17/03/2026
ኢትዮጵያዊያን በነጻነት በከተማቸው ውስጥ ዘና ብለው የእግር ጉዞ ሲያደርጉ ተመለከትን!
የአፍሪካ ህብረት ታዳሚዋ ስለ አዲስ አበባ ከተማ አንጸባራቂ ልማት የሰጡት አስተያየት።
ሰሞኑን አዲስ አበባ ነበርኩ። ከሆቴላችን ወደ አፍሪካ ህብረት ስብሰባ ስንጓዝ ስለ ከተማዋ ዕድገት እንጂ ስለምንም አላወራንም።
እነሱ በአዲስ አበባ ውስጥ ይህንን ስሰሩ እኛ ለምን መስራት አቃተን የሚል ውይይት ስናደርግ ነው የሄድነው።
ከአምስት ዓመታት በፊት አዲስ አበባ ሄጄ ነበር። ዛሬ ከአምስት ዓመታት በኋላ ተመልሼ ስመጣ ከተማዋን መለየት ሁሉ አልቻልኩም። መንገድ ስሰሩ በከፍተኛ ንቃተህሊና ነው።
ደረጃቸውን የጠበቁ አራትና አምስት መስመር መንገዶችን በከተማዋ ውስጥ መገንባት ችለዋል። ማንኛውም ኢትዮጵያዊ በእግሩ የሚሄድበት ሰፊና ምቹ የእግረኛ መንገዶችን በስፋት ገንብተዋል።
ኢትዮጵያዊያን በነጻነት በከተማቸው ውስጥ ዘና ብለው የእግር ጉዞ ሲያደርጉ ተመለከትን።
አካባቢያቸውን ለመጠበቅ ዛፎችን እየተከሉ ነው!