29/05/2026
ተቋሙ በመሬት መንሸራተት ለተጎዱ ወገኖች የገንዘብ ድጋፍ አደረገ
ግንቦት 21/2018 ዓ.ም፣
የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት በጋሞ ዞን በመሬት መንሸራተት ለተጎዱ ወገኖች ከ8 መቶ ሺ ብር በላይ የገንዘብ ድጋፍ አደረገ።
ተቋሙን ወክለው በጋሞ ዞን ተገኝተው ድጋፉን ያስረከቡት የተቋሙ የዋና ዳይሬክተር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አብነት ሐዋዝ የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት የስታቲስቲክስ መረጃዎችን በማመንጨትና በማሰራጨት ሙያዊ ኃላፊነቱን ከመወጣት ባሻገር ማህበራዊ ኃላፊነቱን በመወጣት ከህዝብ ጎን የሚቆም ተቋም መሆኑን ገልፀው፣ በጋሞ ዞን በደረሰው የመሬት መንሸራተት አደጋ የተጎዱ ወገኖቻችንን መልሶ ለማቋቋምና ለመደገፍ ከዋናው መ/ቤትና ከ26 ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤቶች የሚገኙ አመራሮችና ሰራተኞችን በማስተባበር ከ8 መቶ ሺ ብር በላይ የሰበሰበ ሲሆን በዛሬው ዕለትም ይህንን ለማስረከብ በቦታው መገኘታቸውን ገልፀዋል።
ድጋፉን የተረከቡት የጋሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ልዩ አማካሪ አቶ ተስፋፅዮን ዘነበ የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት በዞናቸው ለደረሰው ጉዳት ላደረገው ድጋፍ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።