገቢውን አግልግሎት እንድትሰጡ እናሳውቃለን።
አዳማ ጉ/ቅ/ጽ/ቤት!!

04/09/2026

አዋጅ ቁጥር 1425/2018 የጉምሩክ አዋጅን እንደገና ለማሻሻል የወጣ አዋጅ
------ ካለፈው የቀጠለ

2) የአዋጁ አንቀጽ 25 ኑዑስ አንቀጽ(4) ተሰርዞ የሚከተለዉን ኑዑስ አንቀጽ(4) እንዲሁም ከኑዑስ አንቀጽ(4)ቀጥሎ አዲስ ኑዑስ አንቀጽ(5) ተጨምሯል፡፡

4/ በአንድ ዲክላራሲዮን ተመዝግበዉ ወደ አገር የገቡ ዕቃዎች ለነጻ ዝዉዉር መለቀቅ ያለባቸዉ በአንድ ላይ ነዉ

5/ በዚህ አንቀጽ ኑዑስ አንቀጽ(4) ድንጋጌ ቢኖርም ዲክላራሲዮን አቅራቢዉ ወደ አገር ለገቡ ዕቃዎች ሊከፈል የሚገባዉን ቀረጥና ታክስ በአንድ ጊዜ መክፈል እንደማይቻል ገልፆ እቃዎችን በክፍልፋይ እንዲለቀቁ ጥያቄ ያቀረበ እንደሆነ ኮሚሽኑ በክፍልፋይ ለሚለቀቀዉ ዕቃ መጠን ሊከፈል የሚገባዉ ቀረጥና ታክስ መክፈሉ ሲያረጋግጥ ዕቃዎች በክፍልፋይ እንዲለቀቁ ሊፈቀድ ይችላል፡፡

ይቀጥላል-------

03/09/2026

ውድ ደንበኞቻችን እና ተከታታዮቻችን ፡-የጉምሩክ አዋጅን እንደገና ለማሻሻል የወጣ አዋጅ ቁጥር 1425/2018 ለግንዛቤ ይረዳችሁ ዘንድ በተከታታይ ስለምናቀርብላችሁ ተከታተሉን፡፡

አዋጅ ቁጥር 1425/2018 የጉምሩክ አዋጅን እንደገና ለማሻሻል የወጣ አዋጅ;

የገቢ እና የወጪ ንግድ ይበልጥ የተቀላጠፈ እንዲሆን ማድረግ፤ የጉምሩክ ስርዓት ኢትዮጵያ ከፈረመቻቸዉ አለም ዓቀፍ ስምምነቶች እንዲሁም አህጉራዊ እና ቀጠናዊ ስምምነቶች ጋር የተጣጣመ እንዲሆን ለማድረግ፤አስመጪዎች በቀረጥ እና ታክስ አወሳሰን ረገድ ያላቸዉን አቤቱታ በማቅረብ ረገድ የነበረባቸዉን መሰናክል ለማሰወገድ የጉምሩክ አዋጅን ማሻሻል አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ፤

የኮንትሮባድን ንግድ ስራን ለመከላከል የሚያስችሉ ተጨማሪ ድንጋጌዎችን በአዋጁ ዉስጥ ማካተት የኮንትሮባድን ንግድ ለመከላከል የሚያስችል በመሆኑ፤በኢትዮጵያ ፌደራላዊ ሪፐብሊክ ሕገ-መንግስት አንቀጽ 55 ኑዑስ አንቀጽ(1) መሰረት የሚከተለዉ ታውጇል፡፡

1. አጭር ርዕስ

ይህ አዋጅ የጉምሩክ አዋጅ (እንደተሻሻለ) እንደገና ለማሻሻል የወጣ አዋጅ ቁጥር 1425/2026 ተብሎ ሊጠቀስ ይችላል፡፡

2. ማሻሻያ

የጉምሩክ አዋጅ ቁጥር 859/2006 ( እንደተሻሻለ) እደሚከተለዉ እንደገና ተሻሽሏል፡-

1.አዋጁ አንቀጽ 23 ኑዑስ አንቀጽ(1) ተሰርዞ በሚከተለዉ አዲስ ኑዑስ አንቀጽ (1)፡(2)፡(3) እና(4) ተተክቷል ሌሎች የአንቀጹ ድንጋጌዎች ከኑዑስ አንቀጽ(5) እስከ (11) በመሆን ተሸጋሽገዋል፡-

1/ ከኮሚሽኑ የሚለቀቁ እቃዎች በተመዘገበ ዲክላራሲዮን የተሸፈኑ መሆናቸዉን ለማረጋገጥ እና ቀጣይ የጉምሩክ ሥነ-ሥርዓትን ለመፀም የቃዎቹን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል ወይም በመመሪያ የሚወሰን መጠን ናሙናዎችን በመውሰድ መመርመር ይቻላል፡፡

2/ በዚህ አንቀጽ ኑዑስ አንቀጽ(1) መሠረት የሚከናወን የዕቃ ምርመራ እንደ አስፈላጊነቱ በዕቃ መፈተሻ መሳሪያ ወይም በላቦራቶሪ ወይም በአካላዊ ወይም በሌላ አማራጭ ሊከናወን ይችላል፡፡

3/ ኮሚሽኑ በዲክላራሲዮን አቅራቢዉ የቀረበ የዕቃ ዲክላራሲዮን ላይ የሰፈሩ መረጃዎችን ትክክለኛነት እና የተሟሉ መሆናቸዉን ለማረጋገጥ የሰነድ ምርመራ ሊያከናዉን ይችላል፡፡

4/ በዚህ አንቀጽ ኑዑስ አንቀጽ (2) ድንጋጌ እንደተጠበቀ ሆኖ ኮሚሽኑ አስፈላጊ ሆኖ ሲያገኘዉ አስቀድሞ የዕቃ እና/ወይም የሰነድ ምርመራ በተከናወነባቸዉ ዕቃዎች ላይ በድጋሚ ምርመራ ሊያከናዉን ይችላል::

ይቀጥላል------------

በኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን አዳማ ጉምሩክ ቅ/ጽ/ቤት  በአራት ዙር ሲሰጥ የነበረው የቴክንካል  ስልጠና በዛሬው እለት ተጠናቀቀ፡፡*ነሐሴ  27/2018 ዓ.ም*የኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን ከአዲስ...
02/09/2026

በኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን አዳማ ጉምሩክ ቅ/ጽ/ቤት በአራት ዙር ሲሰጥ የነበረው የቴክንካል ስልጠና በዛሬው እለት ተጠናቀቀ፡፡

*ነሐሴ 27/2018 ዓ.ም*

የኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር ለመላዉ ሰራተኛ በበይነ መረብ /online/ ከነሐሴ 18 /2018 ዓ.ም ጀምሮ ዛሬ ለአዳማ ጉምሩክ ቅ/ጽ/ቤት መላው ሰራተኛ በ 4 ዙር ሲሰጥ የቆየው ቴክኒካል ስልጠና ተጠናቀቀ ፡፡

ስልጠናው ከአዲስ አበባ ዩንቨርስቲ ጋር በትብብር የተዘጋጀ ሲሆን በኮሚሽን ደረጃ እየተተገበረ ላለዉ የሪፎርም ስራ መሰረታዊ ዕዉቀት /ግንዛቤ/ ማሰጨበጫ አካል በመሆኑ ሁሉም ሰራተኛ በንቃትና በትኩረት ክትትል ሲያደርግ ቆይቷል ፡፡

አዳማ ጉምሩክ በስልጠናው እንዲሳተፉ ከያዘው እቅድ ውስጥ 97.8% በስልጠናው ላይ ተሳትፈዋል፡፡

ስልጠናውን የተከታተሉት ሰራተኞች እንዳነሱት ይህ ስልጠና በዚህ ሁኔታ የሰራተኛውን ሁሉአቀፍ ግንዛቤ ለማስጨበጥ ታስቦበት መዘጋጀቱ እንዳስደሰታቸውና በቂ እውቀት እንዳገኙበት አንስተዋል፡፡

ስልጠናው ከቅርንጫፍ ጽቤቱ ዋና ስራ አስኪያጅ በአቶ መንግስቱ ባልቻ እና በየደረጃው ባሉ አመራሮች የቅርብ ክትትል በማድረግ በጥሩ ሁኔታ የተካሄደ ስልጠና ነበር፡፡

አዳማ ጉምሩክ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት!!
"ስለምትከታተሉን ከልብ እናመሰግናለን!!

ደንበኞች ትምህርት ቡድን!!

31/08/2026

በቀረጥና ታክስ ማስከፈያ ዋጋ ስለሚጨመሩ፣ ስለሚቀነሱ እና የማይካተቱ ክፍያዎችና ወጪዎች አጠቃላይ አፈጻጸም ሂደት:-

በጉምሩክ ቀረጥና ታክስ ማስከፈያ ዋጋ ስለሚካተቱ ተጨማሪ ክፍያዎችና ወጪዎች

በአዋጁ አንቀጽ 96 በተደነገገው መሠረት ዕቃውን እስከ ኢትዮጵያ የመጀመሪያ መግቢያ ድረስ ለማድረስ ለዕቃው የተከፈሉ ወይም የሚከፈሉ ወጪዎችና ክፍያዎች በጉምሩክ ቀረጥ ማስከፈያ ዋጋ መካተት አለባቸው፡

ተጨማሪ ክፍያዎች በዕቃው የግብይት ዋጋ ውስጥ የሚካተቱበት ሁኔታ
በአዋጁ አንቀጽ 96 በተደነገገው መሠረት ተጨማሪ ወጪዎችና ክፍያዎች በሚከተሉት ሁኔታዎች ይካተታሉ፡-

 በኢንቮይሱ እና ሌሎች የንግድ ሰነዶች ላይ በግልጽ የተካተቱ ስለመሆናቸው ያልተገለጸ ከሆነ፣ ወይም

 የተከፈለው የዕቃው ዋጋ በንግድ ሰነድ ላይ በትክክል ያልተገለፀ ከሆነ፣ ወይም

 ዋጋ ሊተመንበት ከቀረበው ዕቃ ጋር በተያያዘ የተከፈለ ሲሆን፣ ወይም
 ስለመከፈላቸው ግልጽ መረጃ የቀረበላቸው ከሆነ ነው፡፡

ይቀጥላል --------

27/08/2026

በፖስታ ስለሚገቡና ስለሚወጡ ዕቃዎች የጉምሩክ ስነ-ስርዓት አፈጻጸም

በፖስታ አገልግሎት በኩል ወደ ሀገር ውስጥ የሚገቡ ወይም ከሀገር የሚወጡ ዕቃዎች የጉምሩክ ቁጥጥር ይደረግባቸዋል፡፡

የፖስታ አገልግሎት ሥራ እንዲሠራ የተፈቀደለት ማንኛውም ሰው በፖስታ ወደ አገር ውስጥ ስለገቡትና ወደ ውጪ አገር ስለሚላኩ ዕቃዎች የዕቃ ዝርዝር መግለጫ በማቅረብ ዕቃዎቹንም ለክሊራንስ ማቅረብ አለበት፡፡

ለጉምሩክ ሥነ-ሥርዓት አፈፃፀም ሲባል ወደ አገር ውስጥ የሚገቡ የፖስታ ጥቅል ዕቃዎች እንደሚከተለው ይመደባሉ፡-

 ለቤተሰብ ወይም ለግል ፍጆታ ወይም መጠቀሚያ በፖስታ ጥቅል ወደ ሀገር ውስጥ የሚገቡ ዕቃዎች፣

 በድርጅቶች ለንግድ አገልግሎት ወይም ለእርዳታ ዓላማ ወደ ሀገር ውስጥ የሚገቡ የፖስታ ጥቅል ዕቃዎች፣

 ተላላፊ የፖስታ ጥቅል ዕቃዎች ናቸው፡፡

በፖስታ ጥቅል የተላኩ የግል መገልገያ ዕቃዎች ዲክላራሲዮን መሙላት ሳያስፈልግ በኤሌክትሮኒክስ የመፈተሻ መሳሪያዎች (X-Ray Machine) እና በጉምሩክ አካላዊ ፍተሻ እየተደረገባቸው ወደ ሀገር ውስጥ ሊገቡ ይችላሉ፣

የወጪ ፖስታ ጥቅል ዕቃዎች የጉምሩክ ሥነ-ሥርዓት አፈፃፀም የወጪ ፖስታ ጥቅል ዕቃዎች እንደሚከተለው ይመደባሉ፡-

ሀ) ለቤተሰብ ወይም ለግለሰብ ፍጆታ ወደ ውጭ የሚላኩ ዕቃዎች፣

ለ) ለንግድ ወይም ለሌላ ዓላማ ወደ ውጭ የሚላኩ ዕቃዎች፣

ሐ) የግል መገልገያ ዕቃዎች በፖስታ ጥቅል ከሀገር በሚወጡበት ጊዜ የፖስታ አገልግሎት ድርጅቱ ዕቃው በመመሪያ በተወሰነው ዓይነትና መጠን ልክ መሆኑን በማረጋገጥ ለመውጫ የጉምሩክ ጣቢያ ማቅረብ አለባቸው፡፡

Address

Adama

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Adama Customs Branch Office የአዳማ ጉምሩክ ቅ/ጽ/ ቤት posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Adama Customs Branch Office የአዳማ ጉምሩክ ቅ/ጽ/ ቤት:

Shortcuts

Share