17/06/2026
የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት አመራሮችና ሰራተኞች በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ውይይት አካሄዱ
////////
የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት አመራሮችና ሰራተኞች በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች፣ በተቋሙ የ10 ዓመት የልማት ዕቅድ አፈጻጸም እና በካፒታል ፕሮጀክቶች እንቅስቃሴ ላይ ያተኮረ ውይይት አካሂደዋል።
ውይይቱን የከፈቱት የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር እና በዓለም የሚቲዎሮሎጂ ድርጅት የአፍሪካ ክልል ፕሬዚዳንት ዶክተር ፈጠነ ተሾመ እንደገለጹት፣ መድረኩ ኢትዮጵያ 7ኛውን ሀገራዊ ምርጫ በተሳካ ሁኔታ ካከናወነች በኋላ የተካሄደ በመሆኑ ለሀገራዊ ጉዳዮች የጋራ ግንዛቤ በመፍጠር ረገድ ከፍተኛ ጠቀሜታ አለው ብለዋል።
በዚሁ ወቅት ዶክተር ፈጠነ ተሾመ የኢንስቲትዩቱን የ10 ዓመት የልማት ዕቅድ (2013–2022 ዓ.ም.) አፈጻጸም እና የካፒታል ፕሮጀክቶችን እንቅስቃሴ በተመለከተ ዝርዝር ገለጻ አቅርበዋል።
ተሳታፊዎችም በቀረበው ገለጻ ላይ ሰፊ ውይይት በማድረግ ተቋሙ በተለያዩ ዘርፎች ያስመዘገባቸውን ውጤቶች አድንቀው፣ ወደፊት የተሻለ አፈጻጸም ለማስመዝገብ የሚያስችሉ ገንቢ አስተያየቶችና ጥያቄዎችን አቅርበዋል።
ለተነሱት ጥያቄዎች ምላሽ የሰጡት ዶክተር ፈጠነ ተሾመ፣ በበጀት ዓመቱ የቀሩ ተግባራትን በፈጣንና ውጤታማ አሰራር በማጠናቀቅ የላቀ አፈጻጸም ለማስመዝገብ አመራሩና ሰራተኞች በቅንጅትና በትጋት እንዲሰሩ አሳስበዋል።
ውይይቱ በተቋሙ የወደፊት አቅጣጫዎች ላይ የጋራ ግንዛቤ በመፍጠር እና የተቋሙን የአፈጻጸም ውጤት የበለጠ ለማሻሻል የሚያግዙ ሀሳቦችን በማሰባሰብ ተጠናቋል።