28/04/2026
የቦሌ ክፍለ ከተማ የመሬት ልማትና አስተዳደር ቅ/ጽ/ቤት የ9 ወራት የሥራ አፈፃፀም ግምገማ አካሄደ
"አገልጋይነትን መላበስ መለያችን ሊሆን ይገባል" — አቶ ቤኪ ቱጁ
ሚያዚያ 20/2018 ዓ.ም
የቦሌ ክፍለ ከተማ የመሬት ልማትና አስተዳደር ቅ/ጽ/ቤት የዘጠኝ ወራት ዋና ዋና ተግባራት አፈፃፀም ግምገማ ዛሬ ተካሂዷል። መድረኩን የመሩት የጽህፈት ቤቱ ኃላፊ አቶ ቤኪ ቱጁ እንደገለጹት፣ ተቋሙ የአገልግሎት አሰጣጡን ለማዘመን እያከናወነ ያለው የሪፎርም ስራ ተስፋ ሰጪ ውጤቶች እያሳየ ቢሆንም፣ አሁንም ተገልጋዩ ካለው ፍላጎት አንጻር በቂ አይደለም ያሉ ሲሆን አመራር እና ፈጻሚውም አገልጋይነትን የተላበሱ ቅን የሆኑ እንዲሁም በየዘርፉ የሚያጋጥሙ ችግሮችን የሚፈቱ ባለጉዳይን በአግባቡ በመመሪያና አሰራር መሰረት በቅልጥፍና የሚያስተናገዱ ሊሆኑ ይገባል ብለዋል።
በውይይቱ ወቅት የተነሱ ዋና ዋና ነጥቦች መካከል የተቋሙ ውጤታማነት መለኪያ የአገልግሎቱ ፍጥነት፣ ጥራት እና የተገልጋዩ እርካታ መሆን አለበት።የተገልጋዮች ምልልስና እንግልት ለብልሹ አሰራር በር የሚከፍት በመሆኑ፣ ማንኛውም መስተንግዶ ተገልጋይን ያከበረና ግልጽነት የተሞላበት ሊሆን ይገባል።
በመሆኑም የቀጣይ 70 ቀናት የሚከናወኑ ስራዎችን አቅጣጫ ያስቀመጡ ሲሆን በበጀት ዓመቱ ቀሪ ቀናት ውስጥ ሊሰሩ የሚገባቸውን ስራዎች ቅ/ጽቤቱ በሪፎርም ስራዎቹ የታዩ ውጤቶችን በማጠናከርና ጉድለቶችን በማረም፣ ቀሪ የበጀት ዓመቱ ስራዎችን በላቀ ትጋት ለማከናወን ዝግጁ መሆኑን በመድረኩ ተገልጿል።