Yeka Woreda 12 Communication-የካ ወረዳ 12 ኮሙኒኬሽን

Yeka Woreda 12 Communication-የካ ወረዳ 12 ኮሙኒኬሽን This is the official page of Yeka Woreda 12 Communication!!

በየካ ክፍለ ከተማ አስተዳደር “6400 A” የዲጂታል በጎነት ፕሮጀክት በይፋ ተጀመረነሐሴ 14/2018 ዓ/ም የካ ወረዳ 12 ኮሙኒኬሽንበየካ ክፍለ ከተማ አስተዳደር የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ተ...
20/08/2026

በየካ ክፍለ ከተማ አስተዳደር “6400 A” የዲጂታል በጎነት ፕሮጀክት በይፋ ተጀመረ

ነሐሴ 14/2018 ዓ/ም የካ ወረዳ 12 ኮሙኒኬሽን

በየካ ክፍለ ከተማ አስተዳደር የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ተሳትፎንና ተጠቃሚነትን ለማሳደግ “6400 A” የዲጂታል በጎነት ፕሮጀክት የማስተዋወቂያና በክፍለ ከተማ ደረጃ የማስጀመሪያ መርሃ ግብር ተካሂዷል።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር በመተባበር ያስጀመረው ይህ የዲጂታል በጎነት ፕላትፎርም፣ የዜጎችን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮች ከተረጅነት በዘላቂነት ለማቃለል የሁሉንም የማህበረሰብ ክፍል በቀላሉ በበጎ ፈቃድ ተግባራት ላይ ለማሳተፍ ያለመ ነው።

በማስጀመሪያ መርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት የየካ ክፍለ ከተማ የብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ መገርሳ ገላና በክፍለ ከተማው በርካታ ሰው ተኮር የሆኑ የበጎ ፈቃድ ተግባራት መከናወናቸውን ገልፀው ሁሉም ሰው የበኩሉን አስተዋፅኦ ሲያደርግ የሰው ሰራሽና ተፈጥሮዊ አደጋን በእራሳችን አቅም ለመፍታት በጋራ መስራ ይገባል ሲሉ አሳስበዋል።

የየካ ክፍለ ከተማ የህብረተሰብ ተሳትፎና በጎ ፈቃድ ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ሀላፊ ወ/ሮ መሰለች አቡዬ በበኩላቸው የበጎ ፈቃድ ተግባር ለበርካታ አቅመ ደካማ ወገኖች፣ ለሀገር ባለውለታዎችና ለዝቅተኛ ገቢ ላላቸው የህብረተሰብ ክፍሎች ድጋፍ ማድረስ መቻሉን ያስረዱ ሲሆን የ“6400 A” ዲጂታል በጎነት ፕሮጀክትም በተለይ አቅመ ደካማና በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ ዜጎችን ለመድረስ የሚያግዝ በመሆኑ የክፍለ ከተማው ነዋሪዎች በፕላትፎርሙ ላይ በመሳተፍ የበጎነት አሻራቸውን እንዲያሳርፉ ጥሪ አቅርበዋል።

የ“6400 A” ፕላትፎርም የበጎነት ባህልን በበለጠ ለማስፋፋት፣ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮችን ለመቅረፍ እንዲሁም ዝቅተኛ ገቢ ላላቸው ዜጎች ዘላቂ ጠቀሜታ ለመፍጠር አስተዋጽኦው ከፍተኛ መሆኑን ገልጸዋል።

ህብረተሰቡ ወደ 6400 “A” የጽሑፍ መልዕክት (SMS) በመላክና በቀን 1 ብር በመለገስ የበጎ ፈቃድ አገልግሎቱን በመደገፍ በጎነትን ማስፋፋትና ፕሮጀክቱ የተቀመጠለትን ዓላማ እንዲያሳካ የበኩሉን አስተዋጽኦ እንዲያበረክት ጥሪ ቀርቧል።

በየካ ክፍለ ከተማ አስተዳደር የ8ኛ ዙር የማካካሻ ኮርስ እጩ ምልምል የሰላም ሠራዊት አባላት ተመረቁነሐሴ 14/2018 ዓ.ም  የካ ኮሙኒኬሽን ወረዳ 12 ኮሙኒኬሽን የየካ ክፍለ ከተማ ሰላምና...
20/08/2026

በየካ ክፍለ ከተማ አስተዳደር የ8ኛ ዙር የማካካሻ ኮርስ እጩ ምልምል የሰላም ሠራዊት አባላት ተመረቁ

ነሐሴ 14/2018 ዓ.ም የካ ኮሙኒኬሽን ወረዳ 12 ኮሙኒኬሽን

የየካ ክፍለ ከተማ ሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ጽ/ቤት በ8ኛ ዙር የማካካሻ ኮርስ ለ1,000 እጩ ምልምል የሰላም ሠራዊት አባላት የንድፈ ሐሳብና የተግባር ሥልጠና በመስጠት አስመርቋል።

በምርቃት ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የተገኙት የየካ ክፍለ ከተማ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ፍፁም ኃይሌ እንደገለጹት የሰላም ሠራዊት አባላት ከጸጥታ መዋቅሩ ጋር በመቀናጀት የከተማችንን ሰላምና ጸጥታ በማስጠበቅ፣ ሀገራዊ፣ ከተማዊና ሃይማኖታዊ የአደባባይ ክንውኖች በሰላም እንዲከናወኑ ከፍተኛ አስተዋጽኦ አድርገዋል።

አዲስ የሰላም ሠራዊት ምልምሎችም በሥልጠናው ያገኙትን እውቀትና ክህሎት በተግባር በመተርጎም ለአካባቢያቸውና ለክፍለ ከተማው ሰላምና ጸጥታ መጠበቅ የድርሻቸውን እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል።

ዋና ሥራ አስፈጻሚው አክለውም፣ የሰላም ሠራዊቱ የሰላም አምባሳደርነቱን በተግባር እያረጋገጠ የውስጥና የውጭ ግጭቶችን በመከላከል ረገድ የሚያበረክተው አስተዋጽኦ ከፍተኛ መሆኑን በመጠቆም ዛሬ የተመረቁት አዲስ ምልምል የሰላም ሠራዊት አባላት የአካባቢያቸውንና የክፍለ ከተማውን ሰላምና ጸጥታ ከሚያውኩ ኃይሎች ለመጠበቅ የተሰጣቸውን ኃላፊነት በብቃት መወጣት እንዳለባቸው አስገንዝበዋል።

የየካ ክፍለ ከተማ ሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሀብታሙ ደረጀ በበኩላቸው የሰላም ሠራዊት አባላት በሥልጠናው ያገኙትን የንድፈ ሐሳብና የተግባር እውቀት ወደ ተጨባጭ ውጤት በመቀየር የአካባቢያቸውንና የከተማዋን ሰላም በተጠናከረ መልኩ ማስቀጠል እንዳለባቸው ገልጸዋል።

የሥልጠናው ተሳታፊ አዲስ ምልምል የሰላም ሠራዊት አባላትም ከጸጥታ አካላት ጋር በቅንጅት በመሥራት የአካባቢያቸውን ሰላም ለማስፈን፣ ወንጀልን ለመከላከልና የሰላም አምባሳደርነታቸውን በተግባር ለማረጋገጥ ቁርጠኛ መሆናቸውን ገልጸዋል።

በምርቃት ሥነ-ሥርዓቱ የሥልጠና ማጠናቀቂያ እና ለአሰልጣኞች ማስረጃ ለምልምል የሰላም ሠራዊት አባላት ተሰጥቷል።

ይምጡና በአዲስ መሶብ የአንድ ማዕከል ድጂታል የመንግስት አገልግሎት የካ ቅርንጫፍ ይገልገሉ!በአዲስ መሶብ የአንድ ማዕከል ድጂታል የመንግስት አገልግሎት የካ ቅርንጫፍ የሚሰጡ አገልግሎቶች #1...
19/08/2026

ይምጡና በአዲስ መሶብ የአንድ ማዕከል ድጂታል የመንግስት አገልግሎት የካ ቅርንጫፍ ይገልገሉ!

በአዲስ መሶብ የአንድ ማዕከል ድጂታል የመንግስት አገልግሎት የካ ቅርንጫፍ የሚሰጡ አገልግሎቶች

#1 መሬት ልማትና አስተዳደር ቢሮ

የባለቤትነት ስመ ንብረት ዝውውር አገልግሎት
የሊዝ ይዞታ መብት ማስተላለፍ
ዋስትና ዕዳና ዕገዳ ምዝገባ አገልግሎት
የዋስት ዕዳ እገዳ የመሰረዝ አገልግሎት
የሊዝ ውል አገልግሎት

#2. ቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ

1. የአከራይ ተከራይ የምዝገባ አገልግሎት
2. የአከራይ ተከራይ ውል ማደስ ወይም ማቋረጥ
3. በኪራይ ቤት አዲስ ውል የማዋዋል አገልግሎት
4. የቤት ቅይይር ጥያቄን ምሊሽ የመስጠት
5. . ተነሺዎች ምትክ ቤት የመመደብ
6. አምስት አመት የሞሊቸዉ የጋራ መኖሪያ ቤቶች ማስረጃ
7. የዉሃና የመብራት ማስገባት የፍቃድ
8. የመንግስት ቤት የኪራይ ውሌ ማደስ ወይም ማቋረጥ
9. የስም ዝውውር አገልግሎት
10 የቤት እድሳትና ጥገና ጥያቄ
11. የመንግስት ቤት አገልግሎት ለውጥ

#3. የመሬት ይዞታና ምዝገባ መረጃ ኤጀንሲ

1. የቋሚ ንብረት እዳ መያዣ ዋስትና ምዝገባ
2. የሪል ስቴት የጋራ ህንጻ ንብረት እዳ ስረዛ
3. የቁራሽ መሬት ይዞታ የፍርድ ቤት ዕግድ ምዝገባ
4. የቋሚ ንብረት እዳ ምዝገባ ዕድሳት
5. የሪል እስቴት የተናጠል ሰርተፍኬት ካርታ
6. የሪል እስቴት የስም ዝውውር

#4. ቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን

1. የጋራ መኖሪያ ቤቶችን ተጠቃሚዎች የማስተላለፍ ስራ
2. የጋራ መኖሪያና ቤቶችን በሸያጭ በጨረታ ማስተላለፍ

#5. የሲቪል ምዝገባና ነዋሪዎች አገልግሎት ኤጀንሲ

1. የልደት ምዝገባና ማስረጃ
2. የጉዲፈቻ ምዝገባና ማስረጃ
3. የፍቺ ምዝገባና ማስረጃ
4. የሞት ምዝገባና ማስረጃ
5. የጋብቻ ምዝገባ ማስረጃ እድሳት
6. የነዋሪነት መታወቂያ አገልግሎት
7. የዲጂታል መታወቂያ

#6. የሥራና ክህሎት ቢሮ

1. የመረጃ ምክርና ግንዛቤ አገልግሎት
2. ስራ ፈላጊዎችን እና ኢንተርፕራይዞችን መመዝገብ
3. በኢንተርፕራይዝ ማደራጀት
4. የአገር ውስጥ ሥራና ሠራተኛ ማገናኘት
5. የፋይናንስ ድጋፍ ማመቻቸት

#7. ገቢዎች ቢሮ

1. የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር መስጠት
2. የኢ ፋይሊንግ እና ኢ ፔይመንት አገልግሎ

#8. ፕላንና ልማት ቢሮ

1. የፕላን ማብራሪያ አስተያየት
2. የውስጥ ለውስጥ መንገድ ጥናት
3. የፕላን መረጃዎችን ማሰራጨት

#9. ብሔራዊ መታወቂያ

1. የፋይዳ መታወቂያ ምዝገባ
2. የፋይዳ መታወቂያ ማስተካከያ

#10. የሰነዶች ማረጋገጫ አገልግሎት

1. የሚንቀሳቀስ እና የማይንቀሳቀስ ንብረቶች ማስተላለፍ ዉል
2. ብድር ውል
3. የሽርክና ማህበር ቃለ-ጉባኤ
4. የሽርክና ማህበር ቃለ-ጉባኤ ማረጋገጥ
5. የትርጉም ሰነዶች ማረጋገጥ
6. የውጭ ጉዳይ ሰነዶች
7. ውል ማፍረሻ
8. ውል ማሻሻያ
9. ውክልና መሻሪያ
10. ቃለ መሀላ
11. ኑዛዜ
12. ድርሻ መልቀቅ
13. ዲክላሬሽን(ማረጋገጫ)
14. ልዩ ልዩ ዉሎች
15. የኪራይ ውል
16. ማህበራት መመስረቻ
17. ውክልና

#11. የኢትዮጵያ ፖስታ

1. የፋይዳ መታወቂያ ቀጠሮ ማስያዝ
2. የፋይዳ መታወቂያ ህትመት
3. የፋይዳ መታወቂያ ምዝገባ
4. የፋይዳ መታወቂያ እደላ
5.የፋይዳ መታወቂያ ማስተካከያ
6. የመንገድ ፈንድ አገልግሎት
7. የጽፈት አገልግሎት

#12. ኢትዮ ቴሌኮም

1. በቴሌብር ለመክፈል
2. ቴሌብር ለመክፈት
3. ሲም ለማውጣት

#13. የትራፊክ ማኔጅመንት ባለስልጣን

1. የተሃድሶ ስልጠና የሚወስዱ አሽከርካሪዎችን ማስተላለፍ
2. የጠፋ ሰሌዳ እና የአሽከርካሪነት ብቃት ማረጋገጫ መንጃ ፈቃድ ወይም ለአሽከርካሪነት ብቃት ማረጋገጫ መንጃ ፈቃድ እድሳት ከአደጋ ነፃ መረጃ መስጠት
3. የትራፊክ ደንብ ተላላፊዎች የአሽከርካሪነት ብቃት ማረጋገጫ ሪከርድ ማጣራት አገልግሎት
4. ለውጪ ሃገር ለኤምባሲ የአደጋ ረከርድ ማረጋገጫ መስጠት

#14. አሽ ተሽ ባለስልጣን

1. የቀረጥ ነፃ ማንaሳት አገልግሎት
2. የተሽከርካሪ እግድ ማንሳት አገልግሎት
3. የተሽከርካሪ ዕዳና ዕገዳ ማከናወን አገልግሎት
4. ለተበላሸ ቦሎ ተለጣፊ ምትክ መስጠት
5. ለጠፋ ቦሎ ተለጣፊ ምትክ መስጠት
6. ለጠፋ ቦሎ ተለጣፊ ምትክ ለመስጠት ለፖሊስ መረጃ መጠየቅ
7. የተሽከርካሪ አመታዊ ብቃት ማረጋገጫ ቦሎ መስጠት
8. በተበላሸ የአሽከርካሪ ብቃት ማረጋገጫ ፈቃድ ምትክ መስጠት
9. ወደ ውጪ ሃገር ለሚሄዱ አሽከርካሪዎች የአሽከርካሪ ብቃት ማረጋገጫ ፈቃድ ትክክለኛነት ማረጋገጫ መስጠት ኢንተርናሽናል
10. በውጪ ሃገር የአሽከርካሪ ብቃት ማረጋገጫ ፈቃድ ምትክ
11. 11. የአዲስ አበባ የአሽከርካሪ ብቃት ማረጋገጫ ፈቃድ መስጠት
12. የአሽከርካሪ ብቃት ማረጋገጫ ፈቃድ እድሳት አገልግሎት መስጠት

#15 ግንባታ ፍቃድና ቁጥጥር ባለስልጠን

1. ዲጂታል ማስታወቂያ ፈቃድ አገልግሎት
2. የህንፃ መጠቀሚያ ፈቃድ አገልግሎት
3. አስቢውልት ፈቃድ መስጠት
4. የስም እና አገልግሎት ለውጥ ፈቃድ መስጠት
5. የህንፃ የማሻሻያ ፈቃድ መስጠት
6. አዲስ ግንባታ ፈቃድ መስጠት
7. ፕላን ስምምነት መረጃ መስጠት አገልግሎት

#16. ንግድ ቢሮ

1. የግለሰብ ቅድመ አካውንት ማጽደቅ
2. የንግድ ማህበራት የንግድ ድርጅት ስም ማሻሻል
3. የግለሰብ ነጋዴና የንግድ ማህበራት የንግድ ምዝገባ ምስክር ወረቀት መስጠት
4. የንግድ ምዝገባ የምስክር ወረቀት ማሻሻል
5.ምትክ የንግድ ምዝገባ የምስክር ወረቀት
የንግድ ምዝገባ ስረዛ
ምትክ የንግድ ሥራ ፈቃድ የምስክር ወረቀት መስጠት
የንግድ ሥራ ፈቃድ የምስክር ወረቀት መሰረዝ
ምትክ የንግድ ስም የምስክር ወረቀት መስጠት
የንግድ ስም የምስክር ወረቀት ማሻሻል
የንግድ ስም የምስክር ወረቀት መሰረዝ
የግለሰብ ማጽደቅ
የግለሰብ ቅድመ ማጽደቅ
የማህበራት ቅድመ አካውንት ማጽደቅ
የንግድ ስም ምዝገባ ምስክር ወረቀት ማውጣት
#17. የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ጤና ቢሮ
1. የጤና አገልግሎት
#18. ኤሌክትሪክ አገልግሎት
1. መክፈል
#19 የምግብ መድሀኒት ባለስልጣን
1. አዲስ ጤና ባለሙያዎች የሙያ ምዝገባና ፈቃድ መስጠት
2. Old Licence (Old License Digitalization)
3. የነባር ጤና ባለሙያዎች የሙያ ምዝገባና ፈቃድ ማደስ
4. ማሻሻያ ያደረጉ የጤና ባለሙያዎች የሙያ ምዝገባና ፈቃድ ማደስ
5. የትምህርት ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን
#20. የትምህርት ማስረጃ ማረጋገጥ አገልግሎት
1. የአዲስ ዕውቅእና የእውቀትና እድሳት ሰርተፊኬት አገልግሎት
2. የደረጃ ፈቃድ ሰርተፍኬት አገልግሎት
3. የመምህራን እና የትምህርት አመራር ሙያ ፈቃድሰርተፊኬት አገልግሎት
#21. ቅድመ አገልግሎት
1. ጠቅላላ አገልግሎት መስጠት
ባንኮች
#22. ንግድ ባንክ
#23. ስኬት ባንክ

በየካ ክ/ከተማ ወረዳ 12 የአገልግሎት አሰጣጥ ሂደት በጥራትና በቴክኖሎጂ ተጠናክሮ ቀጥሏ።ነሐሴ 13/2018 ዓ/ም የካ ወረዳ 12 ኮሙኒኬሽን በየካ ክ/ከተማ ወረዳ 12 ለነዋሪዎችና ለተገልጋ...
19/08/2026

በየካ ክ/ከተማ ወረዳ 12 የአገልግሎት አሰጣጥ ሂደት በጥራትና በቴክኖሎጂ ተጠናክሮ ቀጥሏ።

ነሐሴ 13/2018 ዓ/ም የካ ወረዳ 12 ኮሙኒኬሽን

በየካ ክ/ከተማ ወረዳ 12 ለነዋሪዎችና ለተገልጋዮች የሚሰጡ የተለያዩ የአስተዳደርና የሕዝብ አገልግሎቶች በጥራት፣ በፍጥነትና በተጠያቂነት እንዲሰጡ የሚደረገው ሥራ ተጠናክሮ ቀጥሏል።

የወረዳው አስተዳደር ተገልጋዮች ያለአስፈላጊ መጉላላት አገልግሎታቸውን በወቅቱ እንዲያገኙ የአሠራር ሥርዓቶችን በማሻሻል፣ የሥራ ሂደቶችን በማቀላጠፍና ቴክኖሎጂን በማስገባት ተገልጋይ ተኮር የአገልግሎት አሰጣጥን ለማጠናከር ትኩረት እየሰጠ መሆኑ ተገልጿል።

ተገልጋዮች እንደተናገሩት፣ ከጊዜ ወደ ጊዜ በወረዳው የሚሰጡ አገልግሎቶች በጥራትና በፍጥነት እየተሻሻሉ መምጣታቸው አስደስቷቸዋል። በተለይም ቴክኖሎጂን በመጠቀም ሂደቶችን ማቀላጠፍ የተገልጋዮችን ጊዜና ጉልበት ለመቆጠብ አዎንታዊ ሚና እየተጫወተ ነው ብለዋል።

አገልግሎቱ በተገልጋይ እርካታ ላይ የተመሠረተ እንዲሆን የሠራተኞች የአገልግሎት አሰጣጥ አቅምን ማሳደግ፣ ለተገልጋዮች ግልጽና ተደራሽ መረጃ መስጠት፣ የቅሬታና ጥቆማ ሥርዓቶችን ማጠናከር እና የሥራ ክትትልን ማሻሻል እንደ ቀጣይ አቅጣጫዎች ተጠቅሰዋል።

ከዚህም በተጨማሪም የተገልጋዮችን አስተያየት በመቀበል የአገልግሎት ክፍተቶችን በመለየትና በፍጥነት በማስተካከል ተገልጋይ እርካታን ማሳደግ የሚገባ መሆኑ ተገልጿል። ይህም የአስተዳደሩን ተቋማዊ አቅም ከማጠናከር ባለፈ ከሕዝብ ጋር ያለውን የመተማመን ግንኙነት ለማጠናከር ወሳኝ መሆኑ ተመላክቷል።

"የሰላም ሰራዊቱ ከነዋሪውና ከፀጥታ አካላት ጋር በመቀናጀት ሁሌም የአካባቢውን ሰላም በንቃት በመጠበቅ እያደረገው ያለው ተሳትፎ በቀጣይም ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል"!!አቶ ፍስሃ ጥበቡየአዲስ ...
18/08/2026

"የሰላም ሰራዊቱ ከነዋሪውና ከፀጥታ አካላት ጋር በመቀናጀት ሁሌም የአካባቢውን ሰላም በንቃት በመጠበቅ እያደረገው ያለው ተሳትፎ በቀጣይም ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል"!!
አቶ ፍስሃ ጥበቡ
የአዲስ አበባ ከተማ ሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ምክትል ቢሮ ኃላፊ

ነሀሴ12/2018ዓ•ም የካ ወረዳ 12 ኮሙኒኬሽን

የሰላም ሠራዊት አባላት የአካባቢ ሰላምን በማስጠበቅና ቅድመ ወንጀልን በመከላከል ጉልህ ሚና እየተወጡ መሆኑ ተገለፀ

በየካ ክፍለ ከተማ አስተዳደር የአንድ ማዕከል የሰላም ሠራዊትና የፀጥታ መዋቅር ስምሪት የከተማና የክፍለ ከተማ ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት በወረዳ 06 በሚገኘው 28 ሜዳ ላይ ተሰጥቷል።

ስምሪቱ የአካባቢውን ሰላምና ፀጥታ በማስጠበቅ፣ ቅድመ ወንጀልን በመከላከልና የህብረተሰቡን ደህንነት በማረጋገጥ የተሻለ የሰላም ሁኔታ መፍጠር መሆኑ ተገልጿል።

በአንድ ማዕከል ስምሪት አሰጣጡ ላይ የአዲስ አበባ ከተማ ሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ ፍስሐ ጥበቡ እንደገለፁት የሰላምና ፀጥታ ሥራ የተወሰነ ጊዜና ቦታ የማይገድበው በመሆኑ በቅንጅትና በተቀናጀ መልኩ መሥራት የአካባቢውንና የከተማዋን ሰላም ለማረጋገጥ ወሳኝ መሆኑን አስገንዝበዋል።

አቶ ፍስሐ አክለውም አሁን ያለንበት ወቅት ከፀጥታ አንፃር ልዩ ትኩረትን የሚጠይቅ በመሆኑ የአካባቢውን ፀጥታ በትጋት 24/7 መጠበቅ እንደሚገባ በማሳሰብ በተለይም የሰላም ሠራዊት አባላት በቅድመ ወንጀል መከላከልና የህብረተሰቡን ሰላም በማስጠበቅ የሚያበረክቱት አስተዋፅኦ ከፍተኛ መሆኑንም ጠቁመዋል።

የየካ ክፍለ ከተማ ሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሀብታሙ ደረጀ በበኩላቸው የሰላም ሠራዊት አባላት ከመደበኛው የፀጥታ መዋቅር ጋር በመቀናጀትና በተቀናጀ አሠራር በመስራት አስተማማኝ ሰላም ለማረጋገጥ የሚያደርጉት ሚና የላቀ መሆኑን ገልጸዋል።

የሰላምና ደህንነት ሥራውም ከተለመደው መዋቅራዊ አሠራር በተጨማሪ ህብረተሰቡን በማሳተፍና የሰላም ሠራዊትን ሚና በማጠናከር በቀጣይነት እንደሚጠናከር አቶ ሀብታሙ ገልጸዋል።

የሰላም ሠራዊትና የፀጥታ መዋቅሮች በቅንጅት በመሥራት ቅድመ ወንጀልን በመከላከል፣ የህብረተሰቡን የሰላም ንቃተ ህሊና በማጎልበትና የአካባቢውን ፀጥታ በማስጠበቅ የየካ ክፍለ ከተማን ሰላም ለማረጋገጥ የሚያደርጉት ተግባር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተገልጿል።

18/08/2026
የኮሪደር እና የወንዝ ዳር ልማቶች ገጽታን ከመቀየር ባለፈ በአእምሮ፣ በጤና እና በአካል የበለጸገ ትውልድን ለመገንባት ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከቱ ነውበአዲስ አበባ የተገነቡ የኮሪደር እና የ...
18/08/2026

የኮሪደር እና የወንዝ ዳር ልማቶች ገጽታን ከመቀየር ባለፈ በአእምሮ፣ በጤና እና በአካል የበለጸገ ትውልድን ለመገንባት ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከቱ ነው

በአዲስ አበባ የተገነቡ የኮሪደር እና የወንዝ ዳርቻ ልማቶች ገጽታን ከመቀየር ባለፈ በአእምሮ፣ በጤና እና በአካል የበለጸገ ትውልድን ለመገንባት ጉልህ አስተዋጽኦ እንዳላቸው ነዋሪዎች ገለጹ።

በአዲስ አበባ ከተማ የተከናወኑ የኮሪደር እና የወንዝ ዳርቻ ልማት ሥራዎች የከተማዋን መሠረተ ልማት ከዘመኑ ጋር በማስተሳሰር፣ የነዋሪዎችን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ደህንነት ማሻሻልና አረንጓዴ ቦታዎችን በማስፋፋት ትርጉም ያለው ለውጥ ማምጣት ችለዋል።

ከተማዋን ለቱሪስቶች ማራኪ ከማድረጉም በላይ በወንዞች ዳርቻዎች ላይ የነበሩ የጎርፍ አደጋ ስጋቶችን በመቀነስ ህብረተሰቡ ንጽህናው የተጠበቀ የመኖሪያ እና መዝናኛ ስፍራዎችን እንዲያገኝ አድርጓል።

በዚህም ዘላቂ የከተማ ልማት እውን እንዲሆን በማስቻል የዜጎችን የኑሮ ጥራት ከፍ አድርጓል።

አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡት የመዲናዋ ነዋሪዎች፣ የኮሪደር እና የወንዝ ዳርቻዎች ልማት ሥራ ከፍተኛ የገጽታ ግንባታ ከመፍጠሩም በላይ ሁሉንም ተጠቃሚ ማድረግ የቻለ አካታች ልማት መሆኑን ተናግረዋል።

የአዲስ አበባ ነዋሪ ሲሳይ ተስፋዬ እንደገለጹት፤ የተከናወኑት ግዙፍ የልማት ሥራዎች ለንባብ፣ ለምርምር እና ለህፃናትና ወጣቶች መዝናኛ ያላቸው ፋይዳ ከፍተኛ ነው።

በተለይም የቱሪዝም ፍሰትን በማሳደግና የውጭ ምንዛሬ ገቢን በመጨመር ረገድ ወሳኝ ሚና እንደሚጫወት እምነታቸውን ገልጸዋል።

በመሆኑም ህብረተሰቡ የተገነቡት መሠረተ ልማቶች ያላቸውን ዘርፈ ብዙ ፋይዳ በመገንዘብ በባለቤትነት ስሜት ሊንከባከባቸውና ሊጠብቃቸው እንደሚገባ አንስተዋል።

አልማዝ ባሻ በበኩላቸው፣ መንግሥት በከተማዋ ያከናወናቸው የልማት ሥራዎች አዲስ አበባን ዘመናዊ፣ ጽዱ እና ለኑሮ ተስማሚ እንዳደረጓት ገልጸዋል።

ሀገር ተረካቢው ትውልድም የእረፍት ጊዜውን በመናፈሻዎችና በስፖርት ማዘውተሪያዎች የሚያሳልፍበት ምቹ ሁኔታ መፈጠሩንም ጠቁመዋል።

ይህም መንግስት ለአሁን እና ለቀጣዩ ትውልድ የምትሆን ሀገር እየገነባ መሆኑን ያሳያል ብለዋል።

ደስታ መአረንዳ እና አዱኛ ጌትነት እንዳሉት በአዲስ አበባ አሁን ላይ የሚገባትን ውበት እና ክብር መጎናጸፍ ችላለች።

ይህ ሊሆን የቻለው በአእምሮ፣ በጤና እና በአካል የበለጸገ ትውልድን ለመፍጠር ታሳቢ ያደረጉ ሁለንተናዊ የከተማ ልማት ሥራዎች በስፋት በመሰራታቸው መሆኑን አንስተዋል።

የወንዝ ዳርቻ፣ መጽዳት ቤቶችና ቆሻሻ አወጋገድ በመስተካከሉ መጥፎ ሽታዎችን በማስቀረት ለነዋሪዎች፣ ለህፃናት፣ ለሁሉም ህብረተሰብ ክፍሎች እንዲሁም ለቱሪስቶችም ጭምር ዘመኑን የሚመጥን ከተማ ተፈጥሯል ያሉት ደግሞ ክብሩ ወልደሰንበት እና ወልዱ ግርማ ናቸው።

መንግስት ቀደም ሲል የተዘነጉ ጉዳዮች ላይ ከፍተኛ በጀት በመመደብ ለዜጎች የኑሮ ዘይቤ መሻሻል የሚያደርገው ቁርጠኛ አካሄድ የሚደነቅ መሆኑንም ተናግረዋል።

ተመራቂ የፖሊስ  መኮንኖች እንኳን ደስ አላችሁ! ዛሬ በአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሌጅ  በሁለተኛ ዙር የሰለጠኑ 864 የፖሊስ  መኮንኖችን መርቀናል።  ተመራቂዎቹ በንድፈ ሀሳብ እና በተግባር  በጠ...
15/08/2026

ተመራቂ የፖሊስ መኮንኖች እንኳን ደስ አላችሁ!

ዛሬ በአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሌጅ በሁለተኛ ዙር የሰለጠኑ 864 የፖሊስ መኮንኖችን መርቀናል።

ተመራቂዎቹ በንድፈ ሀሳብ እና በተግባር በጠንካራ ዲሲፕሊን ስልጠናቸውን በብቃት ያጠናቀቁ ፤ በአካልና በመንፈስ ጠንክረው የወጡ በመሆናቸው በፖሊስ መኮንንነት ማዕረግ ተመርቀዋል።
ተመራቂዎች በቆይታችሁ ያገኛችሁት እውቀት ለላቀ ፖሊሳዊ ስብዕና የሚያበቃችሁ እንደመሆኑ ወደ ስራ ስትሰማሩም ያለአድልዎና ልዩነት በታማኝነት፣ በጀግንነት፣ በሰብዓዊነትና በክብር፣ የህግ የበላይነት እንዲረጋገጥ እንደምታገለግሉ ሙሉ እምነት አለኝ።
በድጋሚ እንኳን ደስ አላችሁ!

ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ህዝቦቿን ይባርክ!

በየካ ሰማይ ስር የአዲስ አበባ ከተማን ከፍታ ያረጋገጡ የኮሪደርና የቀበና ወንዝ ዳርቻ ልማቶች!ነሐሴ 10/2018 ዓ.ም የካ ወረዳ 12 ኮሙኒኬሽን
15/08/2026

በየካ ሰማይ ስር የአዲስ አበባ ከተማን ከፍታ ያረጋገጡ የኮሪደርና የቀበና ወንዝ ዳርቻ ልማቶች!
ነሐሴ 10/2018 ዓ.ም የካ ወረዳ 12 ኮሙኒኬሽን

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Yeka Woreda 12 Communication-የካ ወረዳ 12 ኮሙኒኬሽን posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share