Addis Ababa City Land Development And Administration Bureau

Addis Ababa City Land Development And Administration Bureau Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Addis Ababa City Land Development And Administration Bureau, Government Organization, Addis Ababa.
(1)

-Ensure the effectiveness of land preparation, banking and transfer systems
-Ensure the effectiveness of redevelopment and boundary works
-Update service delivery and data management system

03/09/2026
ከመኪና ሽያጭ ጋር ተያይዞ የሕግ ጥሰቶች የሚፈጸሙ አካላት ላይ እርምጃ እየተወሰደ ነው - የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ በመዲናዋ በመኪና አስመጪዎች እና በኮሚሽን ሠራተኞች በኩል የሚፈጸምን የታ...
03/09/2026

ከመኪና ሽያጭ ጋር ተያይዞ የሕግ ጥሰቶች የሚፈጸሙ አካላት ላይ እርምጃ እየተወሰደ ነው - የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ

በመዲናዋ በመኪና አስመጪዎች እና በኮሚሽን ሠራተኞች በኩል የሚፈጸምን የታክስ ስወራ እና የግብር ማጭበርበር ድርጊት ለመግታት ጠንካራ የሕግ ማስከበር ሥራ እየሠራ መሆኑን የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ አስታወቀ።

ቢሮው በሰጠው መግለጫ እንደገለጸው፣ በርካታ የመኪና አስመጪዎች ለከተማ አስተዳደሩ የሚገባውን ወርሃዊ ቫት እና ዓመታዊ ግብር ላለመክፈል ሲሉ ሽያጮቻቸውን በኮሚሽን ሠራተኞች አማካይነት እያካሄዱ ይገኛሉ።

በተጨማሪም አብዛኞቹ አስመጪዎች አድራሻቸው ሳይታወቅ ከዋጋ በታች ደረሰኝ በመቁረጥ ከፍተኛ የግብር ስወራ ወንጀል እንደሚፈጽሙ በተካሄደው ጥናት መረጋገጡ በመግለጫው ተጠቅሷል።

በታክስ ሕጉ መሠረት በሌሎች ክልሎች የተመዘገቡ አስመጪዎች አዲስ አበባ ውስጥ ሽያጭ ለማካሄድ በሚያስችል መልኩ የክልል ንግድ ፈቃዱን ማስጠቀስ፣ የመሸጫ ቦታ መከራየት እና የሽያጭ መመዝገቢያ ማሽኖቻቸውን ማስተካከል ይጠበቅባቸዋል።

ማንኛውም አስመጪ ያስገባውን መኪና መሸጥ ያለበት በኮሚሽን ሠራተኞች አድራሻ ሳይሆን ንግድ ፈቃድ ባወጣበት ቦታ ብቻ ሊሆን እንደሚገባም ቢሮው አሳስቧል።

የኮሚሽን ንግድ ፈቃድ ያላቸው ሠራተኞችም ቢሆኑ በኮሚሽን ፈቃድ የመኪና መሸጫ ግቢዎችን ተከራይተው ከአስመጪዎች የተረከቧቸውን መኪኖች መሸጥ በሕግ ተጠያቂ የሚያደርግ የታክስ ስወራ ወንጀል መሆኑን ተገንዝበው ከድርጊቱ እንዲቆጠቡ ጥሪ ቀርቧል።

ቢሮው ከመኪና ሽያጭ ጋር ተያይዞ የሕግ ጥሰቶችን የሚፈጸሙ አካላት ላይ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመቀናጀት ሕግ የማስከበር እርምጃውን አጠናክሮ እንደሚቀጥልም ገልጿል።

03/09/2026
ማገልገልን እንደ ክብር የሚያይ አመራርና ሰራተኛ በመፍጠር በሪፎርሙ የተገኙ ውጤቶችን ማስቀጠል ያስፈልጋል። ኢንጅነር ወንድወሰን ባንጃውየአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ መሬት ልማትና አስተዳደር ቅር...
03/09/2026

ማገልገልን እንደ ክብር የሚያይ አመራርና ሰራተኛ በመፍጠር በሪፎርሙ የተገኙ ውጤቶችን ማስቀጠል ያስፈልጋል። ኢንጅነር ወንድወሰን ባንጃው

የአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ መሬት ልማትና አስተዳደር ቅርንጫፍ ጽ/ቤትም በቀጣዮቹ ሁለት ወራት የሚፈፀሙ ተግባራት ላይ ከዘርፉ አመራርና ሰራተኞች ጋር ውይይት አካሂዷል።

ነሐሴ 28/2018 (መልአ)
***************************

የመሬት ልማትና አስተዳደር ቢሮ በበጀት ዓመቱ ያቀዳቸውን የልማት፣ የመልካም አስተዳደርና የማሕበራዊ አገልግሎቶች በስኬት ለማጠናቀቅ የተለያዩ ስልቶችን ነድፎ በመንቀሳቀስ ላይ ይገኛል። የእዚሁ አካል በሆነውንና በቀጣዮቹ ሁለት ወራት በተጨባጭ በሚተገበሩ ዕቅዶች ላይም የአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ መሬት ልማትና አስተዳደር ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ከዘርፉ አመራርና ሰራተኞች ጋር ተወያይቷል።

የማፍጠኛ እቅዱ አገልግሎት አሰጣጥን በማቀላጠፍ የህብረተሰቡን የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች በአጭር ጊዜ ለመመለስ ታስቦ መዘጋጀቱን የገለፁት የመብት ፈጠራና ይዞታ አገልግሎት ዘርፍ ምክትል ቢሮ ኃላፊ ኢንጅነር ወንድወሰን ባንጃው ማገልገልን እንደ ክብር የሚያይ አመራርና ሰራተኛ በመፍጠር በሪፎርሙ የተገኙ ውጤቶችን ማስቀጠል እንደሚገባ አሳስበዋል።

ዕቅዱን በውጤት ለማጠናቀቅና በሠራተኛው ላይ የሚስተዋሉትን የአመለካከት፣ የክህሎትና የስነ-ባህሪ ችግሮች በሚገባ ለይቶ በማረም በዘርፉ የሚስተዋሉ የአገልግሎት አሰጣጥ ግድፈቶችን ደረጃ በደረጃ የማረም ስራ በትኩረት ይሰራል ያሉት ደግ ሞየቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ ኃላፊ ወ/ሮ ትዕግስት አበራ ናቸው ።
ለበለጠ መረጃ ትስስር ገፆቻችንን Like, Follow, subscribe በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ።

👇👇👇👇👇👇👇
Website: - https://www.aalb.gov.et
https://linktr.ee/addisabababacityland
Email: [email protected]

በተጠናቀቀው በጀት ዓመት የተጀመረው የቀበሌ ቤቶች የካርታ ዝግጅት ተጠናክሮ ይቀጥላል ። የአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ መሬት ልማትና አስተዳደር ቅርንጫፍ ጽ/ቤት።ነሐሴ 28/2018 (መልአ) # ...
03/09/2026

በተጠናቀቀው በጀት ዓመት የተጀመረው የቀበሌ ቤቶች የካርታ ዝግጅት ተጠናክሮ ይቀጥላል ። የአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ መሬት ልማትና አስተዳደር ቅርንጫፍ ጽ/ቤት።

ነሐሴ 28/2018 (መልአ)
# # # # # # # # # # # # # #

በተጠናቀቀው 2018 በጀት ዓመት የተጀመረው የቀበሌ ቤቶች የካርታ ዝግጅትና የይዞታ ማረጋገጫ ስራ በተያዘው በጀት ዓመትም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል በመሬት ልማትና አስተዳደር ቢሮ የአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ገልጿል።

የቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ ኃላፊ ወ/ሮ ፍቅርአዲስ አባይነህ እንደገለፁት ፤ የካርታ ዝግጅቱ ዋና ዓላማ የመንግሥትና የህዝብ ሀብት የሆኑ የቀበሌ ቤቶችን በህጋዊ መንገድ ለመመዝገብና ህገወጥ አሰራርን ለመግታት አንዲሁም ለአገልግሎት አሰጣጡ ግልጽነትና ቅልጥፍናን ለመፍጠር ነው ።

እንደ 2018 በጀት ዓመት ሁሉ በ2019 በጀት ዓመትም በክፍለ ከተማው የሚገኙ ከ18ሺህ በላይ የቀበሌ ቤቶችን ወደ ዲጅታል የመረጃ አያያዝ ስርዓት ለማስገባት መታቀዱንም ጠቁመዋል ።

አገልግሎቱ ከክፍለ ከተማው የቤቶች ልማት አስተዳደር በኩል የታደሰ የኪራይ ውል መረጃ ተደራጅቶ ሲላክ እንደሚሰጥ ያነሱት ወ/ሮ ፍቅርአዲስ የካርታ ዝግጅቱ የከተማውን የመሬትና ቤቶች አስተዳደር ዘመናዊ ለማድረግ በሚደረገው ጥረት ትልቅ አበርክቶ እንደሚኖረው ገልጸዋል ።

ከዚህ በተጨማሪ ቢሮው በተጠናቀቀው በጀት ዓመት አገልግሎት አሰጣጥን ይበልጥ ለማቀላጠፍ እና ብልሹ አሰራርን ለመቆጣጠር ባሻሻለው ሲስተም በመታገዝ ለጋራ መኖሪያ ቤቶችና የሪል ስቴት የተናጠል ካርታ ህትመት በትኩረት እንደሚሰራ ከቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ ኃላፊ ማብራሪያ ለመረዳት ተችሏል ።

ለበለጠ መረጃ ትስስር ገፆቻችንን Like, Follow, subscribe በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ
👇👇👇👇👇👇👇
Website: - https://www.aalb.gov.et
https://linktr.ee/addisabababacityland
Email: [email protected]

Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Addis Ababa City Land Development And Administration Bureau posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Addis Ababa City Land Development And Administration Bureau:

Shortcuts

Share