Arada community participation and voulantry coordination office

Arada community participation and voulantry coordination office Have a responsbility of promoting public participation,coordinating any voulantry service,in Arada

በጎነት ለህልናችን እረፍት፣ለመንፈሳችን ደግሞ እርካታ ይሰጣል‼ የሚንሰጠው ከተረፈልን ሳይሆን ካለን ነው የሚናካፍልው።በአራዳ ክፍለ ከተማ የገና በዓል ማዕድ ለማጋራት የተለያዮ ማህበራት፣መንግ...
03/01/2023

በጎነት ለህልናችን እረፍት፣ለመንፈሳችን ደግሞ እርካታ ይሰጣል‼

የሚንሰጠው ከተረፈልን ሳይሆን ካለን ነው የሚናካፍልው።

በአራዳ ክፍለ ከተማ የገና በዓል ማዕድ ለማጋራት የተለያዮ ማህበራት፣መንግስታዊና መንግሰታዊ ያልሆኑ ተቋማት፣ በጎ ፈቃደኛ ወጣቶች፣ ነጋዴዎች፣ሴቶች ወጣቶችና ሌሎች በቅንጅት ዝግጅቶች እየተደረጉ ነው።

26/12/2022

በጎነት ለህልና እረፍት‼

በበጎ ፈቃድ ስራ እንትሳተፉ እናበረታታለን።

ለመሳተፍ የሚትፈልጉ አራት ኪሎ በሚገኘው የአራዳ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ህንጻ 4ኛ ፎቅ በሚገኘው የህብረተሰብ ተሳትፎና በጎ ፈቃድ ማስተባበሪያ በጽ/ቤት ተገኝታችሁ አስፈላጊ ድጋፍ ማግኘት ትችላላችሁ።

26/12/2022

ይህ የአራዳ ክፍለ ከተማ የህብረተሰብ ተሳትፎና በጎ ፈቃድ ማስተባበሪያ ፅ/ቤት የፌስቡክ አድራሻ ነው።

" በበጎ ፈቃደኞች የነቃ ተሳትፎ በክረምት ወቅት የተተከሉ ችግኞች እንክብካቤ አጠናክረን እንቀጥላለን ‼"             አቶ አለማየሁ አራጋው የአራዳ ክፍለ ከተማ ህብረተሰብ ተሳትፎና በ...
24/12/2022

" በበጎ ፈቃደኞች የነቃ ተሳትፎ በክረምት ወቅት የተተከሉ ችግኞች እንክብካቤ አጠናክረን እንቀጥላለን ‼"

አቶ አለማየሁ አራጋው
የአራዳ ክፍለ ከተማ ህብረተሰብ ተሳትፎና በጎ ፈቃድ ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ሀላፊ

የአራዳ ክፍለ ከተማ ህብረተሰብ ተሳትፎና በጎ ፈቃድ ማስተባበሪያ ጽ/ቤት የበጋ በጎ ፈቃድ መረሃ ግብር አካል የሆነውን በወንዝ ዳርቻ የተተከሉ የፍራፍሬ ችግኞችን የማንከባከብ ስራ በባሻ ወልዴ ወንዝ ዳርቻ አጠናክሮ መቀጠሉን አስታወቀ።

"በጎ ፈቃደኝነት ለማህበራዊ መስተጋብር" በሚል መሪ ቃል እየተከናወነ የሚገነው የበጋ በጎ ፈቃድ በክረምት ወቅት የተተከሉ ችግኞች እንድጸድቁ ለማድረግ የእንክብካቤ ስራው በበጎ ፈቃደኛ ወጣቶች አማካይኝነት እየተከናወነ እንደሚገኝ የገለጹት የአራዳ ክፍለ ከተማ ህብረተሰብ ተሳትፎና በጎ ፈቃድ ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ አለማየሁ አራጋው በንቅናቄ ችግኞችን እንደተከልን ሁሉ በንቅናቄ እንክብካቤ ማድረግ እንደሚገባ አሳስበዋል።

በክፍለ ከተማ አስተዳደሩ በይፋ በተጀመረው የችግኝ እንክብካቤ መረሃ ግብር ዛሬ ለሁለተኛ ጊዜ እየተከናወነ እንደሚገኝ ያስታወሱት ሀላፊው በጎ ፈቃደኝነት የወጣቱ ባህል እንድሆን ለማድረግ የሚታዩ ሰራዎች እየተሰሩ ይገኛልም ብሏል።

ከሁሉም ወረዳ የተወጣጡ የአረንጓዴ ልማት ችግኝ እንክካቤ በጎ ፈቃደኛ ወጣቶች የተሳተፉ ሲሆን መረሃ ግብሩ ቀጣይነት እንደሚኖረው ተገልጿል ሲል የኢዜአ ዘግቧል።

በህብረተሰባችን ተሳትፎ የ90 ቀን እቅዳችን እናሳካለን !!በአራዳ ክፍለ ከተማ ወረዳ 4 አስተዳዳር በ90 ቀን እቅድ ተይዞለት ከሚከናወኑ ተግባራት መካከል የወረዳው አስተዳደር ግቢ ሳቤዝና ቴ...
24/12/2022

በህብረተሰባችን ተሳትፎ የ90 ቀን እቅዳችን እናሳካለን !!

በአራዳ ክፍለ ከተማ ወረዳ 4 አስተዳዳር በ90 ቀን እቅድ ተይዞለት ከሚከናወኑ ተግባራት መካከል የወረዳው አስተዳደር ግቢ ሳቤዝና ቴራዞ ንጣፍ ፕሮጀክት እንዲሁም የጥበቃ ቤት ግንባታ ማስጀመሪያ ፕሮግራም ተካሔደ ።

ታህሳስ 13/2015 ዓ.ም

ይህ ፕሮጀክት ግቢውን በተለያዩ አትክልቶች የማስዋብ ስራን የሚጨምር ሲሆን በአጭር ጊዜ ተጠናቆ ለአገልግሎት ክፍት እንደሚሆን ይጠበቃል ።

የእለቱ የክብር እንግዳ የአራዳ ክፍለ ከተማ ህብረተሰብ ተሳትፎና በጎ ፈቃድ ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶአለማየሁ አራጋው እንደገለፁት ህብረተሰቡን በማሳተፍ የምንሰራቸው ስራወች የህዝቡን ጥያቄ የሚመልሱ ስለሆነ እንደነዚህ አይነት ፕሮጀክቶችን ህብረተሰቡ በገንዘብ በእውቀትና በጊዜም ጭምር መደገፍ እንዳለበት ተናግረዋል ።

የአራዳ ክፍለ ከተማ ወረዳ 4 አስተዳደር ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ አበበ ሃይሉ በበኩላቸው በ90 ቀን የምንሰራቸው የልማት ስራወች በተደጋጋሚ የመልካም አስተዳደር ጥያቄ የነበሩና ዛሬ የተጀመረው የግቢ የቴራዞ ንጣፍ በተለይ አገልግሎት ፈልገው ለሚመጡ ባለጉዳዪች ምቹ ሁኔታ ያልነበረውና አሁን ግን ይህንን ችግር አይተን ህዝባችን አሳትፈን ባጭር ጊዜ አጠናቀን ለአገልግሎት ክፍት አናደርጋለን ብለዋል ።

Address

Arat Kilo To Pissa
Addis Ababa
251

Telephone

+251920109516

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Arada community participation and voulantry coordination office posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share