Addis ketema Wereda 13 Communication

Addis ketema Wereda 13 Communication This is Addis Ketema Sub-city wereda 13 Communication Offical page,Come and join us!

ኢትዮጵያውያን መርጠዋል፤ ኢትዮጵያ አሸንፋለች!ኢትዮጵያ ከዜጎቿ የፈለገችዉን ኹሉ በፈለገችው ጊዜና ኹኔታ የምታገኝ ሀገር ናት፡፡ ለሀገራቸዉ የተጠየቁትን ሁሉ ለመስጠት ወደኋላ የማይሉ ዜጎች ስ...
02/06/2026

ኢትዮጵያውያን መርጠዋል፤ ኢትዮጵያ አሸንፋለች!

ኢትዮጵያ ከዜጎቿ የፈለገችዉን ኹሉ በፈለገችው ጊዜና ኹኔታ የምታገኝ ሀገር ናት፡፡ ለሀገራቸዉ የተጠየቁትን ሁሉ ለመስጠት ወደኋላ የማይሉ ዜጎች ስላሏት በእጅጉ ኮርታለች፡፡ ከዓድዋ እስከ ሕዳሴ ግድብ፣ ከወገን ለወገን መረዳዳት እስከ አረንጓዴ ዐሻራ የዜጎቿን ተሳትፎ ጠይቃ፣ ከመሻቷ በላይ ተሳትክቶላታል፡፡ ዛሬ የተደገመዉም ይኸው ነው፡፡

ኢትዮጵያ ኢትዮጵያዊ ዴሞክራሲን ማንበር፣ በግልጽና ዴሞክራሲያዊ ምርጫ መንግሥትን መምረጥ፣ ሕገ መንግሥታዊነትን ፅኑ መሠረት ማስያዝ ትሻለች፡፡ ለዚህ ደግሞ 7ኛዉን ሀገራዊ ምርጫ እንደ ትልቅ አጋጣሚ መጠቀም አስፈልጓት ነበር፡፡

በምላሹም ከ54 ሚሊዮን በላይ ዜጎች ለመራጭነት ተመዝግበው የዛሬዋን ቀን ሲጠባበቁ ቆይተዋል፡፡ እነሆ የእናት ሀገር ጥሪን በመቀበል ዜጎች በነቂስ ወጥተው ሲመርጡ ውለዋል፤ ሌሊቱንም አጋምሰዋል፡፡ በኢትዮጵያ የምርጫ ታሪክ ዜጎች ለረዥም ሰዓታት ተሰልፈዉ ድምፅ የሰጡበት ልዩ ምርጫም ነው፡፡

ምርጫዉ እንዳይካሄድ ባዳ እና ባንዳ ተቀናጅተዉ ያልቆፈሩት ጉድጓድ፣ ያልደረደሩት እንቅፋት አልነበረም፡፡ ነገር ግን ኢትዮጵያ ለጠራችው ሀገር ወዳድ ኢትዮጵያዊ የማይቻል ነገር አልነበረምና በስኬት ተጠናቅቋል፡፡ ኢትዮጵያውን በሰላማዊ መንገድ መርጠው ኢትዮጵያ አሸንፋለች፡፡

የኢትዮጵያን የዴሞክራሲያዊ ምርጫ ጥሪ ተቀብሎ ከንጋት እስከ ምሽት በመምረጥ ምላሽ ለሰጠው ሕዝብ፣ ሕገ መንግሥታዊ ሥርዐቱ እንዲጸና እና ዜጎች በሰላም እንዲመርጡ ምቹ ዓውድ ለፈጠሩ የፀጥታ አካላት፣ ወቅታዊና ትክክለኛ መረጃ በየደቂቃዉ ሲያደርሱ ለነበሩ የመገናኛ ብዙኃን ተቋማት እንዲሁም የምርጫዉን ሂደት ለመሩ፣ ላስተባበሩ እና ለታዘቡ ሁሉ ኢትዮጵያ ታመሰግናለች፡፡

የኢፌዴሪ መንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት

ግንቦት 25 2018፣አዲስአበባ፣ኢትዮጵያ

የኢትዮጵያ ሕዝብ አስደናቂም ተአምረኛም ሕዝብ ነው። ከፈጣሪ በቀር ሕዝባችንን አሟልቶ ሊያውቅና ሊገመግም የሚችል ማን ነው? የዳበረ ባህል፣ ሀገር ወዳድና የወል መሻቱን መጠበቅ የሚችል ሕዝብ ...
01/06/2026

የኢትዮጵያ ሕዝብ አስደናቂም ተአምረኛም ሕዝብ ነው። ከፈጣሪ በቀር ሕዝባችንን አሟልቶ ሊያውቅና ሊገመግም የሚችል ማን ነው? የዳበረ ባህል፣ ሀገር ወዳድና የወል መሻቱን መጠበቅ የሚችል ሕዝብ መሆኑን በዘንድሮው ምርጫ ዳግም ለዓለም አሳይቷል። በዛሬው ታሪካዊ ዕለት፡-

• የሌሊቱ ብርድና ጨለማ ያላስፈራቸው፣
• የቀትሩ ፀሐይና ድንገተኛ ዝናብ ያልበገራቸው
• ሠርግ፣ ኀዘን፣ ወሊድና ሌሎች ማኅበራዊ ሁነቶች ያላገዳቸው፣
• ረጃጅም ሰልፎች ያላታከታቸው፣
• የአካል ጉዳት ድምጽ ለመስጠት ያልገደባቸው፣
• ሕመም እና እርጅና የሀገር ተስፋን ከማየት ያላገዳቸው፣
• የነገ ሀገር ተረካቢ ጨቅላ ልጃቸውን ማዘል ያላደከማቸው፣
• ከምንም በላይ የጠላት ጩኸትና ማስፈራሪያ ያላስቆማቸው ዜጎች፤

በብዙ ውጣ ውረዶች መካከል (against all odds) ያሳያችሁት ጽናት ለዴሞክራሲና ለሀገር ሕልውና የተከፈለ ነውና ከልብ የመነጨ ምስጋና ይገባቸዋል፡፡

ይሄንን ሕዝብ ማገልገል መታደል ነውና ተመራጮች ያከበራችሁን አክብራችሁ ለዴሞክራሲ ሥርዓት ዋጋ የከፈለውን ይሄንን ሕዝብ በንጽሕና ለማገልገል ያብቃችሁ።

The people of Ethiopia are an extraordinary and remarkable people. Other than the Creator, who can truly know and assess our people in their entirety? Through this year’s election, Ethiopians have once again shown the world that they are a people with a rich culture, deep patriotism, and the ability to safeguard the common good.

On this historic day:

* Citizens who were not intimidated by the cold and darkness of the night,
* Who were not deterred by the midday sun or sudden rain,
* Whom weddings, funerals, childbirth, and other social obligations did not prevent from participating,
* Who were not wearied by long lines,
* Whose physical disabilities did not stop them from casting their vote,
* Those whose illness and old age did not prevent from witnessing the hope of their country,
* Who were not exhausted by carrying their infant children; the future inheritors of the nation,
* And above all, whom the shouting and threats of enemies could not intimidate or stop;

The perseverance you demonstrated amid many challenges and hardships, against all odds, was a contribution made for democracy and for the very survival of the nation. For this, you deserve heartfelt gratitude.

It is a privilege to serve such a people. Therefore, may those who have been elected honor the trust placed in them and serve this people, with integrity and sincerity! A people

ድምፅ ሳንሰጥ ወደ ቤት መግባት የማይታሰብ ነው ሲሉ የአዲስ ከተማ ክ/ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ::በአዲስ ከተማ ክ/ከተማ የሚገኙ  ነዋሪዎች ዲሞክራሲያዊ መብታቸውን በመጠቀም ኢትዮጵያን ለማጽናት...
01/06/2026

ድምፅ ሳንሰጥ ወደ ቤት መግባት የማይታሰብ ነው ሲሉ የአዲስ ከተማ ክ/ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ::

በአዲስ ከተማ ክ/ከተማ የሚገኙ ነዋሪዎች ዲሞክራሲያዊ መብታቸውን በመጠቀም ኢትዮጵያን ለማጽናት በምሽትም ድምፃቸውን እየሰጡ ይገኛሉ::

በክፍለ ከተማው በሚገኙ በሁሉም የምርጫ ጣቢያዎች ድምፅ የመስጠት ሂደቱ አሁንም በከፍተኛ መነሳሳት ቀጥሏል።

የኢትዮጵያ ሕዝብ አስደናቂም ተአምረኛም ሕዝብ ነው። ከፈጣሪ በቀር ሕዝባችንን አሟልቶ ሊያውቅና ሊገመግም የሚችል ማን ነው? የዳበረ ባህል፣ ሀገር ወዳድና የወል መሻቱን መጠበቅ የሚችል ሕዝብ ...
01/06/2026

የኢትዮጵያ ሕዝብ አስደናቂም ተአምረኛም ሕዝብ ነው። ከፈጣሪ በቀር ሕዝባችንን አሟልቶ ሊያውቅና ሊገመግም የሚችል ማን ነው? የዳበረ ባህል፣ ሀገር ወዳድና የወል መሻቱን መጠበቅ የሚችል ሕዝብ መሆኑን በዘንድሮው ምርጫ ዳግም ለዓለም አሳይቷል። በዛሬው ታሪካዊ ዕለት፡-

• የሌሊቱ ብርድና ጨለማ ያላስፈራቸው፣
• የቀትሩ ፀሐይና ድንገተኛ ዝናብ ያልበገራቸው
• ሠርግ፣ ኀዘን፣ ወሊድና ሌሎች ማኅበራዊ ሁነቶች ያላገዳቸው፣
• ረጃጅም ሰልፎች ያላታከታቸው፣
• የአካል ጉዳት ድምጽ ለመስጠት ያልገደባቸው፣
• ሕመም እና እርጅና የሀገር ተስፋን ከማየት ያላገዳቸው፣
• የነገ ሀገር ተረካቢ ጨቅላ ልጃቸውን ማዘል ያላደከማቸው፣
• ከምንም በላይ የጠላት ጩኸትና ማስፈራሪያ ያላስቆማቸው ዜጎች፤

በብዙ ውጣ ውረዶች መካከል (against all odds) ያሳያችሁት ጽናት ለዴሞክራሲና ለሀገር ሕልውና የተከፈለ ነውና ከልብ የመነጨ ምስጋና ይገባቸዋል፡፡

ይሄንን ሕዝብ ማገልገል መታደል ነውና ተመራጮች ያከበራችሁን አክብራችሁ ለዴሞክራሲ ሥርዓት ዋጋ የከፈለውን ይሄንን ሕዝብ በንጽሕና ለማገልገል ያብቃችሁ።

The people of Ethiopia are an extraordinary and remarkable people. Other than the Creator, who can truly know and assess our people in their entirety? Through this year’s election, Ethiopians have once again shown the world that they are a people with a rich culture, deep patriotism, and the ability to safeguard the common good.

On this historic day:

* Citizens who were not intimidated by the cold and darkness of the night,
* Who were not deterred by the midday sun or sudden rain,
* Whom weddings, funerals, childbirth, and other social obligations did not prevent from participating,
* Who were not wearied by long lines,
* Whose physical disabilities did not stop them from casting their vote,
* Those whose illness and old age did not prevent from witnessing the hope of their country,
* Who were not exhausted by carrying their infant children; the future inheritors of the nation,
* And above all, whom the shouting and threats of enemies could not intimidate or stop;

The perseverance you demonstrated amid many challenges and hardships, against all odds, was a contribution made for democracy and for the very survival of the nation. For this, you deserve heartfelt gratitude.

It is a privilege to serve such a people. Therefore, may those who have been elected honor the trust placed in them and serve this people, with integrity and sincerity! A people

በድጋሚ የተሰጠ መግለጫየኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዛሬ ሰኞ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. ከማለዳ 12:00 ሰዓት ጀምሮ እስከ ምሽት 12:00 ሰዓት የ7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ድምፅ የማስ...
01/06/2026

በድጋሚ የተሰጠ መግለጫ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዛሬ ሰኞ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. ከማለዳ 12:00 ሰዓት ጀምሮ እስከ ምሽት 12:00 ሰዓት የ7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ድምፅ የማስፈጸም ሂደት ላይ እንደነበር ይታወቃል። ቦርዱ በሥምሪት ላይ ያለው የክትትል ቡድኑ ያቀረበለትን ሪፖርት ተመልክቶ የሚከተለውን ወሥኗል።

በኢትዮጵያ የምርጫ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና የምርጫ ሥነ-ምግባር ዐዋጅ 1162/2011 አንቀጽ 49(4) መሠረት ቦርዱ የምርጫው ነፃና ፍትሐዊነት ይበልጥ ያሰፍናል ብሎ ካመነ የድምፅ መስጫ ሰዓቱን ሊያራዝም እንደሚችል በግልጽ ይደነግጋል። በመሆኑም የድምፅ መስጫ ሂደት ባልተጠናቀቀባቸው የምርጫ ጣቢያዎች ላይ ድምፅ የመስጠት ሂደቱ እስከ ዕኩለ ለሊት 6:00 ሰዓት ድረስ የተራዘመ መሆኑን ቦርዱ ያሳውቃል።

ማሳሰቢያ: የተመዘገቡ መራጮች መርጠው የተጠናቀቁባቸው ጣቢያዎች ላይ አስፈጻሚዎች የድምፅ ቆጠራ ሂደቱን እንዲያከናውኑ ቦርዱ ያስታውሳል።

በአዲስ ከተማ ክ/ከተማ የድምፅ አሰጣጥ ሂደት በአመሻሹም ቀጥሏልበክፍለ ከተማው በሚገኙ የምርጫ ጣቢያዎች 7ኛው ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫ የድምፅ አሰጣጥ ሒደቱ በአመሻሹም ተጠናክሮ እንደቀጠለ ነው...
01/06/2026

በአዲስ ከተማ ክ/ከተማ የድምፅ አሰጣጥ ሂደት በአመሻሹም ቀጥሏል

በክፍለ ከተማው በሚገኙ የምርጫ ጣቢያዎች 7ኛው ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫ የድምፅ አሰጣጥ ሒደቱ በአመሻሹም ተጠናክሮ እንደቀጠለ ነው።



​የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ መራጩ ህዝብ በሙሉ መርጦ እስኪያጠናቅቅ ድረስ የድምፅ አሰጣጥ ሰዓቱን ማራዘሙን ተከትሎ በአሁኑ ሰዓትም በክፍለ ከተማው በሚገኘው በእያንዳንዱ የምርጫ ጣቢያ ሂደቱ በሰላማዊ ሁኔታ እየተከናወነ ይገኛል

በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ወረዳ 13 የሚገኘው የምርጫ ክልል 25 በ17ቱ የምርጫ ጣቢያዎችን  የምርጫ ሂደቱ እንደቀጠለ ነዉ ።
01/06/2026

በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ወረዳ 13 የሚገኘው የምርጫ ክልል 25 በ17ቱ የምርጫ ጣቢያዎችን የምርጫ ሂደቱ እንደቀጠለ ነዉ ።

በአዲስ ከተማ ክ/ከተማ በሚገኙ ሁሉም ወረዳዎች ድምፅ የመስጠቱ ሂደቱ ተጠናክሮ እንደቀጠለ ነዉ፡፡ የክፍለ ከተማው ነዋሪዎች ህገ-መንግስቱ የሰጣቸዉን መብት በመጠቀም ከነፍሰ ጡር እስከ አካል ...
01/06/2026

በአዲስ ከተማ ክ/ከተማ በሚገኙ ሁሉም ወረዳዎች ድምፅ የመስጠቱ ሂደቱ ተጠናክሮ እንደቀጠለ ነዉ፡፡

የክፍለ ከተማው ነዋሪዎች ህገ-መንግስቱ የሰጣቸዉን መብት በመጠቀም ከነፍሰ ጡር እስከ አካል ጉዳተኛ እንዲሁም ሌሎች የህብረተሰብ ክፍሎች ድምፃቸዉን እየሰጡ ይገኛሉ፡፡

ምርጫው ሰላማዊ፣ ዴሞክራሲያዊና ነጻ በሆነ መንገድ እየተካሄደ ነው - የአዲስ አበባ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ም/ቤት AMN - ግንቦት 24/2018 ዓ.ም7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊ፣ ዴሞክራሲ...
01/06/2026

ምርጫው ሰላማዊ፣ ዴሞክራሲያዊና ነጻ በሆነ መንገድ እየተካሄደ ነው - የአዲስ አበባ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ም/ቤት

AMN - ግንቦት 24/2018 ዓ.ም

7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊ፣ ዴሞክራሲያዊና ነጻ በሆነ መንገድ እየተከናወነ መሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት አስታወቀ።

ምክር ቤቱ ይህንን የገለጸው በኢትዮጵያ የምርጫ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ በተቋቋመውና የምርጫ ሂደቱን በቀጥታ በሚከታተልበት የክትትል ክፍል በሰጠው መግለጫ ነው።

በመግለጫው፤ መራጩ ሕዝብ የዴሞክራሲ ሥርዓት እንዲሰፍን ከፍተኛ ጨዋነት በተሞላበት መልኩ ከሌሊቱ 9 ሰዓት ጀምሮ ከቤቱ በመውጣት ድምፅ ሲሰጥ መቆየቱን ጠቅሶ ለዚህም ምስጋና አቅርቧል።

የፖለቲካ ፓርቲዎች አማራጭ ሐሳባቸውንና ርዕዮተ-ዓለማቸውን በመገናኛ ብዙኃን አማካኝነት ካስተዋወቁ በኋላ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ሕዝብ ለመራጭነት መመዝገቡን ያስታወሰው ምክር ቤቱ፣ ዛሬ እስከ እኩለ ቀን ባለው ሂደትም ሂደቱ ፍጹም ሰላማዊ ሆኖ መዋሉን ገልጿል።

ምክር ቤቱ በሁሉም ክፍለ ከተሞች ባለው መዋቅር አማካኝነት መረጃዎችን ሲለዋወጥና ሂደቱን ሲከታተል እንደነበር የጠቆመ ሲሆን፤ እስካሁን ባለው ሂደት የጸጥታ አካላት፣ ታዛቢዎች እንዲሁም በጎ ፈቃደኞች እያደረጉ ባለው ገለልተኛ አገልግሎት መደሰቱንም አስታውቋል።

በቀሪው የድምፅ አሰጣጥ ሂደትም ህዝቡ እስካሁን ባለው ጨዋነትና ትዕግሥት የዜግነት ግዴታውን እንዲወጣ የጋራ ምክር ቤቱ ጥሪውን አቅርቧል።

በአንዋር አህመድ

Address

Winget
Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Addis ketema Wereda 13 Communication posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Addis ketema Wereda 13 Communication:

Share