Sami Gatlang James Page

Sami Gatlang James Page Jesus you have turned My Life around, I'm a living testimony,I'm so blinded by your grace ✨️ 🎶 .

(ዘ-ሐበሻ ዜና) በጋምቤላ ክልል ኢታንግ ልዩ ወረዳ ተርፋም ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ታኅሣሥ 15 ቀን 2018 ዓ.ም (እ.ኤ.አ. ዲሴምበር 24/2025) በደረሰ ጥቃት ቢያንስ 47 ሰዎች መገደ...
25/12/2025

(ዘ-ሐበሻ ዜና) በጋምቤላ ክልል ኢታንግ ልዩ ወረዳ ተርፋም ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ታኅሣሥ 15 ቀን 2018 ዓ.ም (እ.ኤ.አ. ዲሴምበር 24/2025) በደረሰ ጥቃት ቢያንስ 47 ሰዎች መገደላቸውን የአካባቢው ምንጮች ገለጹ። በዚሁ ዕለት በክልሉ የተቀሰቀሰውን መጠነ ሰፊ ጥቃት ተከትሎ የድንበር የለሽ ሐኪሞች ቡድን (MSF) ከመቶ በላይ በጦር መሣሪያ የቆሰሉ ሰዎችን ማከሙን አስታውቋል።

ጥቃቱ የተፈጸመው በተርፋም ንዑስ ከተማ የመኖሪያ መንደር ውስጥ ሲሆን፣ ሰለባዎቹም ሴቶች፣ ሕፃናትና አካል ጉዳተኞችን ያካተቱ መሆናቸውን የዓይን እማኞች ገልጸዋል። በጥቃቱ የመኖሪያ ቤቶች መቃጠላቸውና ነዋሪዎች ከቤት ንብረታቸው መፈናቀላቸውም ተመልክቷል። ድርጊቱ ድንበር ተሻግረው ከመጡ ግለሰቦች ጋር በተቀናጀ ሁኔታ የተፈጸመ መሆኑን ምንጮች ቢጠቁሙም፣ የሟቾች ቁጥር ከመጀመሪያ ደረጃ መረጃ የተገኘ በመሆኑ ወደፊት ሊጨምር እንደሚችል ተገልጿል።

የድንበር የለሽ ሐኪሞች ቡድን ታኅሣሥ 15 ቀን ባወጣው እና ለዘ-ሐበሻ የደረሰው መግለጫ፣ በክልሉ ያለው ግጭት ከጠዋት ጀምሮ መጠናከሩንና ድርጅቱ በአንድ ቀን ውስጥ ብቻ ከ100 በላይ በጦር መሣሪያ የቆሰሉ ሰዎችን መቀበሉን አረጋግጧል። ግጭቱ የሚቀጥል ከሆነ በቀጣይ ቀናት ተጨማሪ ቁስለኞች ሊመጡ እንደሚችሉም ድርጅቱ አስጠንቅቋል።

ይህንን እየተባባሰ የመጣውን የጸጥታ ችግር ተከትሎ የጋምቤላ ክልል መንግሥት ታኅሣሥ 16 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ የሚተገበር ያልተገደበ የሰዓት እላፊ ገደብ ጥሏል። ገደቡ የጋምቤላ ከተማን ጨምሮ አለመረጋጋት የሚታይባቸውን ሌሎች አካባቢዎችን የሚሸፍን መሆኑ ተገልጿል።

Address

Addis Ababa

Telephone

+251929236184

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Sami Gatlang James Page posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Sami Gatlang James Page:

Shortcuts

Share

Category