Addis Ketema Communication-አዲስ ከተማ

Addis Ketema Communication-አዲስ ከተማ This is Addis Ketema Sub-city Communication Office's Offical page,Come and join us!
(2)

በአዲስ ከተማ ክ/ከተማ የጷጉሜ 3 የፅናት ቀን በሰንደቅ ዓላማ መስቀልና ሌሎች ዝግጅቶች በድምቀት ተከበረ።********************* ጷጉሜ 3 -2018 ዓ.ም ሁሉም የክፍለ ከተማ አስ...
08/09/2026

በአዲስ ከተማ ክ/ከተማ የጷጉሜ 3 የፅናት ቀን በሰንደቅ ዓላማ መስቀልና ሌሎች ዝግጅቶች በድምቀት ተከበረ።
*********************
ጷጉሜ 3 -2018 ዓ.ም

ሁሉም የክፍለ ከተማ አስተዳደሩ ሰራተኞችና አመራሮች እንዲሁም የአስተባባሪ ኮሚቴ አባላትና የምክር ቤቱ ዋና አፈጉባኤ አቶ በቀለ ጉታ በተገኙበት የጷጉሜ 3 የፅናት ቀን ሰንደቃላማ በመስቀልና በሌሎች ዝግጅቶች በደማቅ ሁኔታ ተከብሯል::

በመንገዳችን ለሚገጥሙን እንቅፋቶች ሳንበገር በፅናትና በአይበገሬነት መንፈስ መሻገር ይገባል ያሉት የክፍለ ከተማው ምክትል ሥራ አስፈጻሚና የሥራ ክህሎት ጽ/ቤት ኃላፊ ወ/ሮ እቴማር ጌታቸው አባቶቻችን ደማቸውን አፍሰውና አጥንታቸውን ከስክሰው ያስረከቡን ሀገር መገለጫ የሆነውን ባንዲራ መጠበቅና ከፍ ማድረግ ከአሁኑ ትውልድ የሚጠበቅ ተግባር ነው ብለዋል።

የአዲስ ከተማ ክ/ከተማ ሰላምና ፀጥታ ጽ/ቤት ኃላፊ ዶ/ር ጥበቡ ደጀኔ በበኩላቸው ሀገራችን ኢትዮጵያ ብዙ ዋጋ የተከፈለባት መሆኗን ጠቅሰው በቀጣይም የዛሬው የፅናት ቀን የኢትዮጵያውያንን አንድነት እና ፈተናዎችን አልፎ ለልማት የመቆም ባህልን የሚያሳይ ነው ሲሉ ገልፀዋል።

የጳጉሜ 3 የፅናት ቀን ለኢትዮጲያ ማንሰራራት መሰረት የሆነዉ ፅናታችን የሉዓላዊነታችን መሰረት መሆኑ እንዲሁም የኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ የሐገራችን ሉዓላዊነት መገለጫና የዜጎቿ ፅናት ምስክር ነው ተብሏል።

በተያያዘ ዜና የጳጉሜ 3 የፅናት ቀን በአዲስ መሶብ አዲስ ከተማ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት በሰንደቃላማ መስቀልና ሌሎች ዝግጅቶች ተከብሯል::

# # # # # # # # # # # # # #
መረጃን ከምንጭ በተለያየ አማራጭ
https://linktr.ee/Addis_Ketema_Communication

08/09/2026

ጳጉሜን 3 "ለጽናት" ቀን

ፈተናዎችን ሁሉ በፅናት በመሻገር የኢትዮጵያን ብልፅግና እውን ይሆናል!

"ጽናት" ለእኛ ኢትዮጵያውያን ተራ ቃል ሳይሆን የህልውናችን ጽኑ መሰረት፣ ዘመናትን በአሸናፊነት የተሻገርንበት የታሪካችን ህያው ማህተም ነው። ሀገራችን ኢትዮጵያ በረዥም ታሪኳ በርካታ ውጫዊና ውስጣዊ ፈተናዎችን፣ የባዳና ባንዳ ሴራና አሻጥር በተደጋጋሚ አስተናግዳለች። ይሁን እንጂ ወደ ኋላ ሊጎትቷት የተዘረጉ እኩይ እጆችን ሁሉ በማይበገር ጽናት ተጋፍጣ አክሽፋለች። ማዕበልና ወጀብ ጉዞዋን ሳያስተጓጉለው፣ ተግዳሮቶችን ወደ መወጣጫነት በመቀየር አዲሲቷንና የበለጸገችውን ኢትዮጵያን እውን እያደረገች ትገኛለች።

የኛ የኢትዮጵያውያን የጽናት እሴታችን በጋራ ዓላማ መቆምን፣ የህብረትን ጥንካሬን፣ ክቡር መስዋዕትነትን እና በታሪክ ፈተናዎች ውስጥ ሳይበገሩ አብሮ መጽናትን በጉልህ የሚያሳይ ነው። በመሆኑም በዛሬው ታሪካዊ የጽናት ቀን፣ ኢትዮጵያን በታማኝነትና በጀግንነት እያገለገሉ ላሉት የቁርጥ ቀን ልጆች ልዩ ክብርና ሞገስ እንሰጣለን።

እንደ ሁልጊዜው ሁሉ በዳር ድንበር፣ በዱር በገደሉ፣ ቀን ከፀሐይ ግለት ሌሊት ከቁርና ከብርድ ጋር ታግለው፣ ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይሉ የሀገርን ሉዓላዊነት በጽናት ለሚጠብቁ ጀግኖቹ የመከላከያ ሰራዊት፣ የፖሊስና አጠቃላይ የፀጥታ አካላት ኢትዮጵያ ላቅ ያለ ምስጋና ታቀርባለች፡፡

የነዚህ ጀግኖች ዘመናዊ ቁመናና የከፈሉት ውድ መስዋዕትነት ለሀገረ-መንግሥቱ ዘላቂነትና ለሁለንተናዊ እድገታችን ጽኑ ዋስትና እንደሆነ ሁሉ እኛም ኢትዮጵያውያን ህብረታችንን አጠናክረን የትኛውንም ፈተና በጋራ እንሻገራለን።

ኢትዮጵያ በውድ ልጆቿ ጽናት ታፍራና ተከብራ ለዘላለም ትኖራለች! ብልጽግናዋም በተባበረው ክንዳችን እውን ይሆናል፡፡

ጳጉሜን 3/2018 ዓ.ምየፅናት ቀን ፤-ለኢትዮጲያ ማንሰራራት መሰረት የሆነዉ ፅናታችን የሉዓላዊነታችን መሰረት ነው!የኢትዮጵያ ብቸኛ ወር የሆነችው የጳጉሜ ወር በከተማ አስተዳደሩ በተለያዩ ሀ...
08/09/2026

ጳጉሜን 3/2018 ዓ.ም

የፅናት ቀን ፤-ለኢትዮጲያ ማንሰራራት መሰረት የሆነዉ ፅናታችን የሉዓላዊነታችን መሰረት ነው!

የኢትዮጵያ ብቸኛ ወር የሆነችው የጳጉሜ ወር በከተማ አስተዳደሩ በተለያዩ ሀገራዊ ሁነቶች እየተከበረ ይገኛል።

ጳጉሜ 3 "የፅናት ቀን" በአዲስ አበባ ከተማ ሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ፤- የአዲስ አበባ ከተማ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ ዋና አዛዥ ሌተናል ጀነራል አስራት ዴኔሮ ፣ የአዲስ አበባ ከተማ ሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ ምክትልና የፀጥታ ኦፕሬሽን ዘርፍ ኃላፊ አቶ ተስፋዬ ደንድርን ጨምሮ ከፍተኛ የፖሊስ እና የደንብ ማስከበር አመራሮች የፀጥታ አካላት እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት በተለያዩ መርሀ ግብሮች ተክብሯል፡፡

የፀናች ሀገር መሠረት የተቋማት ጥንካሬ ብቻ ሳይሆን፣ የህዝብ አንድነት፣ኃላፊነትና ተሳትፎ ሲሆን ፅናት በፈተና ጊዜ አለመሸነፍ፣በችግር ውስጥ ተስፋን መጠበቅና የተጀመረን የለውጥ ጉዞ በጥራት እስከ መጨረሻ መፈፀምና ማስፈጸም ነው።

የዛሬ ፈተና የነገ ድል መሠረት በመሆኑ በጋራ በመተጋገዝ፣ በትዕግስትና በቁርጠኝነት ችግሮችን በመሻገር የተሻለ ነገን መገንባት እንችላለን።

የአዲስ አበባ ከተማ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ ዋና አዛዥ ሌተናል ጀነራል አስራት ዴኔሮ በመርሐ ግብሩ ላይ ተገኝተው እንደተናገሩት የአዲስ አመት መሸጋገሪያ የሆነችው የጳጉሜ ወር ቀናት በተለያዩ ሀገራዊ ድሎችን በሚዘክሩ ስያሜዎች እየተከበሩ እንደሚገኙ ጠቁመዉ ቀደምት አባቶቻችን በአንድነት ቆመው የፀናች ሀገርን እንዳስረከቡን ሁሉ የአሁኑ ትውልድም ሀገርን በሚያፀኑ የልማትና የለውጥ ስራዎች በአንድነት በመቆም የሀገርን ፅናት ማረጋገጥና ማስቀጠል ይገባል ሲሉ ገልፀዋል፡፡

ጀነራሉ አክለውም በዱር በገደሉ ሀገርን ለማፅናት መስዋትነት እየከፈሉ ለሚገኙ የሀገር መከላከያ ሰራዊት ታላቅ አክብሮት ሰጥተው ኢትዮጲያ በጀግኖች ልጆቿ ታፍራና ተከብራ ትኖራለች ብለዋል።

አቶ ተስፋዬ ደንድር የአዲስ አበባ ከተማ ሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ /ምክትልና የፀጥታ ኦፕሬሽን ዘርፍ ኃላፊ በበኩላቸዉ ኢትዮጲያውያን ለጋራ ዓላማ በጋራና በፅናት የሚኖሩ ህዝቦች መሆናቸውንና ለዚህም የአድዋ ድል ግንባር ቀደም ተጠቃሽ መሆኑን አንስተው አሁን ላይ ታላቁን የህዳሴ ግድብን ጨምሮ ሀገር እንድንታሰራራና ወደ ብልፅግና ማማ እንድትሄድ የለውጡ መንግስት ከመጣ ጀምሮ ውጤታማ ስራዎች በመስራት የጋራ ድምር ዉጤት እየተመዘገበ ይገኛል ብለዋል።

ኃላፊው አክለውም እንደ ሀገር የተገኙ ውጤቶችን ለማስቀጠል ውስጣዊ አንድነታችንን በማጠናከር፤ የይቻላል መንፈስን በማጎልበት፤ድህነትንና ተረጅነትን ታሪክ በማድረግ ኢትዮጲያን አፅንተን እናሻግር ሲሉም መልእክታቸዉን አስተላልፈዋል፡፡

በመርሐግብሩ የፌደራል ፖሊስ ፣ የአዲስ አበባ ፖላስ ፣ የደንብ ማስከበርና የእሳትና አደጋ አባላት የተለያዩ ትርኢቶችና ሀገርና የሚዘክሩ ሁነቶች ተካሂደዋል።

የጽናት ቀንኢትዮጵያን ስናስብ፣ ሌት ተቀን በጽናት በመቆም ሀገርን ከጠላት ለመጠበቅ ወጥተው ለሚያድሩት ብርቱ የፀጥታ ኃይሎቻችን ቅድሚያ ሳንሰጥ ስለ ሁለንተናዊ ከፍታ ማሰብ ፈጽሞ አይቻልም፡፡...
08/09/2026

የጽናት ቀን
ኢትዮጵያን ስናስብ፣ ሌት ተቀን በጽናት በመቆም ሀገርን ከጠላት ለመጠበቅ ወጥተው ለሚያድሩት ብርቱ የፀጥታ ኃይሎቻችን ቅድሚያ ሳንሰጥ ስለ ሁለንተናዊ ከፍታ ማሰብ ፈጽሞ አይቻልም፡፡ ለዚህም ነው በዚህ የጽናት ቀን፣ ለሀገረ-መንግሥታችን ዘላቂነትና ሉዓላዊነት ሲሉ ውድ ሕይወታቸውን የከፈሉትን የጀግኖቻችንን ታሪካዊ መስዋዕትነት በከፍተኛ ሀገራዊ ክብር የምንዘክረው፡፡
ዛሬ ላይ ሀገራችን በራሷ ዕውቀትና በልጆቿ አቅም የላቀ የቴክኖሎጂ ብቃት ያላቸውን ሰው አልባ አውሮፕላኖችን፣ ዘመናዊ የታጠቁ ወታደራዊ ተሽከርካሪዎችን፣ ከባድ መሣሪያዎችንና መድፎችን፣ እንዲሁም ተተኳሽ ጥይቶችን በራሷ ወታደራዊ ኢንዱስትሪዎች ማምረት ችላለች፡፡ ይህ በራስ የመቆም አቅም፣ የሕዝባችን ሰላምና የሁለንተናዊ ኢኮኖሚ እድገታችን ጽኑ መሠረት በመሆኑ፣ ሀገራዊ ጽናታችንን በተጨባጭ ልማትና በጠንካራ የመጠበቅና የመከላከል አቅም እያረጋገጥን የኢትዮጵያን ዘላቂ ብልጽግና እናጸናለን!



ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

የጳጉሜ 2 "የማንሰራራት ቀን" የከተማዋን የመንገድ መሠረተ ልማት እድገት የሚያስቃኝ የፎቶግራፍ አውደ-ርዕይ ለህዝብ እይታ ቀረበ የጳጉሜ 2 "የማንሰራራት ቀን" ምክንያት በማድረግ  ባለፉት ...
07/09/2026

የጳጉሜ 2 "የማንሰራራት ቀን"

የከተማዋን የመንገድ መሠረተ ልማት እድገት የሚያስቃኝ የፎቶግራፍ አውደ-ርዕይ ለህዝብ እይታ ቀረበ

የጳጉሜ 2 "የማንሰራራት ቀን" ምክንያት በማድረግ ባለፉት አምስት ዓመታት በከተማዋ በመንገድ ዘርፍ የተመዘገበውን ስኬት የሚያስቃኝ የፎቶ አውደ-ርዕይ በመሐመዲያ ቪሌጅ ፕላዛ ለዕይታ ክፍት ሆኗል።

የአዲስ አበባ ከተማ መንገዶች ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢንጅነር ሙህዲን ረሻድ፤ ባለፉት 5 ዓመታት ከተማዋን ዘመናዊ የመንገድ መሠረተ-ልማት ባለቤት ለማድረግ መጠነ-ሰፊ ሥራዎች መከናወናቸውን ገልጸዋል።

በተለይም ሞተር አልባ ትራንስፖርት ተጠቃሚነትን ለማሳደግ ምቹና ሰፋፊ የብስክሌት መተላለፊያ መስመሮች፣ የእግረኛ መንገዶችና አረንጓዴ ሥፍራዎችን በመገንባት ለአገልግሎት ማብቃት መቻሉ ጎልቶ የሚጠቀስ ስኬት መሆኑን ተናግረዋል።

ከዚህ በተጨማሪም፤ ለብዙሀን ትራንስፖርት አገልግሎት አሰጣጥ የሚያመቹና አጠቃላይ የትራፊክ ፍሰቱን የሚያሳልጡ የነባር መንገዶች ማሻሻያ፣ የአዳዲስ መንገዶች ግንባታ፣ ዘመናዊና ምቹ የመኪና ማቆሚያ ስፍራዎችና የታክሲ ተርሚናሎች ግንባታ የማንሰራራት ሂደታችን ማሳያዎች መሆኑን ጠቁመዋል፡፡

የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ማርሽ ባንድ የማንሰራራት ቀንን በተለያዩ አደባባዮች በድምቀት አከበረየኢትዮጵያ ብቸኛ ወር የሆነችው የጳጉሜን ቀናት የተለያዩ ሀገራዊ ራዕዮችን በሚያሳዩ ስያሜዎች ...
07/09/2026

የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ማርሽ ባንድ የማንሰራራት ቀንን በተለያዩ አደባባዮች በድምቀት አከበረ

የኢትዮጵያ ብቸኛ ወር የሆነችው የጳጉሜን ቀናት የተለያዩ ሀገራዊ ራዕዮችን በሚያሳዩ ስያሜዎች እየተከበሩ የሚገኙ ሲሆን፤ የዛሬው የጳጉሜን 2 ቀንም “የኢትዮጵያ ማንሰራራት” ቀን በሚል መሪ ሀሳብ በድምቀት ተከብሯል፡፡

ይህንኑ ዕለት በተለዩ አውዶች ለማሰብና ለሕዝብ ለማድረስ የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ማርሽ ባንድ በአዲስ አበባ ከተማ በሚገኙ በተለያዩ አደባባዮች በደምቀት አክብሯል፡፡

ጳጉሜን 2 "የማንሰራራት ቀን" ተብሎ መከበሩ በተጨባጭ እየታዩ ያሉ ሰፋፊ ሀገራዊ ስኬቶችን አመላካች መሆኑን ያሳያል፡፡

ኢትዮጵያ ባለፉት የለውጥ ዓመታት የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚ፣ የተቋማት ግንባታ እና ሌሎች አጠቃላይ ሪፎርሞችን በማድረግ ጠንካራ መሠረት የጣለችበት፤ አሁን ደግሞ የዘላቂ ልማት ትሩፋቶችን ለቀጣዩ ትውልድ የማሸጋገር ወሳኝ ምዕራፍ ላይ መድረሷን የማንሰራራት ጉዞዋ በግልጽ እንደሚያሳይ ተመላክቷል።

በተለይም በታዳሽ ኃይል ልማት፣ በከተሞች ገጽታን የመቀየር ሥራዎች እና በዘመናዊ የኮሪደር ልማት ውጤት ተኮር ተግባራት የተከናወኑበት ወቅት መሆኑ ለቀኑ መበሰር ዋና ምስክሮች ናቸው፡፡

ኢትዮጵያን ከሌሎች ሀገራት ልዩ ከሚያደርጓት ነገሮች አንዱ የጳጉሜን ቀናት ሲሆኑ፣ እነዚህ ቀናትም የተለያየ ትርጉምና ሀገራዊ ራዕይ ተሰጥቷቻ በመከበር ላይ ይገኛሉ፡፡

የመዲናችን የግብርና ምርቶች በተለያዩ አካባቢዎች በተመጣጣኝ ዋጋ እየቀረቡ ነው!ጳጉሜን 2 የማንሰራራት ቀን በተለያዩ ሁነቶች እየተከበረ ነው፡፡የመዲናችንን የከተማ ግብርና እና የሌማት ቱሩፋት...
07/09/2026

የመዲናችን የግብርና ምርቶች በተለያዩ አካባቢዎች በተመጣጣኝ ዋጋ እየቀረቡ ነው!

ጳጉሜን 2 የማንሰራራት ቀን በተለያዩ ሁነቶች እየተከበረ ነው፡፡

የመዲናችንን የከተማ ግብርና እና የሌማት ቱሩፋት ማንሰራራት ማሳያ የሆኑ ምርቶችም በተመጣጣኝ ዋጋ ለተጠቃሚዎች እየቀረቡ ይገኛሉ።

በፒያሳ፣ በሜክሲኮ እና በጋርመንት በከተማችን አርሶ አደሮች የተመረቱ እንቁላል ፣ ዶሮ ፣ እርጎ ፣ አይብ፣ ማር ፣ ሽንኩርት፣ ቲማቲም፣ ጎመን እና የመሳሰሉ የሌማት ቱሩፋት እና የከተማ ግብርና ምርቶች በተመጣጣኝ ዋጋ በመቅረብ ላይ ይገኛል።

በውስን የከተማ ቦታ ላይ ምርታማ መሆን አይቻልም የሚለው የቆየ የተዛባ እሳቤ በመሰበሩ በግለሰቦች እና በተቋማት ላይ የተፈጠረው መነሳሳት ለምርት እና ምርታማነት ከፍ ማለት ጉልህ አስተዋፅዖ አበርክቷል።

 !!በአዲስ ከተማ ክ/ከተማ የጳጉሜ  2 የማንሰራራት ቀን በተለያዩ ዝግጅቶች እየተከበረ ሲሆን የአስተዳደሩ ሰራተኞችም የላቀ አገልግሎት አሰጣጥ መስጠት እንደሚገባ በመስማማት ቀኑን አስበዋው ...
07/09/2026

!!

በአዲስ ከተማ ክ/ከተማ የጳጉሜ 2 የማንሰራራት ቀን በተለያዩ ዝግጅቶች እየተከበረ ሲሆን የአስተዳደሩ ሰራተኞችም የላቀ አገልግሎት አሰጣጥ መስጠት እንደሚገባ በመስማማት ቀኑን አስበዋው ውለዋል::

የላቀ አገልግሎት አሰጣጥ እንዲኖር ከሚያስችሉ ስልቶች ውስጥ አሰራርን ማሻሻል፣ አገልግሎትን ዲጅታላይድ ማድረግ፣ አፈጻጸምን መላካትና የተጠያቂነትን ሥርዓት መዘርጋት እንዲሁም ለውጥ በቶሎ የመቀበል ልምድ በማዳበር የተሰጡ ተግባራት ማከናወን ይገባልም ተብሏል::

የላቀ አገልግሎት ለመሰጠት ከሠራተኞች የሚጠበቁ ጉዳዮችን በተመለከተ የአገልጋይነት ስሜት መፍጠር፣ ሙያዊ ስነ ምግባር መላበስ ፣ የዲጂታል ብቃት መገንባት መቻል፣ ኃላፊነትን መወጣት፣ ቀጣይነት ያለው መሻሻል እንዲኖር እና የህዝብ አመኔታ ማሳደግ ግንባር ቀደም ሥራዎች መሆናቸው ተገልጿል።

በመጨረሻም የአመራሩ ሚና በላቀ አገልግሎት አሰጣጥ የራሱ የሆነ ሁለንተናዊ ተግባራት እንዲመሩና እንዲፈፀሙ የሚያስችል መሆኑ ተጠቁሟል።

ጷጉሜ 2 -2018ዓ/ም

Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Addis Ketema Communication-አዲስ ከተማ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Addis Ketema Communication-አዲስ ከተማ:

Shortcuts

Share