06/08/2026
ከምገባ እስከ ሰብአዊ ከብር — የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ታሪካዊ የምገባ ፕሮግራም
በአሁኑ ወቅት በዓለም አቀፍ ደረጃ በኢኮኖሚ መፋዘዝና በኑሮ ውድነት ምክንያት በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ወገኖች ለረሃብና ለምግብ እጥረት መጋለጣቸው የዓለም አቀፉ ማህበረሰብ አሳሳቢ ስጋት ሆኖ ቀጥሏል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የዘላቂ ልማት ግቦችን (SDG Goal 2 - Zero Hunger) ለማሳካት አገራት ዘርፈ ብዙ ጥረት እያደረጉ በሚገኙበት በዚህ ወቅት፣ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ያስጀመረው አጠቃላይ የምገባ ፕሮግራም ለሌሎች ከተሞች ጭምር ትልቅ ተሞክሮ የሚሆን ሰብአዊ እርምጃ ሆኖ ተመዝግቧል።
ከተማ አስተዳደሩ የከተማዋን ነዋሪዎች ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ደህንነት ለማረጋገጥ ባስቀመጠው ግልጽ ግብ መሰረት፣ በተለይም አቅመ-ደካሞችንና ተማሪዎችን ማዕከል ያደረገ ሰፊ ስራ ሰርቶ በተግባር እየፈፀመ ይገኛል። ፕሮግራሙ በቀን አንድ ጊዜ እንኳ በቂ ምግብ ማግኘት የማይችሉ ዜጎችን ለመደገፍ በመላው ከተማዋ ከ30 በላይ ዘመናዊና የተቀናጁ የምገባ ማዕከላትን አቋቁሞ አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል።
👉 የተማሪዎችን የትምህርት ተሳትፎ ማሳደግ፡ በምግብ እጥረት ምክንያት ከትምህርት ገበታ የሚቀሩና ትኩረት የሚያጡ ተማሪዎችን በመደገፍ፣ ትምህርታቸውን በትክክል እንዲከታተሉና የነገዋን ኢትዮጵያ በዕውቀት እንዲገነቡ መንገድ ከፍቷል።
👉 ሰብአዊ ክብርን ማረጋገጥ፡ ማንኛውም ዜጋ በራሱ ከተማ ውስጥ የመኖር፣ የመብላትና የመጠበቅ ሰብአዊ መብቱን የሚያረጋግጥ የአመራር ቁርጠኝነት ማሳያ ነው።
✅ ዓለም አቀፍ ደረጃን ያገናዘበ እይታ፡ ፕሮግራሙ ከተማዋ ዓለም አቀፍ የልማትና የሰብአዊነት መስፈርቶችን እንድታሟላ የሚያስችል ከመሆኑም በላይ፣ በከተሞች ደረጃ የሚደረግ ማህበራዊ ዋስትና (Social Protection) እንዴት ውጤታማ መሆን እንደሚችል ያሳያል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ይህንን በጎ ተግባር አጠናክሮ በመቀጠል፣ ረሃብና ድህነት የተሸነፉባት፣ የዜጎቿ ሰብአዊ ክብር የተጠበቀባትና ለአፍሪካ አህጉር አርአያ የምትሆን ከተማ የመገንባት ግቡን አሳክቶ ለማሳየት በሙሉ ቁርጠኝነት እየሰራ ይገኛል።