06/09/2026
የእመርታ ቀንን በማስመልከት የከተማ ግብርና እና የከብት ማድለብ ሥራ ጉብኝት ተካሄደ
የእመርታ ቀንን ምክንያት በማድረግ በወረዳው የሚከናወኑ የከተማ ግብርና እና የከብት ማድለብ ሥራዎች የመስክ ጉብኝትና የማነቃቂያ ሥራ ተካሄደ።
በጉብኝቱም የከተማ ግብርና ሥራዎች ለምግብ ዋስትና፣ ለገቢ ማስገኛ እና ለኑሮ መሻሻል የሚኖራቸውን አስተዋፅዖ በማጠናከር፣ በተለይም የከብት ማድለብ ሥራን በዘመናዊና በንግድ አስተሳሰብ እንዲመሩ ለሚሳተፉ አካላት የማነቃቂያና የሙያ ድጋፍ ተሰጥቷል።
በመስክ ላይ ያሉ ሥራዎች አፈጻጸም ተመልክቶ ያሉ ተግዳሮቶችን በመለየት የመፍትሔ አቅጣጫዎች ተመክረዋል። የከተማ ግብርናን በማስፋፋት ምርታማነትን ማሳደግ፣ የሥራ ዕድልን መፍጠር እና የነዋሪዎችን ገቢ ማሳደግ እንደሚገባም ተጠቁሟል።
የእመርታ ቀንም የተመዘገቡ ውጤቶችን በመገምገም ቀጣይ የሥራ አቅጣጫዎችን ለማስቀመጥ እና ተግባራዊ ውጤቶችን ለማስፋት የሚያግዝ መድረክ መሆኑ ተገልጿል።