04/07/2026
የኢትዮጵያ ፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ባካሄደው ጉባኤ ስለ 7ኛው ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫን ሂደትን አስመልክቶ ውይይት አደረገ::
ምክር ቤቱ ሰኔ 27 2018 ዓ.ም ባካሄደው ጠቅላላ ጉባኤ የፖለቲካ ፓርቲዎች ከ7ኛው ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫ ሂደት ስለሚወስደው ትምህርት : ያጋጠመሟቸውን ተግዳሮቶች፣ የሂደቱ ተዓማኒነት እና አካታችነትን በተመለከተ፣ በቀጣይ ምን መደረግ እንዳለበት እና በጋራ መፍትሄዎች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል ::
የጉባኤው ተሳታፊዎች ህዝቡ አሉታዊ የሆኑ የውስጥ እና የውጭ ተጽእኖዎች ሳይበግሩት ያሳየው ዲሞክራሲያዊ ተሳትፎን አድንቀዋል :: ምርጫው ሰላማዊ ሆኖ መጠናቀቁ በበጎነት አንስተው ለዚህም ስኬት የበኩላቸውን ሃላፊነት ለተወጡ አካላት ምስጋናቸውን አቅርበዋል:: የፀጥታና የደህንነት አካላት ለብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ፣ ለክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች የጋራ ምክር ቤቶች አመራሮች፣ በየደረጃው የላቀ ምስጋናቸውን ገልጸው በሂደቱ የተስተዋሉ ችግሮች በቀጣይ የዲሞክረሲ ስርዓት መጎልበት እንቅፋት በመሆናቸው እንዳይደገሙ ሁሉም የድርሻው እንዲወጣ አሳስበዋል ።
ከዚህ ጋር በማያያዝም ምርጫ ያልተካሄደባቸው የሀገራችን አካባቢዎችም ህዝቡ የመምረጥ እድል እንዲያገኝ በማድረግ በመረጠው አስተዳደር እንዲመራ ለማስቻል ሁሉም ሃይሎች ለሰላማዊ የፖለቲካ ትግል ቅድሚያ እንዲሰጡና ሃላፊነታቸውን እንዲወጡ ጥሪ አቅርቧል::