Addis Ababa City Admin. Landholding Registration and Information Agency

Addis Ababa City Admin. Landholding Registration and Information Agency Serving reliable cadastral services and information

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመሬት ይዞታ ምዝገባና መረጃ ኤጀንሲ

ራዕይ

በ2022 በከተማችን የህጋዊ ካዳስተርና አድራሻ ሥርዓት እውን ሆኖ ማየት፣

ተልዕኮ

በአዲስ አበባ ከተማ ወሰን ውስጥ የሚገኙ የመሬት ይዞታዎችን በሙሉ በማረጋገጥና በመመዝገብ አስተማማኝና ደህንነቱ የተጠበቀ በዘመናዊ ቴክኖሎጅ በመታገዝ ህጋዊ ካዳስተር፣ የአድራሻና የተቀናጀ የመሬትና መሬት ነክ መረጃ ሥርዓት መገንባት፣

ዕሴቶች

 አገልጋይነት
 ታማኝነት
 ተጠያቂነት
 በዕውቀት መምራት
 ግልጽነትና አሳታፊነት
 የለውጥ ባለቤት መሆን
 የቡድን ሥራ ለስኬታማነት

12/06/2026

📢 ለላቀ አገልግሎትና ለተደራጀ መረጃ የተዘጋጀ ልዩ ጥሪ!

​ለመሬት ይዞታ ምዝገባና መረጃ ኤጀንሲ አመራሮች እንዲሁም በየደረጃው ለምትገኙ መላው ሰራተኞች በሙሉ፦

​የኤጀንሲያችንን የአግልግሎት ጉዞ፣ የተከናወኑ ስራዎችንና የቀጣይ አቅጣጫዎችን በስፋት የሚዳስስ ልዩ የዶክመንተሪ (የሰነድ) ፊልም ተዘጋጅቶ ይጠብቃችኋል።

​ይህ ፕሮግራም የሁላችንንም የዕለት ተዕለት የልፋት ውጤት የሚያሳይና ለቀጣይ ስራዎቻችን ትልቅ መነቃቃትን የሚፈጥር በመሆኑ፣ ሁላችሁም በጋራ እንድትከታተሉት ጥሪያችንን እናስተላልፋለን።

​📺 የሥርጭት መርሃ-ግብር

​ቀን፦ ዛሬ ምሽት (አርብ)

​ሰዓት፦ ከምሽቱ 2:00 ሰዓት ጀምሮ

​የአየር ላይ ጣቢያ፦ በአዲስ ሚዲያ ኔትወርክ (AMN) ቴሌቪዥን

​የፕሮግራምዓይነት፦ በዶክመንተሪ ፕሮግራም ክፍለ-ጊዜ

​💡 ማሳሰቢያ፦ እባካችሁ ይህንን መልዕክት በየደረጃው ባሉ የማህበራዊ ሚዲያ ግሩፖች (Telegram, WhatsApp) ላይ ሼር በማድረግ ለሁሉም የስራ ባልደረቦቻችን እንዲደርስ እናሳስባለን።

​የመሬት ይዞታ ምዝገባና መረጃ ኤጀንሲ

“ለተደራጀ መረጃና ለተቀላጠፈ አገልግሎት!”

12/06/2026
12/06/2026

📢 ለላቀ አገልግሎትና ለተደራጀ መረጃ የተዘጋጀ ልዩ ጥሪ!

​ለመሬት ይዞታ ምዝገባና መረጃ ኤጀንሲ አመራሮች እንዲሁም በየደረጃው ለምትገኙ መላው ሰራተኞች በሙሉ፦

​የኤጀንሲያችንን የአገልግሎት ጉዞ፣ የተከናወኑ ስራዎችንና የቀጣይ አቅጣጫዎችን በስፋት የሚዳስስ ልዩ የዶክመንተሪ (የሰነድ) ፊልም ተዘጋጅቶ ይጠብቃችኋል።

​ይህ ፕሮግራም የሁላችንንም የዕለት ተዕለት የልፋት ውጤት የሚያሳይና ለቀጣይ ስራዎቻችን ትልቅ መነቃቃትን የሚፈጥር በመሆኑ፣ ሁላችሁም በጋራ እንድትከታተሉት ጥሪያችንን እናስተላልፋለን።

​📺 የሥርጭት መርሃ-ግብር

​ቀን፦ ዛሬ ምሽት (አርብ)

​ሰዓት፦ ከምሽቱ 2:00 ሰዓት ጀምሮ

​የአየር ላይ ጣቢያ፦ በአዲስ ሚዲያ ኔትወርክ (AMN) ቴሌቪዥን

​የፕሮግራምዓይነት፦ በዶክመንተሪ ፕሮግራም ክፍለ-ጊዜ

​💡 ማሳሰቢያ፦ እባካችሁ ይህንን መልዕክት በየደረጃው ባሉ የማህበራዊ ሚዲያ ግሩፖች (Telegram, WhatsApp) ላይ ሼር በማድረግ ለሁሉም የስራ ባልደረቦቻችን እንዲደርስ እናሳስባለን።

​የመሬት ይዞታ ምዝገባና መረጃ ኤጀንሲ

“ለተደራጀ መረጃና ለተቀላጠፈ አገልግሎት

12/06/2026
11/06/2026

ውድ ኢትዮጵያውያን ለ5 ሚሊዮን ኮደሮች ምዕራፍ ስኬት እንኳን ደስ አላችሁ!

‎በሦስት ዓመታት ውስጥ ለማሳካት የታቀደውን ግብ ከሁለት ዓመት ባነሰ ጊዜ ውስጥ ማሳካት ተችሏል። የ«5 ሚሊዮን የኢትዮጵያ ኮደሮች» ሐምሌ 16 ቀን 2016 ዓ.ም. ከተጀመረበት ጊዜ አንስቶ በኮምፒውተር ፕሮግራሚንግ፣ በመረጃ ትንተና፣ በአንድሮይድ ሶፍትዌር ልማት እና በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ መሠረታዊ ትምህርቶች 5,005,146 ሰልጣኞች ተመዝግበው ከ3 ሚሊዮን በላይ የሚሆኑት ስልጠናውን አጠናቀዋል። ይህ ስኬት የሕዝባችንን ቁርጠኝነት እና ወሰን የሌለው አቅም ማረጋገጫ ነው።

‎በዲጂታሉ ዓለም በልኩ ለመዘጋጀት የጀመርነው ታሪካዊ ምዕራፍ፤ የጉዟችን ማብቂያ ሳይሆን፥ ብሔራዊ ርዕያችንን ይበልጥ የምናፋጥንበት መነሻ ነው። እስከ ነሐሴ 2018 ዓ.ም. ድረስ የሰልጣኞችን ቁጥር 7 ሚሊዮን ለማድረስ የተሰነቀውን ግብ ለማሳካት፥ እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ የዚህ ብሔራዊ ተልዕኮ አካል እንዲሆን ጥሪዬን አቀርባለሁ።

‎ለወጣት ተማሪዎቻችን፤ መጭው የክረምት ወቅት ትልቅ ዕድላችሁ ነው። ጊዜያችሁን በዋዛ ከማሳለፍ ተቆጥባችሁ፤ በመመዝገብና በመማር ወደ ትምህርት ገበታችሁ ስትመለሱ ተማሪዎች ብቻ ሳትሆኑ፣ በዓለም አቀፍ ደረጃ እውቅና ያላችሁ የዲጂታል መሪዎች እንድትሆኑ አሳስባለሁ። ሥልጠናዎቹ ሙሉ በሙሉ በነጻ የሚሰጡ ሲሆን፥ የምስክር ወረቀቱም በዓለም አቀፍ ደረጃ እውቅና ያለው ነው።

‎የምትገነቡት ነገ የሚጀምረው ዛሬ ነው!

‎ለመመዝገብ እዚህ ይጫኑ:
‎ethiocoders.et/

የግንቦት ወር የስራ አፈጻጸም ተገመገመ--------------------------------------ሰኔ 04/2018 ዓ.ም(የመ/ይ/ም/መ/ኤ) AA-LHRIAየመሬት ይዞታ ምዝገባና መረጃ ኤጀንሲ...
11/06/2026

የግንቦት ወር የስራ አፈጻጸም ተገመገመ
--------------------------------------
ሰኔ 04/2018 ዓ.ም
(የመ/ይ/ም/መ/ኤ) AA-LHRIA

የመሬት ይዞታ ምዝገባና መረጃ ኤጀንሲ የልደታ፣ የንፋስ ስልክ እና የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤቶች በግንቦት ወር ያከናወኑትን የሥራ አፈጻጸም በጋራ ገምግመው በተገኙ ውጤቶች ላይ ውይይት አድርገዋል።

በወሩ ውስጥ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤቶቹ የይዞታ ማረጋገጥና ምዝገባ ሥራዎችን በስፋት በማከናወን የመሬት መረጃዎችን የተደራጀና ተደራሽ ለማድረግ አስፈላጊ ዕርምጃዎችን ከመውሰዳቸው ባሻገር በተለያዩ ምክንያቶች በክርክር መዝገብ ውስጥ የተያዙ ይዞታዎችን በማጥራትና ከክርክር መዝገብ በማውጣት ጉልህ ሥራ መሰራቱ ተገልጿል።

የዘመናዊ አገልግሎት ሥርዓት ግንባታን በተመለከተም የይዞታ ማህደራትን ስካኒንግና ዲጅታላይዜሽን ሥራዎች በስፋት መከናወናቸው የተጠቆመ ሲሆን የወረቀት አልባ (Paperless) ወይም የኢ-ላንድ አገልግሎት ለመጀመር እየተደረገ ያለው ጥረት ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ተገልጿል።

በኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ዘርፍ 12 የተለያዩ ሲስተሞች የለሙ ሲሆን፣ የስማርት ኦፊስ ትግበራም በይፋ መጀመሩ የተቋሙን የዲጅታል ሽግግር ጉዞ አዲስ ምዕራፍ ላይ እንዳደረሰው ተገልጾ እነዚህ ሲስተሞች የመረጃ አስተዳደርን ለማዘመን፣ የአገልግሎት ፍጥነትን ለማሳደግ እና የተገልጋዮችን እርካታ ለማሻሻል ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደሚኖራቸው ተመልክቷል።

በግምገማው ወቅት የኤጀንሲው ምክትል ዋና ዳይሬክተሮች አቶ አሸናፊ ቶላ እና አቶ አሳሳኸኝ ተስፋዬ በወሩ ውስጥ የተመዘገቡትን ውጤቶች አድንቀው፣ ቀሪ የክርክር መዝገብ ጉዳዮችና የዲጅታላይዜሽን ሥራዎች በተጠናከረ ሁኔታ እንዲቀጥሉ እና በተለይም የወረቀት አልባ አገልግሎትን በቅርብ ጊዜ ለማስጀመር የሚያስችሉ ሥራዎች ቅድሚያ ሊሰጣቸው እንደሚገባ ጠቁመዋል።

የኤጀንሲው ዋና ዳይሬክተር አቶ ተስፋዬ ጥላሁን በበኩላቸው በወሩ የተከናወኑ የላተራል ግዥ ሥራዎች፣ የመረጃ ማሰባሰብና ለሚዲያዎች ተደራሽ የማድረግ ጥረቶች አበረታች መሆናቸውን ገልጸው በተጨማሪም አገልግሎትን ቀልጣፋ በማድረግ በቴሌብር የክፍያ ሥርዓት ገቢን የመሰብሰብ ሥራ ማጠናከር እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡

በመጨረሻም የኤጀንሲው እና የቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊዎች በቦሌ ክ/ከተማ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የስራ ጉብኝት አድርገዋል፡፡

ለበለጠ መረጃ 👇👇👇
👉Website; https://addiscadaster.gov.et/
👉Facebook; Addis Ababa City Admin. Landholding Registration and Information
👉TikTok; A.Acadaster2016
👉Telegram; https://t.me/lhria
👉you tube; Legal cadaster
👉Customer Call Center: 6577

Address

604 Equatorial Guiene Avenue
Addis Ababa

Opening Hours

Monday 08:30 - 17:30
Tuesday 08:30 - 17:30
Wednesday 08:30 - 17:30
Thursday 08:30 - 17:30
Friday 08:30 - 17:30

Telephone

+251911409817

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Addis Ababa City Admin. Landholding Registration and Information Agency posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Addis Ababa City Admin. Landholding Registration and Information Agency:

Share