03/09/2026
በአ/ከ/ክ/ከ ወረዳ 13 እና ወረዳ 14 አስተዳደር የሰላም ሰራዊት አባላትን ውጤታማነት ለማሳደግ የጋራ የሆነ "የአንድ ማዕከል ስምሪት" ተሰጠ።
በአካባቢ ሰላምና ጸጥታ በማስጠበቅና ዘላቂ ሰላምን ለማረጋገጥ የተሰማሩ የሰላም ሰራዊት አባላት ስራቸውን ይበልጥ በተቀናጀ እና በታቀደ መልኩ ማከናወን እንዲችሉ የሚያስችል "የአንድ ማዕከል ስምሪት ተሰጠ።
ይህ የስምሪት መድረክ በዋናነት መጪውን አዲስ አመት ያለምንም የፀጥታ ስጋት በሰላም እንዲከበር የሰላም ሰራዊቱን አደረጃጀት ለማበረታትና እንዲሁም መረጃዎችን በፍጥነት ለመለዋወጥና ለጸጥታ ስጋቶች አፋጣኝ ምላሽ ለመስጠት ያለመ መሆኑ ተመላክቷል።
የአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ወረዳ 13 ሰላምና ፀጥታ ኃላፊ አቶ አስፍው ተፍሪ ለአካባቢው ሰላም አስተማማኝ ዋስትና የሚሰጥ ስራ መሆኑን እና አባላቱም ከህዝቡ ጋር ያላቸውን ግንኙነት በማጠናከረሰ አስተዳደሩም የሰላም ሰራዊት ስምሪቱን ከመቼውም በላይ አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልፀዋል ።
የሰላም ሰራዊት አባላቱ በበኩላቸው የተሰጣቸውን መመሪያ መሰረት በማድረግ ፣ የአካባቢያቸውን ሰላም በንቃት ለመጠበቅና ማንኛውንም የጸጥታ ችግር ለመከላከል ዝግጁ መሆናቸውን አረጋግጠዋል።
ነሀሴ 28/12/2018