Ethiopian Statistical Service-ESS

Ethiopian Statistical Service-ESS Ethiopian Statistical Service collects, processes, and disseminates official statistical data.
(4)

ተቋሙ በመሬት መንሸራተት ለተጎዱ ወገኖች የገንዘብ ድጋፍ አደረገ          ግንቦት 21/2018 ዓ.ም፣የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት በጋሞ ዞን በመሬት መንሸራተት ለተጎዱ ወገኖች ከ8...
29/05/2026

ተቋሙ በመሬት መንሸራተት ለተጎዱ ወገኖች የገንዘብ ድጋፍ አደረገ
ግንቦት 21/2018 ዓ.ም፣
የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት በጋሞ ዞን በመሬት መንሸራተት ለተጎዱ ወገኖች ከ8 መቶ ሺ ብር በላይ የገንዘብ ድጋፍ አደረገ።
ተቋሙን ወክለው በጋሞ ዞን ተገኝተው ድጋፉን ያስረከቡት የተቋሙ የዋና ዳይሬክተር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አብነት ሐዋዝ የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት የስታቲስቲክስ መረጃዎችን በማመንጨትና በማሰራጨት ሙያዊ ኃላፊነቱን ከመወጣት ባሻገር ማህበራዊ ኃላፊነቱን በመወጣት ከህዝብ ጎን የሚቆም ተቋም መሆኑን ገልፀው፣ በጋሞ ዞን በደረሰው የመሬት መንሸራተት አደጋ የተጎዱ ወገኖቻችንን መልሶ ለማቋቋምና ለመደገፍ ከዋናው መ/ቤትና ከ26 ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤቶች የሚገኙ አመራሮችና ሰራተኞችን በማስተባበር ከ8 መቶ ሺ ብር በላይ የሰበሰበ ሲሆን በዛሬው ዕለትም ይህንን ለማስረከብ በቦታው መገኘታቸውን ገልፀዋል።

ድጋፉን የተረከቡት የጋሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ልዩ አማካሪ አቶ ተስፋፅዮን ዘነበ የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት በዞናቸው ለደረሰው ጉዳት ላደረገው ድጋፍ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለ1447ኛ የኢድ አል-ዓደሃ (አረፋ)  በዓል  በሰላም አደረሳችሁ፤ ኢድ ሙባረክ!
26/05/2026

ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለ1447ኛ የኢድ አል-ዓደሃ (አረፋ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ ኢድ ሙባረክ!

በ55ኛ መደበኛ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ስብሰባ ውሳኔ ካስተላለፈባቸው ጉዳዮች ውስጥ የስታቲስቲክስ ረቂቅ አዋጅ አንዱ መሆኑ ተገለፀግንቦት 18 ቀን 2018 ዓ.ም፣ አዲስ አበባ          ...
26/05/2026

በ55ኛ መደበኛ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ስብሰባ ውሳኔ ካስተላለፈባቸው ጉዳዮች ውስጥ የስታቲስቲክስ ረቂቅ አዋጅ አንዱ መሆኑ ተገለፀ
ግንቦት 18 ቀን 2018 ዓ.ም፣ አዲስ አበባ የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ ረቂቅ አዋጅ ምክር ቤቱ የተወያየበት ሌላው አጀንዳ ነው፡
የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ሞያዊ ነፃነትን ለማረጋገጥ፣ የተቆጣጣሪ እና የፈጻሚ አካላትን የቁጥጥር እና የአሠራር ተግባራትን ሚና በግልፅ ለመለየት፣ በሁሉም ኦፊሽያል ስታቲስቲክስ አመንጪዎች መካከል ያለውን ትብብር ለማጠናከር፣ የመረጃ ምስጢራዊነትን ለመጠበቅ፣ የስታቲስቲክስ ውጤቶችን ጥራት ለማሻሻል፣ ተደራሽነታቸውን ለማረጋገጥ እና ሀገራዊ አሠራሮችን ከዓለም አቀፍ የስታቲስቲክስ መርሆዎች እና ደረጃዎች ጋር ለማጣጣም እንዲያስችል ረቂቅ አዋጁ ተዘጋጅቶ ቀርቧል፡፡
ምክር ቤቱም በረቂቅ አዋጁ ላይ በሰፊው ከተወያየ በኋላ ግብአቶችን በማከል ወደ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲተላለፍ በሙሉ ድምፅ ወስኗል፡፡

በተቋሙ የስራ አፈፃፀምና ቀጣይ የስራ አቅጣጫዎች ላይ ውይይት ተደረገግንቦት 18/2018 ዓ.ም አዲስ አበባ፣የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ባለፉት ሶስት ተከታታይ ዓመታት ባከናወናቸው  የ...
26/05/2026

በተቋሙ የስራ አፈፃፀምና ቀጣይ የስራ አቅጣጫዎች ላይ ውይይት ተደረገ
ግንቦት 18/2018 ዓ.ም አዲስ አበባ፣
የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ባለፉት ሶስት ተከታታይ ዓመታት ባከናወናቸው የስታቲስቲክስ ልማት ፕሮግራም የጥናትና ቆጠራዎች አፈፃፀም ቀርቦ ቀጣይ የስራ አቅጣጫ ላይ ከተቋሙ ዋና መስሪያ ቤት መላ ፈፃሚ ጋር ውይይት ተደረገ።

መድረኩን በንግግር የከፈቱት የስታቲስቲክስ ዲጂታላይዜሽን ዘርፍ ም/ዋና ዳይሬክተር ክብርት ዶ/ር ሜሮን ክፈለው ተቋማችን ባለፉት ሶስት ዓመታት ያከናወናቸውን ጥናቶችና ቆጠራዎች በስኬት መጠናቀቅ የሁሉም ባለሙያ የጎላ ተሳትፎ ውጤት መሆኑ እና ቀጣይ ከዚህ በተሻለ ለመስራት በስራ ክፍሎች መካከል የዕውቀት ሽግግር እንዲኖር በማድረግና የበለጠ በቅንጅት ለመስራት ለመዘጋጀት ታስቦ የተፈጠረ መድረክ መሆኑን ገልፀዋል።

በመድረኩ ከጥናቶች ስነ ዘዴ፣ ከቴክኖሎጂ አጠቃቀም አንፃር፣ ከመረጃ አሰባሰብና አመዘጋገብ፣ አማራጭ የመረጃ ምንጮች ፣ የመረጃ ተደራሽነት፣ ከመረጃ አስተዳደር ማዕቀፍ አንፃር የተሰሩ ዋና ዋና ስራዎች ላይ ገለፃዎች ቀርበው ግንዛቤ ተፈጥሯል።

የተቋሙ ዋና ዳይሬክተር ክቡር ዶ/ር በከር ሻሌ በመድረኩ ማጠቃለያ ተቋሙ በስታቲስቲክስ ልማት ፕሮግራም የታቀዱ ስራዎችን ለመፈፀም የተቻለው የአመራሩ እና ፈጻሚው ርብርብ ፣ የባለድርሻ አካላት በቅንጅት በመስራት ፣ በዘመናዊ ቴክኖሎጂዎች መታገዝ ፣ አማራጭ የመረጃ ምንጮችን በመጠቀም የተሰጠውን ኃላፊነቱን የተወጣ መሆኑን ገልፀዋል።

በተጨማሪም ይህን ስኬት መነሻ በማድረግ በየደረጃ ያሉት ፈጻሚዎች በቀጣይ የበለጠ በመነሳሳት ፣የተሻሉ የቴክኖሎጂ አማራጮችን በመጠቀም ወደ ልህቀት የምናደርገውን ጉዞ ለማሳካትና የሀገራችንን የመረጃ ሉዓላዊነት ለማፅናት እና ለማላቅ ሁሉም አካላት በጋራ መስራት አለብን ሲሉ የስራ አቅጣጫ ተሰጥተዋል። ተሳታፊዎቹም ዝግጁነታቸውን የገለጹ ሲሆን የተፈጠረውን ተነሳሽነት ወደ ተሻለ ደረጃ ማሻገር እንደሚገባ ስምምነት ላይ ተደርሷል።

23/05/2026
ተቋማቱ በጋራ ለመስራት የሚያስችል የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረሙ                  ግንቦት 14/2018 ዓ.ም አዲስ አበባ፣የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ከኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚ...
23/05/2026

ተቋማቱ በጋራ ለመስራት የሚያስችል የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረሙ
ግንቦት 14/2018 ዓ.ም አዲስ አበባ፣
የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ከኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ጋር በሀገራችን በምርምርና ልማት ዘርፍ ያለውን የመረጃ ክፍተት የሚሞላ ብሔራዊ የምርምርና ልማት ጥናት በጋራ ለማካሄድ የሚያስችል የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረመ።

ስምምነቱን የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዶ/ር በለጠ ሞላ እና የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር በከር ሻሌ በጋራ ፈርመውታል።

የጥናቱ ዋና ዓላማ የምርምርና ልማት ወጪን ከሀገር ውስጥ ጠቅላላ ምርት አንፃር ለመለካት፣ በዘርፉ የተሰማሩ ባለሙያዎችን ብዛት ለማወቅ፣ የምርምር ዓይነቶችን ለመለየት፣ የአሠራር ፈተናዎችንና ክፍተቶችን በማጥናት መነሻ አመልካች መረጃ ለማዘጋጀትና ከጥናቱ ከተገኙት መረጃዎች በመነሳት ተግባራዊ የሚሆኑ የፖሊሲ ምክረ-ሀሳቦችን ማቅረብ ሲሆን መረጃው ከንግድ ድርጅቶች፣ ከከፍተኛ የትምህርት ተቋማት፣ ከመንግሥት መሥሪያ ቤቶችና ለትርፍ ያልተቋቋሙ የግል ድርጅቶች እንደሚሰበሰብ በፊርማ ስነ-ስርዓቱ ላይ ተገልጿል።

ጥናቱ ለ2030 የዘላቂ ልማት ግቦች (ለኢንዱስትሪ፣ ፈጠራና መሠረተ ልማት)፣ ለአፍሪካ አጀንዳ 2063 የሳይንስ፣ ቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ስትራቴጂ)፣ ለሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ እና ለኢትዮጵያ የ10 ዓመት መሪ የልማት ዕቅድ ስኬት ከፍተኛ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው ተገልጿል።

22/05/2026
22/05/2026
22/05/2026
22/05/2026

Address

Piassa
Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethiopian Statistical Service-ESS posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Ethiopian Statistical Service-ESS:

Share